Wednesday, 22 May 2013

ከእነ መላኩ ፈንታ እስር በስተጀርባ


ሁለት የመንግስት ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ከ12 ያላነሱ ነጋዴዎችና ባለ ሀብቶች በሙስና ተጠርጥረው ወደ ማረፊያ ቤት እንዲወርዱ መደረጋቸው አይዘነጋም፡፡
በሚኒስትር ደረጃ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የሆኑት አቶ መላኩ ፈንታና ምክትላቸው አቶ ገብረዋህድ ወ/ጊዮርጊስ የእስር ማዘዣ ወጥቶባቸው በቁጥጥር ስር እንዲውሉ የመደረጋቸው ዜና ይፋ ከሆነ በኋላ ከየአቅጣጫው የተለያዮ አስተያየቶች እየተደመጡ ነው፡፡ከባለስልጣናቱ መታሰር በኋላ በፓርላማ በመገኘት የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽንን የአስር ወር ሪፓርት ያቀረቡት ኮሚሽነሩ አቶ አሊ ሱሌይማን ሰዎቹ መታሰር በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ትዕዛዝ ተፈጸመ ነው በማለት መናገራቸውን ኢቴቪ በዜና ዘገባው አስደምጧል፡፡
ለመሆኑ ጸረ ሙስና ኮሚሽን ለምን በአንድ መስሪያ ቤት ብቻ በማነጣጠር ሁለቱን ባለስልጣናት ዘብጥ እዲወርዱ አደረገ፣ሙስኛ በመስራትስ ከኢህአዴግ ሹመኞች ሊጠየቁ የሚገባቸው ሁለቱ ሰዎች ብቻ ናቸው(ምንም እንኳን ኮሚሽነሩ በፓርላማ ቀርበው ሌሎችም እንደሚጠየቁ የተናገሩ ቢሆንም)  ኮሚሽኑ ለምን ትልልቆቹን አሳዎች ሳያጠምድ ቀረ; የእነዚህን ጥያቄዎች ምላሽ ለማግኘት ሁለት ጋዜጠኞችንና አንድ ወጣት ፖለቲከኛን አነጋግረናል፡፡
ወጣቱ ፖለቲከኛ ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት አባል ሲሆን በወቅታዊው ጉዳይ በሰጠው አስተያየት‹‹ኢህአዴግ የፖለቲካ ፕሮግራሙም ሆነ አሁን እየወሰዳቸው የሚገኙ አንዳንድ ድርጊቶች  ሙስናን ቆርጦ ለመዋጋት ያለውን ተነሳሽነት ያሳዩለታል ብዬ አላምንም፡፡ሙስናን መዋጋት ባህሪውም አይደለም፡፡ከሙስና የጸዳ አካል በድርጅቱ ውስጥ ይገኛል ማለት በጣም ያስቸግራል፡፡የሰሞኑ ድርጊት በውስጥ ፖለቲካ እየተፈጠረ ያለውን ነገር ከማሳየት የዘለለ ትርጉም ይኖረዋል ብዬ አላምንም፡፡እንዳንድ ባለስልጣናት አገር ጥለው እንዲሄዱ ሌሎቹ ደግሞ እንዲታሰሩ አድርጓል ይህ የውስጥ ፖለቲካ ነጸብራቅ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ ››
በሚኒስትር ደረጃ የሚገኙትን የአቶ መላኩ ፈንታ እስርን በመመልከት ጸረ ሙስና አቅሙን እያዳበረ መጥቷል በማለት መናገር እንችላለን የሚል ጥያቄ ከፍኖተ ነጻነት የቀረበለት ሀብታሙ‹‹ለእኔ አቶ መላኩ ከትልልቆቹ አሳዎች የሚመደቡ አይደሉም፡፡እንደሚታወቀው ሰውዬው በአብዛኛው የሚታወቁት ሞያዊ በሆነ ስራ እንጂ ወደ ፖለቲካው ገፍተው በመምጣታቸው አይደለም፡፡በቅርቡም እርሳቸው የሚመሩት ድርጅት በአፈጻጸም ረገድ ከመንግስት መስሪያ ቤቶች የተሻለ ነጥብ ማስመዝገቡ አይዘነጋም፡፡በእውነትም መስሪያ ቤቱ በለውጥ ጎዳና ላይ እንደነበር መናገር ይቻላል፡፡ይህ ማለት ግን በአቶ መላኩ የተሰራ ሙስና አልነበረም ማለት አይደለም፡፡ነገር ግን በአፈጻጸም ረገድ የመጀመሪያውን ደረጃ ካገኘው ድርጅት የሙስናን ማጣራት ማድረግ ተገቢ ነው; ለሚለው ጥያቄ ኢህአዴግ ምላሽ ያለው አይመስለኝም››ብሏል፡፡
የፍትህና የልዕልና ጋዜጦች ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ኃይለመስቀል በሸዋምየለህ ‹‹ክርክሩ ሰዎቹ ሙስናውን ሰርተዋል ወይም አልሰሩም አይደለም፡፡ትልቁ ነገር መሆን ያለበት ሌሎቹስ ንጹህ ናቸውን የሚለው ነው፡፡ለዚህ ጥያቄ የምንሰጠው ምላሽ ምን እየተካሄደ ነው የሚለውን  ለማወቅ ይረዳናል፡፡ባህርዳር ላይ ተካሂዶ በነበረው ዘጠነኛው የኢህአዴግ ጉባዔ አቶ መላኩ ፈንታ ሁለት መቶ የሚደርሱ ትግርኛ ተናጋሪ የሆኑ የኢኮኖሚ ልሂቃን ግብር በመሰብሰቡ ረገድ አላሰራ እንዳሏቸው ተናግረው ነበር፡፡በዚህ ሁኔታም መላኩ በአመትና በመንፈቅ ይገኛል በማለት ይተብቀው የነበረ ግብር ወርዶበታል፡፡ እንዲህ ከሆነ ደግሞ ህወሃት በሚታይና በማይታይ እጁ የራሱን ደጋፊዎች የኢኮኖሚ አቅም እያጎለበተ ነው ማለት ነው፡፡መላኩ በጉባዔው የብአዴን አለቆቹን እነ በረከትን ሳያስፈቅድ ሪፖርቱን ያቀርባል የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ ያነሳው ነጥብ ለህወሃት ከፍተኛ ቀውስ ሊፈጥር የሚችል በመሆኑ ለእስሩ የወዲያውኑ ምክንያት እንደሆነ ይሰማኛል››ብሏል፡፡
ለኃይለ መስቀል ገብረዋህድ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ያደረጉት ንግግር አስቂኝ ነገር ሆኖበታል ምክንያቱን ሲያብራራም‹‹አስቂኙ ነገር የገብረዋህድ ወይም የባለቤቱ መታሰር አይደለም፡፡ወዴት እየሄድን ነው በማለት መናገራቸው አስቂኝ ነው፡፡››አቶ መላኩ ሁለት መቶ የሚደርሱት ነጋዴዎች ባደረሱባቸው ጫና ለእስር ተዳርገዋል የሚለው መከራከሪያ ለምን ከመታሰራቸው ቀደም ብሎ ህዝብ እንዲያውቀው አልተደረገም የሚል ጥያቄ የቀረበለት ኃይለ መስቀል‹‹አቶ መላኩ በጉባዔው እንዲህ አይነት ሪፖርት ስለ ማቅረባቸው መረጃ አለ፡፡ይህንን ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት አንድ የተማመኑበት ሃይል እንዳነበር ይሰማኛል በስተመጨረሻ ግን ይህ ሃይል ሳይከዳቸው አልቀረም፡፡መላኩ የሚተማመንበት አንድ ነገር ሳይኖር በአደባባይ ይቅርና ኮሪደር ላይ እንኳን ሊናገረው አይደፍርም፡፡ስለዚህ በእርግጠኝነት የብአዴን ዋነኛ ሰዎች መላኩን መስዋዕት እንዳደረጉት መመልከት
እንችላለን›› ብሏል፡፡
በቅርቡ የኢህአዴግ ፍጻሜ የተሰኘን መጽሀፍ በማሳተም ለንባብ አብቅቷል ጋዜጠኛ ሰለሞን ስዮም፡፡ሰለሞን ኢህአዴግ በሙስና የተፈጠረ ሙስና እንደ ጋንግሪን ሊቆርጠው የደረሰ ድርጅት መሆኑን በማውሳት‹‹የሰዎቹ እስራት ምክንያት ይህ ነው በማለት መናገር ባይቻልም የህወሃት መነሻ በራሱ ከዝርፊያ ጋር የተቆራኘ መሆኑን አክሱም ውስጥ የሚገኝን ባንክ ገጠመኝ ማስታወስ ብቻ ይበቃል፡፡በ1978 ደግሞ ማሊሌት ሲመሰረት መለስ ዜናዊና አረጋዊ በርሄ ይከራከሩ ነበር፡፡ በወቅቱ መለስ እየጎመራ የመጣ ወጣት ነበር፡፡ መለስ አረጋዊን በክርክር መርታት እንደማይችል ሲረዳ ‹‹አረጋዊ ጋንግሪን ነው ቶሎ ቆርጠን ካላወጣነው ድርጅቱን ይበክላል›› በማለት እንዲባረር አደረገው፡፡ ህወሃት አረጋዊን በማባረር ጋንግሪኑን ቆርጦ አውጥቶ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ሙስናውን የተወሰኑ ባለስልጣናትን በማሰር ብቻ ያጠፋዋል የሚልእምነት የለኝም፡፡ምክንያቱም ሙስናው እስከ አናቱ ድረስ ውጦታል፡፡ሌላው በከፍተኛ ደረጃ ሙስና ያልሰራ የትኛው ባለስልጣን ነው ብለህ ብትፈልግ ነጻ ሰው ማግኘት ስለመቻልህ እጠራጠራለሁ ከተማው የሚያወራውም ይህንኑ ነው፡፡ መለስ የ1993 ክፍፍል ይፋ ከመሆኑ በፊት ባቀረበው የቦናፓርቲዝም ጽሁፉ ሙስና በቤተሰባዊነት ውስጥ ያለውን ትስስር ጠቅሶ ነበር፡፡በዚህ መነሻነትም በኋላ ላይ ስዬና ወንድሞቹ በሙስና ለመጠየቅ በቅተዋል፡፡እንዳለመታደል ሆኖ ግን መለስ በቦናፓርቲዝም ሌሎቹን ለማጥቂያነት ተጠቀመበት እንጂ የራሱን ቤተሰብ ሊመለከትበት አልፈቀደም፡፡አሁን እያንዳንዱን ሰው ከሴት የኢህአዴግ አመራሮች መካከል ዋነኛዋ ሙሰኛ ማንናት በማለት ብትጠይቅ ብዞዎቹ የሚጠቅሱልህ የመለስን የቀድሞ ባለቤት ናት፡፡
ሰለሞን መረሳት የሌለበት በማለት የሚጠቁመው ነጥብ‹‹ኢህአዴግ አባላቱን የሚያበዛበትን መንገድ እንድንመረምር ነው፡፡‹‹በድርጅቱ ውስጥ የሚገኙ ሰዎች በድርጅቱ ርዕዮተ አለም አምነው የተመዘገቡ አይደሉም፡፡ምክንያቱም ድርጅቱ ወጥ የሆነ የፖለቲካ ፍልስፍና የለውም፡፡የሚበዙትን ሰዎች ወደ ኢህአዴግነት እያመጣቸው የሚገኘው ነገር ጥቅም ብቻ ነው፡፡ይህ ደግሞ ሙስና ነው፡፡››በማለት አስተያየቱን ቋጭቷል፡፡

Sunday, 19 May 2013

የወያኔ ጉድ ማለቂያ የለውም


የወያኔ ጉድ ማለቂያ የለውም
ሰማያዊ ፓርቲ ከግንቦት 15 እስከ 17 ጥቁር አልባሳት በመልበስ እንዲሁም ግንቦት 17 በአፍሪቃ ህብረት ጽ/ቤት ፊለፊት የተቃውሞ ሠልፍ መጥራቱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን እንጂ ከዚህ በፊት ያልታሰበበት ነገር ግን የተጠራውን የተቃውሞ እንቅስቃሴ ትኩረት ለማስቀየር ከግንቦት 11 እስከ 18 ቀን 2005 ዓ.ም የሚቆይ የተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚያደርግ በተለያዩ የአ/አ አካባቢዎች በተለጠፉ ማስታወቂያዎች አስነብቦናል፡፡ ለዚህም ዝግጅት እስከ 25 ሚሊየን ብር እንደተመደበ ከምንጮቻችን ለማወቅ ችለናል፡፡ ይህን ያህል ገንዘብ ለእንደዚህ አይነት ተልካሻ ዓላማ ለማዋል መባከኑ ያሳዝናል፤ ያስቆጫል፡፡ ይሁን እንጂ ህዝብ በእንዲህ ዓይነት ማታለያ የመብት ጥያቄውን አሳልፎ አይሰጥም፣የወያኔ ጉድም አያልቅም፡፡Yidenkachew Kebede

ግንቦት 7 – ታሪካዊ ቀን



በክፍሉ ታደሰ -(ግንቦት 7 /ኢትዮጵያ፤ እኮ ለምን? እንዴት?/ ከሚለው መጽሐፍ የተቀነጨበ)
ginbot-7--
በግንቦት 7/1997 ምርጫ 524 የምክርቤት ወንበሮች ለምክር ቤት ቀረቡ፡፡ 23 የሚሆኑት በነሐሴ ወር በሱማሌ ክልል ለሚደረገው ምርጫ ወደጎን ተተዉ፡፡
ግንቦት 7 በተካሄደው ምርጫ ተሳትፌያለሁ፡፡ ማን ይናገር የነበረ፤ ማን ያርዳ የቀበረ እንደሚባለው ያየሁትን፣ የሰማሁትን፣ የተሳተፍኩበትን ነው የማቀርበው፡፡ እኔ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ በሦስተኛ ሰው አድርጌ ታሪኩን ላቀርበው ሞክሬ፤ ራቀብኝ፣ ባዕድ ሆነብኝ፣ የኔ መስሎ አልሰማህ አለኝ፡፡ እናም ታሪኩን በቀጥታ ለመተረክ ወሰንኩ፡፡
ግንቦት 7/1997 ከጠዋቱ 12 ሰዓት ከቤቴ ወጥቼ ወደምርጫጣቢያ አመራሁ፡፡ ከምኖርበት ሰፈር ወደምመርጥበት ጣቢያ ለመሄድ ከ15 እስከ 20 ኪ.ሜ. መንዳት ነበረብኝ፡፡ በጠዋት የተነሳሁትም አንድም ቀደም ብዬ ከመረጥኩ በኋላ ከተማውን ተዘዋውሬ ለማየት እንዲረዳኝ በማሰብ ነበር፡፡ ዘጠኝ ኪሜ ያህል ተጉዤ መገናኛ አካባቢ ስደርስ ከአንድ የምርጫ ጣቢያ ፊትለፊት ረዥም ሰልፍ አየሁ፡፡ መኪናዬን ትንሽ ቆም አድርጌ ሰልፉ ምን ያህል ረዥም እደሆነ ለመቃኘት ሞከርኩ፡፡ ሰልፉ እየተጠማዘዘ ቢያንስ 300 ሜትር የሚያክል ቦታ ይዟል፡፡ የተሰለፈውን የሰው ዓይነት ለማየትም ሞከርኩ ዝንቅ ነበር፡፡ ወንድ/ሴት፣ ትልቅ/ትንሽ፣ ወጣት/አዛውንት ሁሉም በትዕግስት ተሰልፈው ይጠብቃሉ፡፡ እንዴት በጥዋት ሊነሱ ቻሉ ብዬ እያሰብኩ መንገዴን ቀጠልኩ፡፡ መገናኛ አደባባዩጋ ስደርስ ወደሰሜን አቅጣጫ ወደሚወስደው መንገድ ወደቀኝ ታጠፍኩ፡፡ ወደ እንግሊዝ ኤምባሲ ወደሚወስደው መንገድ፣ በድሮው አጠራር ወይዝሮል ወደሚባለው መንገድ ወደሚያስገባው አደባባይ ደርሼ ወደግራ ታጠፍኩ፡፡ ከዚህ ቦታ ጀምሮ ምርጫ የማደርግበት ሰፈር እስከምደርስ ድረስ ስድስት ወይም ሰባት የምርጫ ጣቢያዎች አየሁ፡፡ ሁሉም ቦታዎች እጅግ በጣም በርካታ ሰዎች ተሰልፈው በትዕግስት ይጠባበቃሉ፡፡ እንደዕንቁ ጠብቀው ያቆዩት የምርጫ ካርዳቸውን ከሳጥናቸው ለመጨመር በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡
መጀመሪያ እንዳየሁት የምርጫ ጣቢያው ሁሉ ሌሎች ቦታዎችም የተሰለፉት ዓይነት ተመሳሳ ነበር፡፡ ሰው በምርጫው ለመሳተፍ የነበረው ፍላጎት አስገረመኝ፡፡ ረዥም ዘመን በፖለቲካ ትግል ውስጥ ብቆይም ይህን የመሰለ አጋጣሚ አይቼ አላውቅም ነበርና ጥቂት ወራት ወደኋላ ተመልሼ የነበረውን ሁኔታ ለማስታወስ ሞከርኩ፡፡ ምርጫው ሲታወጅ ለመንግሥትም ሆነ ለተቃዋሚ ድርጅቶች አሳሳቢው የነበረው ሒደት ሰው በፖለቲካ ሒደቱ ለመሳተፍ ፍላጎት እያጣ በመሄዱና ተስፋ በመቁረጡ ለምርጫው መመዝገብ ብዙም ፍላጎት ያልነበረው መሆኑ ነበር፡፡ በዚህ የመጀመሪያ ወቅት የመንግሥት፣ የሲቪል ድርጅቶችም ሆነ የተቃዋሚዎቹ ዋና ሥራ ሰው እንዲመዘገብ መቀስቀስና መወትወት ነበር፡፡ በብዙኃን መገናኛ እና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሰፊ ቅስቀሳ ሲካሄድ ቆየ፡፡ በቂ ሰው ሊመዘገብ ባለመቻሉ፣ የምዝገባው ጊዜ ሊራዘም ችሏል፡፡
የምርጫው ሒደት ከተጀመረበት መስከረም 1997 ጀምሮ ምዝገባው እስከተገባደደበት እስከ የካቲት 6 ድረስ የሁሉም ተቋማት ርብርብ በምርጫ ምዝገባው ላይ መሆኑ ያለምክንያት አልነበረም፡፡ ሌላ ቦታ እንደተጠቀሰው በኢሕአዴግ ዘመን ከ1997 በፊት ብቻ ወደ ስምንት የሚጠጉ ብሔራዊ እና ክልላዊ ምርጫዎች ተካሂደዋል፡፡ ሕዝቡ ምረጥ እየተባለ በምርጫዎቹ ተሳትፏል፡፡ ከምርጫዎቹ በኋላ ለውጥ ሲመጣ አላየም፡፡ እናም ለምርጫ ለምን እንደሚቧግት ሊገባው አልቻለም፡፡ ምን አደከመኝ ለውጥ ላይመጣ እያለ ተስፋ እየቆረጠ ሄዷል፡፡ ምርጫ ከንቱ ድካም እንደሆነ ተረድቶ ካልተገደደ በቀር ለመሳተፍ ፍላጎት አልነበረውመ፡፡ ሕዝቡ ፈለገም አልፈለገ፣ ወደደም ጠላ መረጠም አልመረጠ ውጤቱ ገና ከወዲሁ ስለሚታወቅ አብዛኛው ሰው ምን አታከተኝ ብሎ ላለመሳተፍ ድምዳሜ ላይ ደርሷል፡፡ ገዢው ፓርቲ ሁልጊዜም አሸንፌያለሁ እንደሚል ይረዳል፡፡ ገዢው ፓርቲ በሕዝቡ ቡራኬ የሥልጣን ዘመኔን አራዝሜያለሁ እንደሚል፣ ቀደም ሲል ጀምሮ ያውቀዋል፡፡ ሕዝቡ ይህንን ቡራኬ ለምን መስጠት እንዳለበት፣ ለምንስ ጉልበቱንና ጊዜውን እንደሚያባክን አልገባህ ስላለው ምርጫን የመድረክ ተውኔት አድርጎ ራሱን ማግለል እንዳለበት ወስኖ ቆይቷል፡፡
ለ1997 ምርጫ መንግሥትና የመንግሥት ደጋፊዎች ብቻ ሕዝቡን ለምርጫ እንዲሳተፍ ቢጠይቁት ኖሮ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ጥሪያቸውን ባልተቀበለ ነበር፡፡ ይሁንና ጥሪውን ከተቃዋሚዎችም አንደበት በመስማቱ ተመዘገበ፤ ለማንኛውም ካርዱን ልያዝ የሚሆነውን አያለሁ አለ፡፡ ወደኋላ ላይ እንደምናየው የምርጫ ውድድሩ መልክ እየያዘና እውነተኛ ፉክክር እየታየበት ሲሄድ ካርድ ያላወጡ ብዙ ሰዎች ለማውጣት ወሰኑ፡፡ ይህ የሚሆነው ከየካቲት 1997 በፊት ባለው ጊዜ ሲሆን ከዚያ በኋላ በነበረው ሒደት የተቃዋሚዎችና የገዢው ፓርቲ ክርክር ብዙዎችን ቢማርክም ጊዜው በማለፉ የምርጫ ካርድ ለማውጣት ቢፈልጉም ሊሆንላቸው አልቻለም፡፡ ካርድ ባለማውጣታቸው የተፀፀቱ በርካታ ናቸው፡፡
ወደምርጫ ሒደቱ መለስ ልበልና ምርጫ የማካሄድበት ሰፈር ደርሼ ሰልፍ ያዝኩ ተራዬ እስከሚደርስ ባልሳሳት ሦስት ሰዓት ያክል ተሰለፍኩ፡፡ ቆይታዬን አልጠላሁትም፡፡ ብዙ እንድታዘብ ረዳኝ፡፡ የሕዝቡ አንድ አካል መሆኔ ተሰማኝ፡፡
የምርጫ ካርዴን ለማስገባት ተሰልፌ በነበረበት ወቅት ከኋላዬ ተሰልፈው የነበሩ አንዲት ሴት ደግመው ደጋግመው ይናገሩት የነበረው ነገር አስገረመኝ፡፡ ስለምርው ሥነስርዓት፣ ፎርሙ እንዴት መሞላት እንዳለበት፣ ምልክት እንዴት እንደሚደረግ፣ ፎርሙ እንዴት እንደሚተጣጠፍ፣ ወዘተ ቀበሌውን ወክላ አንዲት ሴት ታስረዳለች፡፡ ስለምርጫው ከማስረዳት በስተቀር ምንም የምታደርገው ነገር አልነበረም፡፡ ሴትየዋ የጠራ አማርኛ አትናገርም፡፡ አፏን ያዝ ያደርጋታል፡፡ ይህች ሴት ከቀበሌው ውስጥ ምን ሥልጣን እንዳላት አላውቅም፡፡ ከሌላ ቦታ የመጣች ትሁን አትሁንም ምንም የማውቀው ነገር የለም፡፡ ከኋላዬ የተሰለፉ አንዲት ሴትዮም ይወቋት/አይወቋትም አላውቅም፡፡ ብቻ ያስገረመኝ ሴትየዋ በተናገረች ቁጥር ‹‹ሰላቢ›› ይላሉ፡፡ አንዲት ቃል ናት የሚተነፍሷት፡፡ ‹‹ሰላቢ››፡፡ ዞር ብዬ ሴትየዋን አየኋቸው፡፡ ደርበብ ያሉ የቤት እመቤት ናቸው፡፡ ለምን ሴትየዋን እንደጠሏት ልረዳ አልቻልኩም፡፡ የግል ፀብ ይኑራቸው አይኑራቸው፣ ወይም ሌላ ምክንያት እንዳላቸው የማውቀው ነገር የለም፡፡ ምን በደለችዎት እና ነው የሚሰድቧት ብዬ ለመጠየቅ ዳዳኝ፡፡ አንተስ ማነህ፣ ምናገባህ ቢሉኝ አልኩ፡፡ ብቻ ድፍረት አጣሁና ጥያቄዬን ውጬ ቀረሁ፤ በጉዳዩ ላይ ትንሽ አብሰለሰልሁ፡፡
ምርጫ ያደረግኩበት ሰፈር ውስጥ አብዛኛው ነዋሪ የአማርኛ ተናጋሪ ሲሆኑ፣ በንግድ ሥራ የተሰማሩ በርከት ያሉ ጉራጌዎች አሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ፣ ከሰፈሩ ትንሽ ከፍ ብሎ በሸማ ሥራ የሚተዳደሩ ጋሞዎች ይገኛሉ፡፡ ሁኔታው ይህ ሆኖ ሳለ የቀበሌው ሊቀመንበር ትግርኛ ተናጋሪ ናቸው፡፡፡ ምናልባትም የሕወሓት አባል ይሆናሉ፡፡ ስለሌሎቹ የቀበሌው ባለሥልጣናት ምንም የማውቀው ነገር የለም፡፡ እነዚህ ሐሳቦች በአእምሮዬ ላይ ብልጭ አሉ፡፡ ከሴትዬዋ ድርጊት ጋርም ላዛምዳቸው ሞከርኩ፡፡ ጉዳዩ የትም ሊወስደኝ የማይችል ስለሆነ ብዙም አልቆየሁበትም፡፡ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ማተኮር ጀመርኩ፡፡
በምርጫ በተሰለፍኩበት በዚህ ወቅት ብዙ ነገሮችን ታዘብኩ ተማርኩ፡፡ ሲፈልግ ሕዝቡ ሥነስርዓት ከሚገባው በላ ያከብራል፡፡ እያንዳንዱ ሰው ምርጫው የግሉ አድርጎ ስለወሰደ እንዳይበላሽ ከመንገዱ ወጣ ብሎም እንኳን ሊያስተካክል ይሞክራል፡፡ ሰው ለምርጫ ሳይሆን ለሠርግ ወይም ለሌላ ዓመት በዓል የተጠራ ነበር የሚመስለው፤ ደስተኛ ነበር፡፡ ወጣቶቹም ያ ያልተፈጠረባቸውን ትዕግስት ከየት እንዳገኙት አላውቅም በጨዋነት ተራቸውን ይጠባበቃሉ፡፡ ብዙ እናቶች ተሰልፈዋል፡፡ እጃቸው ባዶ ነው፡፡ ካርዳቸውን አልያዙም እንዴ ብዬ ሳስብ፣ አንዳንዶቹ ከጡታቸው ስር እየመዘዙ ሲያወጡ አየሁ፡፡ ለካርዳቸው የሰጡት ዋጋ ከፍ ያለ መሆኑ አስገረመኝ፡፡ አዛውንቱ ይህንን ያለምክንያት አልነበረም፡፡ የተቃዋሚዎች ክርክር እየበረታ ሲሄድ ኢሕአዴግ ካርዶች እየገዛ ነው ተብሎ በከተማው ስለተወራ አዛዋንቱ ለጥንቃቄው ያህል ያደረጉት ይሆናል ብዬ ገመትኩ፡፡
ከወለደች 15 ቀናት ብቻ ያስቆጠረች አራስ ልትመርጥ መጣች፤ ታመን ከመጣንበት ተነስተን መጣን የሚሉ በሽተኞች፣ መሄድ ያቃታቸው ሽማግሌዎች፣ ወዘተ ሲመርጡ ማየት አስገራሚ ነበር፡፡ ከምርጫው በፊት በሥራ ጉዳይ ከሀገር መውጣት ነበረብኝ፡፡ ይሁንና በሕይወቴ የመጀመሪያ በሆነው በዚህ ምርጫ መሳተፍ አለብኝ ብዬ መወሰኔ አስደሰተኝ፡፡ ለረዥም ዘመን ጠፍቶብኝ የነበረው ደስታ ተመልሶ ወደሰውነቴ ሲገባ ታወቀኝ፡፡ በምንም ዓይነት ሁኔታ ላገኘውና በቃላት ልገልጸው የማልችለውን ስሜት አገኘሁ፡፡ ይህ ስሜት ምን እንደሚመስል ማወቅ በራሱ ፀጋ ነው ብዬ አልኩ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለብዙ ዘመናት የታገለለት መብቱ ሊከበር ይሆን ብዬ እጅግ ደስ አለኝ፡፡ እኔ ያየሁትን እና የሰማሁትን ከጎኔ ያየሁትንና የሰሙትን ከ30 ዓመት በፊት ከጎኔ የነበሩ ጓደኞቼ ምነው በነበሩ ብዬ ተፀፀትኩ፡፡ የወደቁለት ዓላማቸው መሳካቱን ምነው ባዩ  ብዬ አሰብኩ፡፡ በዚህ መሐል ጄኔራል መንግሥቱ ነዋይ ለፍርድ ቀርበው የሞት ፍርድ ሲፈረድባቸው ተናገሩ የተባለው ቃል ትዝ አለኝ፡፡ ‹የዘራችሁት ፍሬ ማሸት ጀምሯል›  ብለው ያሉት፡፡
ሕዝቡ እጅግ ሰላማዊ ከመሆኑ የተነሳ ለጥበቃ የተመደቡት ፖሊሶች ደከማቸው መሰለኝ ቁጭ አሉ፡፡ ወደሰልፈኛው ብዙም ትኩረት አያደርጉም ነበር፡፡ ብቻ አልፎ አልፎ አንዳንድ ወጣቶች ሰልፍ ጥሰው ወደፊት ሲሄዱ በዓይናቸው ይከታተሏቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ከቤተሰቦቻቸውጋ ከተወያዩ በኋላ ወደነበሩበት ይመለሳሉ፡፡ ሥራዬ ብዬ ወጣቶቹን ስከታተል ያልተማሩ እናቶቻቸውን እንዴት መምረጥ እንዳለባቸው ለማሳሰብና ለማስረዳት ነበር የሚመጡት፡፡ ወጣቶቹ ሥራቸውን ካከናወኑ በኋላ ምልስ ይላሉ፡፡ ወጣቶቹ ለቤተሰባቸው የማስረዳት ኃላፊነት ሊወስዱ የቻሉት በምርጫው ወቅት ገዢው ፓርቲ ያልተማሩ ሰዎችን ሊያጭበረብር ይችላልና ጥንቃቄ አድርጉ የሚል ማስታወቂያ ለተቃዋሚ ኃይሉ በተደጋጋሚ ስለተሰጠ ሊሆን ይችላል፡፡
ግንቦት 7/1997 -  25,605,851 የሚሆን ሕዝብ በመራጭነት እጅግ በርካታ የሚሆን ደግሞ በተባባሪነትና በደጋፊነት ሲፍነቀነቅ ዋለ፡፡ ግንቦት ሰባት አንድ ነገር ይዛ ትመጣ ይመስል ሰው ደስታ በደስታ ሆነ፡፡ ሕዝቡ ግንቦት ሰባት የነገ ብርሃንን አብሳሪና በጫንቃው ተሸክሞ ከሚዞረው ችግር የምታላቅቀው ቀን አድርጎ ነበር የተመለከታት፡፡ በጥቅሉ ግንቦት ሰባት በሚሊዮኖች የሚቆጠር የኢትዮጵያ ሕዝብ የሠርግ ታዳሚ ሆኖ የዋለበት ቀን ነበር ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡
ግንቦት 7 በቁምነገሯ ብቻ ሳይሆን ብዙ ገጠመኞችና ቀልዶች የተስተዋሉባት ቀንም ነበረች፡፡ ብዙዎቹ ገጠመኞች ስለምርጫው ሥነስርዓት ኅብረተሰቡ በተለይም በዕድሜ የገፉ ሰዎች ያላቸው ግንዛቤ ዝቅ ያለ በመሆኑ ምክንያት የተፈጠሩ ናቸው፡፡ እነዚህ ገጠመኞች አንድ ሰሞን አነጋጋሪ በመሆናቸው በግል ጋዜጦች ጭምር ሲወጡ ከርመዋል፡፡ በየትኛው ጋዜጣ ላይ እንደሆነ አላስታውስም፡፡ አንድ አዛውንት ሰልፈኛ ወደቆመበት ይሄዱና ‹‹የቅንጅት ሰልፍ የትኛው ነው?›› ብለው ይጠይቃሉ፡፡ ሁሉም ሰው አንድ ቦታ ነበርና የተሰለፈው ሰው ሳቀ፤ አዛውንቷ በየዋሕነት ወይም ባለማወቅ ማንን ሊመርጡ እንዳሰቡ አሳወቁ፡፡ ሰውን ያሳቀው ይህ የአዛውንቷ የዋሕነት ነበር፡፡ በአንድ ቀበሌ ውስጥ ስለተፈፀመ አንድ ሁኔታ ሰው ሲያጫውተኝ አዛውንቷ ፎርሙ የሚሞላበት ክፍል ውስጥ ብቻቸውን ከቆዩ በኋላ ከዚያ ወጥተው ሳጥኑ ወዳለበት ክፍል ይሄዳሉ፡፡ ዞር ዞር ብለው ሲመለከቱ አንድ ሳጥን ብቻ ነው የተቀመጠው፡፡ አንድ ሳጥን ብቻ ነው የተቀመጠው፡፡ አካባቢያቸውን ቢቀኙም ሌላ ሳጥን ሊያዩ አልቻሉም፡፡ ወደአስተባባሪዎቹ ዘወር ብለው ‹‹የቅንጅት ሳጥን የትኛው ነው?›› ይላሉ፡፡ ሰዎቹ ግራ ተጋብተው ዝም ብለው ‹‹እሱ ሳጥን ውስጥ ይጨምሩ›› ይሏቸዋል፤ ሴትየዋ ይናደዳሉ፡፡ ደግመው ‹‹የቅንጅትን ነው እኮ ያልኩህ!›› ይላሉ ወደአንደኛው ዘወር ብለው፣ ሰውዬው መልስ ቢሰጣቸውም ሊያምኑት አልቻሉም፤ ተቆጡ፡፡ ተናገሩት፡፡ ኋላ ላይ ሌሎች ባለሥልጣናት እና የተሰለፈው ሕዝብ ካረጋጋቸው በኋላ ካርዳቸውን ሳጥን ውስጥ ከትተው ሄዱ፡፡
ከላይ የዘረዘርኩት የእኔ ገጠመኝ እና በአንድ የምርጫ ቀጠና የታዘብኩት የሕዝቡ ተሳትፎ በመላ ሀገሪቱ ሁሉ ተፈፅሟል፡፡ የሕዝቡ ትዕግስት ድንበር አልነበረውም፡፡ በአብዛኛዎቹ የምርጫ ጣቢያዎች ችግር ያልነበረ ሲሆን ችግር የተፈጠረባቸው አንዳንድ ቦታዎችም አልጠፉም፡፡ አቶ ኃይሉ ሻወል ‹‹የአዲስ አበባ ምርጫ እየተጭበረበረ ነው›› በማለት ሒደቱ ሳይጠናቀቅ መግለጫ ቢሰጡም ምርጫ ከሞላ ጎደል በጥሩ ሁኔታ ነበር የተጠናቀቀው፡፡ ከዚህ ውጪ ግን ‹‹ከበድ ያሉ ሕገወጥ አሠራሮች የታዩት በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ሲሆን መታወቂያ ያለማየትና ለምርጫ ያልደረሱ ወጣቶች ሲመርጡ ተስተውለዋል፡፡›› ይላል በታዛቢነት የተሳተፈው የካርተር ማዕከል፡፡ እንደካርተር ማዕከል በምርጫ ቀንም ሆነ ከዚያ በኋላ የማስፈራራት እና የማስደንገጥ እርምጃዎች ተወስደዋል፡፡ የምርጫ ሳጥኖች ያለአግባቡ ከቦታቸው ተነስተዋል፤ ወይም ዋስትና ባለው መንገድ አልተቆለፉም፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች በምርጫ ጣቢያዎች እንዳይገኙ ወይም በቆጠራው ላይ እንዳይኖሩ ተደርጓል፡፡
በአጠቃላይ የግንቦት 7/1997 ሕብረ-ብሔራዊ ምርጫ በኢሕአዴግ የ14 ዓመት አገዛዝ እና ይከተላቸው በነበራቸው ፖሊሲዎች ላይ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ሕዝበ ውሳኔ ያደረጉበት፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ያደረጉበት እውነተኛ ምርጫ ነበር፡፡

የ“ቀዩ መስመር” ሰላባዎች?


የ"ማበስበሱ" ቁማርና የደኅንነቱ ሚና!!

red-tape2


መለስ ህይወታቸው እንዳለፈ ከተሰጡት አስተያየቶችና ትንቢቶች መካከል ቀዳሚው የመለስ ሞት ለህወሃት ጊዜውን ጠብቆ የሚፈነዳ ፈንጂ መሆኑ ነበር። በዚሁ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በስልጣን ላይ ያሉ የኢህአዴግ ዲፕሎማት “መለስ የቆፈሩት ጉድጓድ” በሚል ርዕስ በሰጡት ቃለ ምልልስ ይህ እንደሚከሰት ቁልጭ አድርገው ተናግረው ነበር።
መለስ አፍነው የያዟቸው የፖለቲካ ችግሮች ጊዜያቸውን እየጠበቁ የሚፈነዱና በመጨረሻም ፓርቲውን እንደሚፈረካክሰው የተገለጸው በየደረጃ የሚፈነዱት ችግሮች እየበረከቱ በመሄዳቸው ነበር። መለስ አፍነው የያዟቸው ችግሮች የእርስ በርስ መበላላት ደረጃ እንደሚያደርሱ በርካታ ወገኖችና መገናኛዎች ጎልጉልን ጨምሮ አመላክተዋል። አሁን አሁን ትንቢቱ የፍጻሜው ጅማሬ ላይ እንደሚገኝ የሚናገሩም አሉ።
የፖለቲካ አቋም ልዩነት ሳይኖር የአስተሳሰብ ልዩነት ማራመድ በህወሃት ዘንድ አይቻልም። ከተሞከረም ክህደት ነው፤ መፈንቅለ መንግስት የማካሄድ ያህል ነው። የርዕዮተ ዓለም ለውጥ የማቀጣጠል ያህል ያስፈርጃል። ሽብርተኛ ያስብላል። ከቶውንም ተቀባይነት ስለሌለው ድንበር ተበጅቶለታል። ድንበሩም “ቀይ መስመር” በመባል ይታወቃል። የ”ቀይ መስመር” ሃሳብ አመንጪና ደራሲ አቶ መለስ ናቸው። “በጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ” በሚል የምጸት ስም የሚጠሩት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝም ይህንን የቀይ መስመር ጽንሰ ሃሳብ ለንግግር ያህል ይጠቀሙበታል።
haile and girma
ቀይ መስመር የሚሰመርበት በውል ተለይቶ የተቀመጠ ውስን ጊዜ የለውም። መስመሩ ሁሌም አለ። ሁሉም ቆመውበታል። ከልምድ እንደሚታየው በህወሃት ህመም ኢህአዴግ ሲያተኩሰው በድንገት መስመሩ በደማቁ እንዲቀባ ይደረጋል። መስመሩ የሚቀባበት ደማቅ ቀለም የሚቀዳው አቶ መለስ አፈር ሳይልሱ “በስብሰናል” ሲሉ ከሰየሙት የኢህአዴግ የ”ማበስበሻ” ባህር ውስጥ ነው።
በኢህአዴግ የ”ማበስበሻ” ባህር ውስጥ ያልተነከረ የለም። በዚህ ባህር ውስጥ ሆነው የሚንቦጫረቁት ተቆጥረው አይሰፈሩም። አዲስ አበባ በአራቱም ማዕዘን፣ በክልልና በክልል ዋና ዋና ከተሞች፣ እንዲሁም በተለያዩ አገራት የሚሰነፍጠው የባህሩ “ግልማት” የዜጎችን የመኖር ህልውና ከተፈታተነ ቆይቷል።
በባህሩ ውስጥ በመርከብ ሆነው በጀልባ የሚቀዝፉትን የሚመለከቱ አሉ። ጀልባ የሚቀዝፉት ጌቶቻቸውንና “ልዕልቷን” እያዩ ሽታውን በለመዱት ባህር ውስጥ ይምነሸነሻሉ። በዛው ባህር ውስጥ በደረታቸው እየዋኙና እየተንቦጫረቁ ግብር የሚያስገቡ አሉ። “ዲጂታል” የሚባሉትና “ምስለኔዎቹ” ደሞ የማበስበሻውን “መረቅ የማቅለሚያ ማዕድን” ይዘው አራት ኪሎ የባህሩ አናትና ማማ ላይ ሆነው ሁሉንም ይመራሉ። የባህሩን የመጫወቻ ህግ የሚበላቸውና ከበሰበሰው ባህር ወደ እቶን የሚወረወሩት “የቀይ መስመር ሰለባዎች ” ይለያሉ። ለይተው ሲጨርሱ ለባህሩ ካፒቴን የፌዴራል የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ያቀብሉታል። በዚሁ ሂደት ይቀጥላል። አዲስ ነገር የለም። ሊኖርም አይችልም። ይህ መነሻ ነው። ወደ ጉዳዩ እናምራ።
የሰሞኑ ወግ – ኢህአዴግ አመረረ ወይስ ቀለደ?
ሰሞኑን ኢህአዴግ “ሙስና ላይ ዘመትኩ። በህዝብ ጥቆማና ትብበር ሙስና የተንሰራፋበትን ተቋም አበራየሁት። የህዝብ ትብብር አይለየኝ …” በማለት የፍርድ ቤት አሰራርና ህጋዊ የፍርድ አካሄድ እያስኮመኮመ የሚያውጀው አዋጅ ያስገረማቸው ክፍሎች “እንዴት እንመን? እንዴት እንቀበል? ማን ያልተነካካ አለ?” እያሉ ነው። ከተለያዩ አቅጣጫ “ኢህአዴግ አመረረ ወይስ ቀለደ” በሚል ክርክርም እያስነሳ ነው።
የፌዴራል ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አሊ ሱሌማን ፓርላማ ቀርበው “ጥናቱ የተጀመረው በአቶ መለስ ትዕዛዝ ከዓመት ከአስር ወር በፊት ነበር” በማለት ምስክርነታቸውን የሰጡበት ዘመቻ አቶ መለስ በህይወት እያሉ ያልተጠናቀቀው በድንገት በመታመማቸው፣ ከዛም በመሞታቸው፣ ከዛም በላይ የሽግግር ወቅት በመሆኑ እንደሆነ አስረድተዋል። መለስ ሲሞቱ ሃይለማርያም ሙስና ላይ ዘመቱ በሚል ስባሪ ታሪክ እንዳያተርፉ፣ ከዚያም አልፎ ዘመቻው የፖለቲካ ልዩነቱ የፈጠረው “የአራግፍ፣ የመንጥር ዘመቻ” እንዳይመስል አቶ አሊ መለስን የዘመቻው “አባትና ባለታሪክ” አድርገው እንዲያቀርቡ መታዘዛቸው ዘመቻው የተለመደው የኢህአዴግ ቀልድ እንደሆነ አመላካች ስለመሆኑ በስፋት አስተያየት የሚሰነዘርበት ጉዳይ ነው።
ምንም ሆነ ምንም ኢህአዴግ ለጀመረው የሙስና ዘመቻ ሊመሰገን ይገባዋል የሚሉ ወገኖች ዘመቻው እንደ ሰደድ እሳት ተያይዞ የሚነድ ስለመሆኑ ሲናገሩ ይሰማል። የኢህአዴግ ደቀ መዝሙር በመሆን የሚታወቁ ድርጅታቸው “የመለስ ቦናፓርቲ” የተሃድሶ ዘመን ተመልሶ እንደመጣ፣ የዚህ ተሃድሶ ፊት አውራሪ ደግሞ እጩ ጠ/ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል እንደሆኑ በኩራት እየተናገሩ ነው።
ከደህንነቱ ራዳር የተሰወረ አለ?
በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የማናቸውም ባለሃብቶችና ባለስልጣናት እለታዊና አጠቃላይ የክትትል መረጃ ተመዝግቦ የተቀመጠ ነው። ዋናው ደህንነት የማበስበሻው ባህር ቁልፍ እጁ ላይ ነው። ሲፈለግ ከዋናው ባህር መዝገብ የሚፈልጋቸው ነቅሶ በስሩ ላላው የኢኮኖሚ ደህንነት ዘርፍ ያቀብላል። ለስራው ቅርብ የነበሩና በቅርቡ አገር ለቀው ናይሮቢ የሚገኙ እንዳሉት በዚሁ አሰራር መሰረት አሁን የታሰሩት ሰዎች ሪፖርት ተጠናቆ የቀረበው የዛሬ አምስት ወር ግድም ነው።
ደህንነቱ ማን ከማን ጋር እንደሚሰራ፣ የትኞቹ ባለስልጣናት ከየትኛው “ባለሃብት” ጋር አብረው እንደሚሰሩ፣ በየትኛው ወገኖቻቸውና ዘመዶቻቸው ስም እንደሚነግዱ፣ የኤክስፖርትና ኢምፖርት ስራ እንደሚሰሩ፣ ያለ ማስያዣ ብድር እንደሚፈቅዱና እንዲፈቀድ መመሪያ የሚሰጡ፣ ወዘተ ሙሉ መረጃ እንዳለው የሚጠቁሙት እኚሁ ሰው “ሙስና ከግል፣ ከድርጅትና ከተቋማት አልፎ በመንግስት ደረጃ የተዘረጋ ነውና ማን ማንን ይወነጅላል?” የሚል ጥያቄ ያነሳሉ። አያይዘውም “አገራችን ውስጥ ሙስና በግለሰብ ደረጃ ሳይሆን በመንግስት ደረጃ የተቋቋመ ነው” ብለዋል።
ሌሎችም እንደሚሉት ሙስናው ሊደበቅ በማይችል ደረጃ አገሪቱን እንደ ወባ ወረርሽኝ ሲያጥለቀልቃት፣ በየአቅጣጫው ሙስናና የመልካም አስተዳደር ችግር ህዝብን ሲያንገሸግሸው ለምን ዝምታ ተመረጠ? የሚለው አንኳር ጉዳይ ብዙ ከመላምትነት የዘለሉ ምክንያቶች እየቀረቡበት ነው። በተለያዩ ደረጃ የኢህአዴግን የመበስበስና የእድገት ደረጃ የማሟጠጥ ጉዳይ አንተርሰው አስተያየት የሚሰጡ ቅድሚያ አጀንዳ የሚያደርጓቸው አቶ መለስን ነው።
መለስ ዝምታን ለምን መረጡ?
እርሳቸው ምን ያህል ተዋናይ እንደሆኑ አሃዝ ጠቅሶ መናገር ባይቻልም አቶ መለስ አገሪቱ በሙስና መንቀዟን እያወቁ ዝም ማለታቸው ከተባባሪነት እንደማያሸሻቸው ስምምነት አለ። በፓርላማ፤ ከነጋዴዎችና ከኢንቨስትመንት ማህበረሰብ ጋርና ከተለያዩ አካላት ጋር ሲነጋገሩ ሙስናን አስመልክቶ አስገራሚ ዲስኩር ሲያሰሙ ኖረው ያለፉት አቶ መለስ፣ ሙስናን ተሸክመው የኖሩት በፍርሃቻ እንደሆነ የአብዛኞች ማጠቃለያ ነው። አቶ መለስ ሙስናን እንደ ስልት በመጠቀም በዙሪያቸው ያሉትን “በማበስበስ” እንዳሻቸው ይነዱዋቸዋል።
በሙስና የተጨማለቁና በሙስናው ባህር ውስጥ የሚዋኙትን ባለስልጣናት፣ ካድሬዎች፣ ባለሃብቶች፣ የጊዜው ሰዎችና ዘመዶቻቸው ቢታወቁም አቶ መለስ በመፈክር አብረዋቸው ለመኖር የወሰኑትና በዚያው ይህችን ዓለም ባላሰቡበት መንገድ የተለዩት በጡረታና “ያለህን ብላ” በሚል አካባቢያቸውን ለማጽዳት የሞከሩት ሙስናው ውስን አድራሻና መንደር ስለሌለው ነው። ዛሬ ምን አዲስ ነገር ተገኘና መለስ የፈሩት ሙስና እንዴት ተደፈረ?
መለስ በህይወት እያሉ ሙስናውን ዝም አሉ የሚሉትን ክፍሎች አጥብቀው የሚቃወሙ ቡድኖች ደግሞ “አቶ መለስ የሙስናው አውራ ናቸው። በመንግስት ደረጃ ለተገነባው የሙስና መንደር ፊታውራሪና ይለፍ ሰጪ ናቸው” ሲሉ ይከራከራሉ። የሙስናውን አዝመራ የዘሩ፣ ኮትኩተው ያለመለሙት፣ መጨረሻ ላይም ባህር አዘጋጅተው የማበስበሻ አረንቋ የተከሉት አቶ መለስ በመሆናቸው ርምጃ ለመውሰድ እንደማይቻላቸው፣ ርምጃ ልውሰድ ቢሉም ሁሉም ስለተበከሉ “በአገሪቱ የጦር አዛዥ፣ የፖሊስ አለቃ፣ የደህንነት ሹም፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት፣ ፓርላማ፣ ቀበሌ፣ ክፍለ ከተማ፣ ከንቲባ፣ መሃንዲስ፣ ሆስፒታል … የሚቀር ስለማይኖር በቅድሚያ በአገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊታወጅ ይገባል” ሲሉ የሙስናውን አደገኛነትና መንግስታዊ መዋቅር ያለው ስለመሆኑ ይከራከራሉ።
ለማስረጃ ከሚያነሱት መከራከሪያ መካከል “ዋናው የሙስና ሻርክ” በሚል ስያሜ የሚጠሩት ባለሃብትና በሳቸው መዋቅር ውስጥ ሆነው ከተራ ወንጀል እስከ አገር አቀፍና ድንበር ዘለል ዝርፊያ የሚፈጽሙ “ማፍያዎች”፣ በፌስታል ብር የሚያቀባብሉ ምስለኔዎች፣ የባለስልጣናትን ሚስቶችና ዘመዶች በንግድ ተቋሞቻቸው በመሰግሰግ የአገሪቱን ህግና ህገመንግስት እንዳሻቸው የሚጋልቡ  ማጅራት መቺዎች፣ የአገሪቱን ባንኮችና የንግድ ስርዓት በማዛባት ሰርተው የሚበሉ ዜጎችን አሟምተው የጨረሱ፣ የራሳቸው ፖሊስና የደኅንነት ሃይል በመገንባት እንደ መንግስት ያቆጠቆጡ ወዘተ በህዝብ ይታወቃሉ። እኒህ ክፍሎች የአቶ መለስን ኮሪዶርና ማረፊያ ቤት ሲመላለሱበት መለስ ዝም ማለታቸው ከምን የመነጨ ሊሆን ይችላል? የሚል ጥያቄ ለሚያነሱ መልሱ አንድ ነው። እሳቸውም፣ ባለቤታቸውም፣ ዘመዶቻቸውም፣ ወገኖቻቸውም፣ የትልቁ “የማበስበሻው ባህር” አባል በመሆናቸው ነው። ከዚያም በላይ ደግሞ ልንካው ካሉ የመገንደስ አደጋ ስለሚከተል ነው። በሌላ አነጋገር ከስር እስከ አናት በተለያየ ደረጃ በህገወጥ የበለጸጉና የትንንሽ መንግስታት መሪዎች የሆኑ ስለበዙ አቶ መለስም ሆኑ እሳቸው የሚመሩት ህወሃት መራሹ አስተዳደር የመከልበስ አደጋ እንዳያጋጥመው በመፍራት እንደሆነ ከውስጥም ከውጪም በስፋት የሚታመንበት እውነታ ነው።
ደብረጽዮን “የጎበዝ አለቃ”!!
መለስ ሲያልፉ ሃላፊነቱን ጠቅልለው የተረከቡት መለስ በመተካካት ሰበብ ያዘጋጇቸው ሰዎች ናቸው። ከነዚህ አዲስ አመራሮች መካከል ዶ/ር ደብረጽዮን ዋናው መሃንዲስ ናቸው። መለስ የፈሩትን ጉድ እሳቸው እንዴት ደፈሩት ለሚለው የሰሞኑ ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ክፍሎች ዶ/ር ደብረጽዮንን ከፊት ለፊት ያስቀምጣሉ።
debretsionከደህንነት መዋቅር ቁንጮ ላይ እንዳሉና መለስ ከሞቱ በኋላ ህወሃት ፊትለፊት ያወጣቸው ደብረጽዮን ከዋናው ስራቸው በተጨማሪ በምክትል ጠ/ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚና የፋይናንስ ክላስተር የሚመሩ ናቸው። ጉዳዩን የሚከታተሉ እንደሚሉት እንደ እሳቸው ፍላጎት ቢሆን አሁን የተወሰደው ርምጃ ከአምስት ወር በፊት መከናወን የነበረበት ጉዳይ ነበር።
አሁን በቁጥጥር ስር የነበሩት ሰዎች ከአምስት ወር በፊት በቁጥጥር ስር እንደሚውሉ ይታወቅ እንደነበር የሚናገሩት የደህንነት ሰዎች “ከመለስ ህልፈት በኋላ በተፈጠረው የሃይል ክፍፍል  አሸናፊ ሆነው የወጡት ክፍሎች ቅርንጫፍ መቆራረጥ ጀመሩ እንጂ ርምጃው የጸረ ሙስና ዘመቻ አይደለም” ባይ ናቸው። የእነ በረከት ስምዓንና የወ/ሮ አዜብን ቡድን በመጻረር በመለስ ሞት ማግስት ዘመቻ የጀመሩት ቡድኖች ከሙስናው ባህር ውስጥ ተጨልፈው ወደ እቶን ውስጥ እንዲጣሉ ሲወሰን ደረጃ ተዘጋጅቶ እንደሆነ አንዳንድ መረጃዎች ያመለክታሉ።
መለስ አፍነው የያዙት የህወሃት “የመበስበስ” ችግር ገሃድ ከሆነ በኋላ አቶ ስብሃት ነጋ ግንባር ሆነው የወጡ ቢሆንም ለምን ታለፉ? የሚል ጥያቄ ስለመነሳቱ አስተያየታቸውን የሚሰጡት እኒሁ የደህንነት ሰዎች እንደሚሉት “አሁን የተጀመረው ኦፕሬሽን አሸናፊዎቹ ሃይሎች ጉልበታቸውን የሚያሳዩበትና የተጻራሪውን ቅርንጫፍ በመቆራረጥ ዋናውን ግንዶች ማድረቅና ለማገዶ የማዘጋጀት የታሰበ ነው” ዘመቻው በቀጣይነት በጡረታ ስም የሚያስወግዳቸው አውራ ሃይሎች እንዳሉት የሚናገሩት ክፍሎች አቶ አርከበ እቁባይና አምባሳደር ብርሃነ ገ/ ክርስቶስ  በዚህ የማጥራት ቀመር ውስጥ እንዳሉበት ይጠቁማሉ።
ወ/ሮ አዜብ መስፍንና አቶ በረከት ስምዖን ላይ ያነጣጠረ ዘመቻ ጀምረው የነበሩት አቶ ስብሃት  ነጋ ምንም ዓይነት ርምጃ እንደማይወሰድባቸው ያመለከቱት ውስጥ አዋቂዎች “ስብሃት ግን ቅርንጫፎቻቸው በሙሉ ተመልምለው ብቻቸውን ይቀራሉ። በመጨረሻም እንዲደርቁ ይደረጋል” ሲሉ ስለ ስሌቱ የሚያውቁትን ይናገራሉ።
“አቶ ስብሃት ላይ ርምጃ ከተወሰደ የባህሩ ዋና ተዋናዮች በሙሉ ርቃናቸውን ይቀራሉ። ሁሉም መረጃዎች ከወጡ ህወሃት ራሱ ባሰመረው የሞት መስመር ላይ ግንባር ቀደም ተሰላፊ እንዲሆን ያደርገዋል” የሚሉት የመረጃው ሰዎች፣ ለጊዜው አሸናፊ የሆኑት ክፍሎች የተነፈሱ ቢመስላቸውም ውስጥ ውስጡን የጋመ ጉዳይ ስለመኖሩም አመልክተዋል።
የሙስና ፋይል!! የህወሃት ፓናዶል!!
የፌዴራል የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን ከበቂ በላይ ጥቆማ እንደሚደርሰው፣ በሚደርሰው ጥቆማ መሰረት የማጣራት ስራ ባከናወነባቸው ተቋማት ላይ ርምጃ ለመውሰድ ሲጠይቅ ማዕቀብ እንደሚደረግበት ሰራተኞቹ ውስጥ ውስጡን የሚነጋገሩበት ጉዳይ ነው። ከደህንነት ጋር በቁርኝት የሚሰራው ይህ ተቋም ሳንጃ የሚሰጠው ህወሃት ሲታመም ነው። ኢህአዴግ ውስጥ ግለት ሲጨምር ሳንጃው ድንበር ተበጅቶ ይታዘዛል። ሰሞኑን የሆነውና ከዚህ ቀደም የተደረጉት ሁሉ የዚሁ አሰራር ነጻብራቆች ናቸው።
“ቴሌ በሙስና ገልምቷል” ከተባለና ዋናው ተፈላጊዎች እንዲሸሹ ከተደረገ ከአራት ዓመት በኋላ  ኮሚሽኑ “ሳንጃህን ካፎቱ አውጣው ተባለ” መባሉን የሚያስታውሱ ክፍሎች፣ በህወሃት ክፍፍል ወቅት በአንድ ጀንበር የተሰራውን የማራገፍ ድራማ ያጣቅሳሉ። አሁን በቅርቡ ኦህዴድ ውስጥ የህወሃትን የበላይነት ለመሸርሸር በተነሱ ወጣት አመራሮች ላይ ሙስናን ተንተርሶ የተወሰደውን የማጥራት ዘመቻ ያክላሉ። አሁንም በተመሳሳይ ሰሞኑን የተወሰደውን ርምጃ ከዚሁ ከኖረው የህወሃት “የመበላላት” ታሪክ ጋር የሚያገናኙት ክፍሎች፣ በግልጽ አሁን አሸናፊ ሆኖ ከወጣው ቡድን ቁንጮና “ልዕልት” ጋር አብረው የሚሰሩ ግለሰብና፣ ባለስልጣን መታሰራቸው ቢድበሰበስም የክስ ሂደቱ እየጠና ሲሄድ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አሁን ለመገመት የሚችግር እንደሚሆን ይናገራሉ።
ህወሃት በተለይም ተሹለክልከው መሪ የሆኑት አቶ መለስ ከበረሃ ጀምሮ ተቀናቃኞችን እንዴት ይበሉዋቸው እንደነበር ያጋለጡት የቀድሞው የህወሃት የገንዘብ ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መድህን አርአያ የሃሳብ ልዩነት አስመልክቶ ውይይት ተደርጎ መስማማት ባለመቻሉ በጣም ሲመሽ  “አሁን እንረፍ፣ እንተኛ” ከተባለ በኋላ በተኙበት በዛው እንዲቀሩ የተደረጉ ስለመኖራቸው ተናገረው እንደነበር በማስታወስ “የአሁኑ ህወሃት ውሳኔውን ተቋማዊ ለማስመሰል። ተቋሙም በህግ፣ በፍርድ ቤት ችሎት፣ በዳኞችና ራሱ መርማሪ፣ ራሱ ከሳሽ በሆነው የፌዴራል የጸረ ሙስና ኮሚሽን የሚመራ በማስመሰል መበላላቱን “ዲጂታል” አድርጎ እየሰራበት ይገኛል።
ለማጠቃለል
የድሃ ልጆች ቦዘኔ ተብለው ሲታሰሩ አገሪቱ ውስጥ የተዛባ ነገር አልነበረም። በፖለቲካ አመለካከታቸው ዜጎች እስር ቤት ሲጣሉ ህግ የተከበረ ነበር። ንጹሃኖች በፈጠራ ወንጀል ሲገረፉና በስቃይ ሲዘለዘሉ ፍትህ አልጎደለም ነበር። እናት በችግር ልጇን ለገበያ ዝሙት ስትልክ ሃፍረት አልነበረም። በዝርፊያ ገንዘብ አዲስ አበባ በህንጻ ስታብድ አግባብነት አይታይም ነበር። ህዝብ በኑሮ ግለት ሌማቱ ሲደርቅና ገንዳ ላይ ምግብ ፍለጋ ህጻናት ሲባትቱ ችግር ሆኖ አይቆጠርም ነበር። አለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰዎች እንደ ከብት በየአቅጣጫው ሲታጎሩ የፍትህ ስርዓቱ አልተዛባም ነበር … ሰሞኑን እስር ቤት የተወረወሩት አቶ ገብረዋህድ ፍርድ ቤት ቀርበው ስለ ባለቤታቸውና ልጃቸው ሲናገሩ “አገሪቱ ምን እየሆነች ነው” አሉ። ከኮብራ ወርደው ወህኒ ቤት ሲገቡ የአገሪቱ የፍትህ ስርዓትና የህግ የበላይነት እንደ ደቀቀ ታያቸው። የባለቤታቸው ከስርዓት ውጪ መታሰር አንገበገባቸው። የልጃቸው መታሰር አቃጠላቸው። ሌሎች ምን ይበሉ? የፕሮፌሰር አስራት ቤተሰቦችና ወዳጆች ምን ይበሉ? የእስክንድር ነጋ ልጅና ባለቤት ምን ይናገሩ? የነበቀለ ገርባ፣ የነ ኦልባና ለሊሳ፣ የነ ሌሊሴ ወዳጆ በኦሮሞነታቸው ብቻ ለስቃይ የተዳረጉና የመከራው ተካፋይ የሆኑት ቤተሰቦቻቸው ይህን ያህል ዓመት ችግሩን እንዴት ተሸከሙት?
የአቶ መለስ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን የቅርብ ባልደረባና የስራ አጋር የሆኑት የአቶ ገ/ዋህድ ባለቤትና ልጃቸው መታሰር ጥፋት ከሌለባቸው የሚደገፍ ባይሆንም ለሌሎች ባለስልጣናትና የህወሃት አለቅላቂዎች ታላቅ ትምህርት የሚሰጥ እንደሆነ በተለያዩ የማህበራዊ ድረአውዶች መነጋገሪያ ሆኗል።

ESAT Ye Ehud Weg May 19 2013 Ethiopia


Friday, 10 May 2013

A 30-second Skype call in Ethiopia could land you 15 years in prison


A 30-second Skype call in Ethiopia could land you 15 years in prison


A new law makes it a crime to engage in audio or video communications over the Internet



The Ethiopian government has passed new legislation that makes it illegal to use Skype and most other video chat platforms.

The Ethiopian government has passed new legislation that makes it illegal to use Skype and most other video chat platforms.
The country's government has passed a new law that makes it a crime to engage in audio or video communications using Voice over Internet Protocol (VoIP) services such as Skype, Google Talk and most other video chat platforms, according to Al Jazeera.
Anyone who makes a phone call over the Internet reportedly faces a three to eight year prison sentence and heavy fines thanks to the May 24 legislation.
The punishment for using an official Internet calling service such as Skype is even stronger, with violators facing a potential 15 years in jail, the African Review reports.
The government claims the law was passed in order to strengthen national security, according to Reporters Without Borders.
Ambroise Pierre, head of the non-profit organization’s Africa Desk, said the measure is really intended to restrict the flow of communication in and out of the country.
"The Ethiopian government is trying to attack every means of information exchange," Pierre said.
Former BBC Ethiopia correspondent Elizabeth Blunt says that law may be intended to protect the state's sole telecommunications provider, Ethio Teleco.
"Internet cafes may be allowing people to make calls for far less than the cost of Ethiopia telecom, the state's telecommunications provider that has the monopoly and charges very high prices — and doesn't want to have its service undermined," Blunt told BBC.
The new legislation also gives the government permission to inspect any imported voice communication equipment, Al Jazeera reports.
Internet access in Ethiopia is already relatively limited.
Only 360,000 Ethiopians, or .04% of the country’s population, had access to the Web in 2009, PCMag reports.
Access in the country’s capital, Addis Ababa, is also unreliable.
Several people have taken to Twitter to express anger over the new law.
"#Ethiopia - #Skype, not allowed please use smoke signals," Coldtusker wrote.
“Cant foster an environment of innovation w so much strangulation of the pipes. Guess they have a strategy out of it,” TMS Ruge tweeted.
Ethiopia has a long history of restricting new technology and later accepting it.
Owning a satellite dish in Ethopia was illegal 15 years ago, according to the blog “Transforming Ethopia.”
Credit cards were also outlawed at a time.
"Both examples show the distrust that the Ethiopian state has always had towards technological advancement," the blog says.
croberts@nydailynews.com

Read more: http://www.nydailynews.com/news/world/30-second-skype-call-ethiopia-land-15-years-prison-article-1.1097288#ixzz2Stz9M7UB

ያልተመዘገበ ቦንድ በኖርዌይም ይሁን በአውሮፓ ህብረት መሽጥ በህግ የተከለከለ ነው::


942239_10151621553164743_376386664_nበኖርዌይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ም/ቤት አባላት የወያኔ የአባይ ቦንድ ሽያጭ ህገወጥ እንደሆነ ለኖርዌይ ባለስልጣናት ማብራሪያ ሰጡ::
በኖርዋይ የሽግግር ምክርቤቱ ሰብሳቢ በአቶ ግሩም ዘለቀ የተመራው እና አባላቶቹን ያቀፈ ቡድን ለኖርዌይ የገንዘብ ሚኒስቴር እና ለገንዘብ ቁጥጥር ባለስልጣን ከፍተኛ ሃላፊዎች እና ባለስልጣናት ዲፕሎማቶች ከኖርዋይ የንግድ ህግ አኳያ የቦንድ አሻሻጥን በተመለከተ እያደረጉ ያለውን ህገወጥ ተግባር በዝርዝር አስረድተዋል::
የኖርዌይ መንግስት ባለስልጣናት እንዳሉት ያልተመዘገበ ቦንድ በኖርዌይም ይሁን በአውሮፓ ህብረት መሽጥ በህግ የተከለከለ ነው::ማንኛውም ለህዝቡ የቦንድ ሽያጭ ከማቅረቡ በፊት በኖርዌይ ህግ መሰረት ማስመዝገብ አለበት::
እንዲሁም በሌላ ወገን በስዊዲን የወያኔ አንጋች የሆኑት ወይዘሮ መብራት ዲፕሎማት ሆነው ወደ ኖርዌይ በመምጣት በኦስሎ ውስጥ ከሚገኘው የኢሚግሬሽን ዳይርክቶሬት ቦንድ ሊሸጡበት የሚችሉበትን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን
በተመለከተ በኖርዌይ ህግም ይሁን በአውሮፓ ህብረት ህግ ማንኛውም ዲፕሎማት በንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ለመሳተፍ እንደማይችል ህጉ አስቀምጧል::በዚህ ጉዳይ ላይ የሚደረግ ማንኛውም የቦንድ ንግድ ተቀባይነት የለውም ብለዋል የኖርዌይ የገንዘብ ሚኒስቴር ባለስልጣናት::
በኖርዋይ የሚገኙት የሽግግር ምክርቤቱ አባላት በጠበቃቸው አማካኝነት ይህንን ጉዳይ ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስዱት ተናግረዋል::ይህነኑ የወያኔን ህገወጥነት በኖርዌይ እና በመላው አውሮፓ ለማጋለጥ እና ህገወጥነቱን ለማሳወቅ የሚችል ግብረሃይል ተመስርቷል::