Sunday, 28 September 2014

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ /EPPFG/ የጀርመንን መንግስትን ጨምሮ ለአለም ታላላቅ መንግስታትና ድርጅቶች ባለ 6 ገጽ ደብዳቤውን አቀረበ

EPPFG Stamp 2
የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ የጀርመንን መንግስትን ጨምሮ ለአለም ታላላቅ መንግስታትና ድርጅቶች ባለ 6 ገጽ ደብዳቤውን አቀረበ::
ድርጅቱ በደብዳቤው የወያኔን የ 23 አመት የግፍና የጭካኔ አገዛዝ አንድ በአንድ ጠቅሶ ያቀረበ ሲሆን ይህም መቀጠል እንደሌለበት ያመነው  የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ ጠንክሮ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ዘግቧል:: ሃገራችን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት በማዕድን ሃብትዋ እና በስው ሃይል ትልቅ ብትሆንም በአስተዳደር ችግር ግን በአለም ከመጨረሻዎቹ ሃገሮች ተርታ ተመድባ መቀመጥዋ ለዚህ ትግል እንዳነሳሳውም ገልጾዋል::
ደብዳቤውንም :-
  • ለጀርመን መንግስት
  • ለአውሮፓ ህብረት
  • ለ አሜሪካ እስቴት ዲፓርትመንት
  • ለአምነስቲ ኢንተርናሽናል
  • ለጀኖሳይድ ዎች መላኩን ኣሳውቆዋል

ህወሃቶች “አቅም ግንባታ” የሚሉት፤ እኛ ደግሞ “አቅም አድክም” የምንለው ሂደት


ህወሃት የመምህራንን፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችንና የመንግስት ሠራተኞችን ”አቅም እገነባለው” ብሎ ተነስቷል። ለዚህ “አቅም ግንባታ” እያሉ ለሚጠሩት አሰለቺ እና አደንቋሪ አቅም አድክም ፕሮፖጋንዳ እየወጣ ያለው ወጪ ለሌላ ተግባር ውሎ ቢሆን ኑሮ የተሻለ ይሆን ነበር። የተሻለ ነገር በህወሃቶች መንደር ይሠራል ብሎ መጠበቅ ግን ሞኝነት ነው። ህወሃት የተፈጠረው አገርን ለማፍረሰና ህዝብን ለማስጨነቅ እንጂ የተሻለ ሥራ ሠርቶ ህዝብን ለማስደስት አይደለም።
ህወሃቶች በአፍቅሮተ ንዋይ አብደው አቅላቸውን የሳቱ፤ ለእውቀትና ከእነርሱ በተሻለ ደረጃ ለሚያውቅ ቅንጣትም ታክል ክብር የሌላቸው፤ ውሸት የመኖሪያቸው ድንኳን ሁኖ ለብዙ ዘመን ያኖራቸው ቡድኖች ናቸው። በዚህ ሁኔታ ራሳቸውን የገነቡ ቡድኖች የሌሎችን አቅም እንገነባለን ብለው የመነሳታቸው ነገር አገራችን የገባችበትን የውርደት አዘቀት ፍንትው አድርጎ የሚያሳየን ነው።
የንዋይ ፍቅር የክፋቶች ሁሉ መሠረት ነው። ህወሃቶች በዚህ በክፋት ሁሉ መሠረት በሆነው በንዋይ ፍቅር ያበዱ በመሆናቸው ህወሃቶችን ከክፋት፤ ክፋትን ደግሞ ከህወሃት ለይቶ ለማየት የማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል። እነዚህ ቡድኖች በአፍቅሮተ ነዋይ አብደው ለእብደታቸውም መድሃኒት ጠፍቶ እኛ ከሌለን አገሪቷን እንበትናታለን በሚል ቅዥት ውስጥ እንደሚኖሩም የታወቀ ነው። ህወሃቶች ገንዘብ ሊያሰገኝ የሚችለውን ማንኛውንም ዓይነት ወንጀል ለመፈፀም የሚያቅማሙ አይደሉም። ህዝቡን በሙሉ በገንዘብ የሚገዛ ቢያገኙ ህዝቡን በሙሉ ለመሸጥ ወደ ኋላ ይላሉ ብሎ ማሰብም አይቻልም። ይህን በመሰለ የሞራል ውደቀት ውስጥ የሚገኙ ህወሃቶች የህዝቡን አቅም እንገነባለን ሲሉ ትንሽም አለማፈራቸው አገራችን ከደረሰችባቸው የሞራል ውደቀቶች መካከል አንዱ ሁኖ ሊጠቀስ የሚችል ዓቢይ ጉዳይ ነው።
ህወሃቶች ለእውቀትና ከእነርሱ በተሻለ ደረጃ ማሰብ ለሚችል ሰው ያላቸው ጥላቻ ወደር የለውም። ለዚህም ነው ከእነርሱ መካከል ይሄ ነው ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል የተመሰገን የተማረ ሰው የማይገኘው። ለህወሃቶች የተማረ ማለት ሲጠሩት አቤት ሲልኩት ወዴት እያለ ለሆዱ ያደረ እንጂ ለአገሬ፤ ለህዝቤ፤ ለወገኔ ምን በጎ ተግባር ልፈፀም የሚል አስተሳሰብ ያለው ሰው አይደለም። የህወሃቶች ዋነኛው ችግር የተማረ ሰው መጥላታቸው ብቻ ሳይሆን ሁሉንም እኛ እናውቃለን ማለታቸውም ጭምር ነው።ሁሉን እኔ አውቃለሁ ማለት ደግሞ የድንቁርና ታላቅ ምልክት ነው። ከዚህ ድንቁርና ራሱን ማላቀቅ ያልቻለ ቡድን የዜጎችን አቅም እገነባለው ብሎ መነሳቱ ከአስገራሚ በላይ ሁኖብናል።
ውሸት ጥሩ ነገር እንዳልሆነ ከህወሃቶች በቀር ሌላው ሁሉ የሚስማማበት ነገር ነው። ህወሃቶች ግን ውሸትን እንደ ታላቅ የትግል ስትራቴጂ ይቆጥሩታል።ህወሃቶች በግለሰብ ደረጃ ሳይሆን በአገር ደረጃ ሲዋሹ ቅንጣት ታክል እፍረት አይሰማቸውም። እንዲያውም ውሸታቸውን እውነት እንደሆነ አድርገው ያምናሉ። ለምሳሌ ኢኮኖሚው ከ11% በላይ አድጓል ይላሉ። ይሄ አሃዝ እውነት እንዳልሆነ ይታወቃል። ህወሃቶችና የሰበሰቧቸው ኮተታም ካድሬዎች ይሄን ውሸት እውነት ነው ብለው ያምናሉ። በአጠቃላይ ህወሃቶች ስለራሳቸውም ሆነ ስለሚገዙት ህዝብ እውነቱን መናገር ሞኝነት ነው የሚል ፅኑ ዕምነት አላቸው። ይሄን ከመሰለ ፅኑ ደዌ ራሳቸውን ማላቀቅ ያልቻሉ ደካሞች የሌላውን አቅም እንገነባለን ሲሉ አለማፈራቸው ያሳፍራል።
የሰሞኑ አቅም ግንባታ ብለው የሚጠሩት ግርግር ዓላማው እና ግቡ በተሻለ ደረጃ ማሰብ የሚችሉ ዜጎች ልዩ ልዩ አማራጮችን ማየት አቁመው አካሄዳቸውን በሞራልም ሆነ በእውቀት ውዳቂ ከሆነው ከህወሃት ጋር እንዲያደርጉ ለማድረግ ነው። ብዙ ኮተታም ካድሬዎቻቸው ለራሳቸው እንኳ የማይገባቸውን አብዮታዊ ድሞክራሲ የሚባለውን ፍልስፍና አዘረክርከው ይዘው በተማሪዎችና በመምህራን ፊት ያለምንም ዕፍረት ተጎልተው እየዋሉ ነው። እነዚህ ቡድኖች ከእነርሱ በተሻለ ደረጃ የሚያስብውን ኃይል መፍራት ብቻ ሳይሆን ሥር የሠደደ ጥላቻም አላቸው። በዚህ በሚፈሩትና በሚጠሉት ዜጋ መሃል ተገኝተው ለሚጠየቁት ጥያቄ መልስ መስጠት ሲገባቸው ማስፈራራት ዛቻ እና ስድብን የመልሳቸው ማሳረጊያ አድርገውታል።
በመሠረቱ አቅም ግንባታ ሲባል ዜጎች ራሳቸውንም ሆነ አገራቸውን ወደ ተሻለ ደረጃ ሊያደርሱ የሚችሉበትን ሁኔታ በራሳቸው ማመቻቸት የሚችሉበትን አስተሳሰብ እንዲያሳድጉ የሚያስችል ነው። አቅም የሚገነባው የዜጎችን የመጠየቅ እና የመመራመር ችሎታ አዳብሮ የተሻለ አማራጭ እንዲያፈልቁ እንጂ መንግስት የሚለውን ብቻ አምነው እንዲቀበሉ ለማድረግ አልነበረም። የህወሃቶች አቅም ግንባታ ግን ዜጎች ማሰብ አቁመው መጠየቅንም ፈርተው ምንሊክ ቤተ-መግስት ውስጥ ከተተከሉት ዛፎች እንደ አንዱ ሁነው እንዲኖሩ ለማድረግ ነው። እነዚያ ዛፎች መጥረቢያውን ሥሎ ሊገነድሳቸው ለሚያንዥብበው ዛፍ ቆራጭ ገንድሶ እሰከሚጥላቸው ድረስ ጥላ ይሆኑታል። ያ መጥረቢያውን ስሎ የተከለላቸው ሰው ጠላታቸው መሆኑን የማወቅ አቅም ግን የላቸውም። የህወሃቶች የአቅም ግንባታ ግቡ ዜጎች እንደ ዛፉ እንዳያስቡ እና ጠላትን ከወዳጅ የሚለዩበትን አቅም ማዳከም ነው።
ህወሃቶች ከ11% በላይ አድገናል ይላሉ። እደገቱ እውነት ከሆነ ለምን እንራባለን? ለምንስ ዜጎች ስደትን ይመርጣሉ? ለምንስ የጨው፤ የሳሙና፤ የስኳር፤ የቲማቲም እና የሽንኩርት ዋጋ የማይቀመስ ሆነ? ብሎ የሚጠይቅ ዜጋ ጠፍቶ፤ የውሸቱን የ11% እድገት ተቀብሎ የሚኖር ዜጋ የመፍጠር ብርቱ ቅዥት አላቸው።በዚህ ቅዥት ውስጥ እንዳይኖሩ የሚያጋድቸው የለም፤ ውሸታቸውንም አምኖ መኖር የእነርሱ ችግር ነው። የእነርሱ ውሸት አምኖ መኖር አገር የሚያፍረሰው እና ዜጎችን የሚያሰጨንቀው የእኛን ውሸት እመኑ ብለው ወደ ማስገደድ ደረጃ ሲደርሱ ነው። አሁንም እያደረጉ ያሉት ይሄንኑ ነው። የመንግስት ሠራተኞች፤ መምህራንና ተማሪዎች ተገደው የህወሃቶችንን ውሸት እየተጋቱት ይገኛሉ። ኢትዮጵያዊያን ህወሃቶችን ማመን ካቆሙ ብዙ ዘመን ተቆጥሯል። ህወሃቶች በእንግሊዘኛው “ፓቶሎጂካል ላየርስ” ተብለው የታወቁ ናቸው። ይሄ ደግሞ በሽታ ነው። የህወሃቶች ውሽት ወደ በሽታ የተሸጋገረ ስለሆነ በማንኛውም መድረክና ሁኔታ የሚናገሩትን ማመን አይቻልም።ለምሳሌ የአዜብን ስታይል እንመልከት በስልክ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር ስትነጋገር መጀመሪያ “አዎን እኔ አዜብ ነኝ” አለች ከአንድ ደቂቃ በኋላ ተመልሳ ደግሞ “አይ እኔ አዜብ አይደለሁም“ አለች። ይሄ እንግዲህ ውሸት ወደ በሽታ ተሸጋግሮባቸው የመኖሪያቸው ድንኳን መሆኑን ያሰየናል። እንግዲህ ዜጎች የህወሃቶችን ውሸት አንሰማም፤የእናንተንም አቅም ግንባታ አንፈልግም ማለት የሚችሉበት አገር የላቸውም። ዜጎች ይሄን እሰማለሁ፤ ያንን ደግሞ መስማት አልፈልግም የሚባል መብታቸው በህወሃቶች ተገፏል። ይህ የዜጎችን የመምረጥ መብት የገፈፈ ገዥ ቡድን እያደረገ ያለው የዜጎችን አቅም ማዳከም እንጂ የዜጎችን አቅም መገንባት አይደለም።አቅም በግዴታ አይገነባምና።
ህወሃቶች የሙስና ምንጮች መሆናቸው የታወቀ ነው።ከህወሃት መንደር ከሌብነት የፀዳ ባለስልጣን አይገኝም።ሁሉም ሌቦች፤ ሁሉም ሥነ-ምግባር የጎደላቸው ሰው ምን ይለኛልን የማያውቁ ናቸው። እነዚህ ቡድኖች የሚፈፅሙትን ሙስና ማስቆም አገሪቷ ከገጠሟት ፈተናዎች መካከል አንዱ ቢሆንም መቆም ይኖርበታል። ይሄን ሙስና የማስቆም ኃላፊነት ከህወሃቶች እና ከኮተታም ካደሬዎቻቸው ውጪ ያሉ ዜጎችን ሁሉ ትብብር የሚጠይቅ ነው። በዚህ ረገድ መምህራኑና ተማሪዎች ለህወሃቶች ያነሷቸው ጥያቄዎች ተጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል። ህወሃቶች በሙስና መጨማለቃቸውን ከሌቦቹ ህወሃቶች በቀር ሁሉም ያውቃል። ህወሃቶች ከእንቅልፋቸው ሲነቁ በሚሊዮን የሚቆጠር ሃብት በእጃቸው ሲገባ የትግሌ ውጤት ይላሉ እንጂ ሰርቄ ነው የሚል አስተሳሰብ በአእምሯቸው ዝር አይልም። የህወሃቶች ትልቁ ችግር የሚፈፅሙትን ዝሪፊያ ሁሉ የትግላችን ውጤት ነው ይገባናል ብለው ከልባቸው ማመናቸው ነው። በዚህ ዓይነት አስተሳሰብ የተቃኘ ቡድን የዜጎችን አቅም ለመገንባት በሚል እያካሄደ ያለው አደንቋሪ ስልጠና ተብየው የዜጎችን አቅም ያዳክም እንደሆነ እንጂ በምንም መሠፍረት የማንንም አቅም አይገነባም።
እነዚህ ቡድኖች ያለ ምንም ዕፍረት ሙስናን እንታገላለን ይላሉ። በሙስና የተጨማለቁ ባላስልጣናት ሙስናን እንዋጋለን ብለው በድፍረት ሲናገሩም ይደመጣል።በሙስና የተዘፈቁ ባላስልጣናት መኖራቸው እየታወቀ ለምን ህግ ፊት አይቀርቡም ተብለው ሲጠየቁ መልስ የላቸውም። ኢታማዦር ሹሙ ሳሞራ የኑስ ዋና ሌባ መሆኑ ይታወቃል፤ በዘረፈው የህዝብ ሃብት የባንክ ቤት ባለድርሻ እሰከመሆን ደርሷል። መላኩ ፈንቴን እንዲታሠር የበየነው ህግ ሳሞራ የኑስን አይነካም። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በህግ ፊት እኩል ነው ቢባልም ሳሞራ የኑስና መላኩ ፈንቴን እኩል የሚያይ ህግ በኢትዮጵያ የለም። በዚህ ዓይነት የሞራል ዝቅጠት ውስጥ የሚገኝ ቡድን የሚገነባው አቅም ምንድ ነው? ዜጎችን በምን አቅጣጫ ወደየት ለመውሰድ ያለመ ስልጠና ነው እየተሰጠ ያለው ተብሎ ቢጠየቅም የሚገኘው መልስ ዜጎች ሁሉ እንደ ህወሃት በጎጥ አስተሳሰብ ተተብትበው፤ ሰው ምን ይለኛል ማለትን ረስተው፤ እግዚአብሄርን መፍራት ትተው፤ ግራና ቀኝ ማየትን አቁመው ከአንድ ማሰብ ከማይችል እንስሳ ሳይለዩ እንዲኖሩ ማድረግ ነው።
የግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ህወሃት የተባለውን ዘረኛና ዘራፊ ቡድን ከተቆናጠጠበት የሥልጣን ኮርቻ ላይ አውርዶ አገሪቷን የሁሉም ለማድረግ የሚችለውን እያደረገ ነው። ለኢትዮጵያ ህዝብ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከህወሃት የበለጠ ጠላት የለም። ህወሃት ዋነኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት መሆኑ ሊሠመርበት የሚገባ ነጥብ ነው። ይሄን ጠላት ሳያቅማሙ በሁሉም መስክ መታገል ግዜው የሚጠይቀው ከዜጎች የሚጠበቅ ተግባር ነው።
ተከብሬ የምኖርበት አገር ያስፈልገኛል የሚል ሁሉ ንቅናቄያችንን እንዲቀላቀል ዛሬም ደግመን የትግል ጥሪያችንን እናቀርባለን። እኛ አገር ያሳጡንን ቡድኖች በሚገባቸው ቋንቋን ለማነጋገር ሳንቅማማ የትግሉን ባቡር ተሳፍረናል። የትግሉን ባቡር አሁኑኑ ተሳፈሩና ለሁላችንም የትሆን አገር እንፍጠር።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

EU Human Rights Committee hearing on Andargachew Tsege

የውጭ ምንዛሬው ዘረፋ በወያኔ ባለስልጣናት እና አጋሮቻቸው ተጧጡፎ ቀጥሏል።

ካለምንም ዋስትና በስልክ ትእዛዝ ብቻ ባለስልጣናት በርካታ ዶላሮችን ከባንክ ይወስዳሉ።
– በድንበር አከባቢ የሚገኙ የውጪ ምንዛሬዎች ወያኔዎች ለግል ጥቅማቸው ይከፋፈሉታል።…
– የውጪ ምንዛሬው ዘረፋ ከብሄራዊ ባንክ ጀምሮ እስከ ድንበር ከተሞች የባንክ ቅርንጫፎች
ድረስ በሙስና መረብ የተያያዘ የባለስልጣናት ስውር እጆች የተደባለቁበት ነው::
– “የሃገሪቱ ዘለቄታዊ የኢኮኖሚ ጥቅሞች በባዶ ካዝናዎች ተተክተዋል።” የብሄራዊ ባንክ ባለሙያዎች
dollarከባንኮች አከባቢ የሚወጡ ዘገባዎች እንዳመለከቱት በላኪነት ስራ ላይ በብዛት ተሰማርተው የሚገኙት የገዢው መደብ ባለስልጣናት እና ዘመድ አዝማዶቻቸው እንዲሁም በጥቅም ትሥሥር ላይ የተለጠፉ አቆርቋዥ ነጋዴዎች ንግድን ሽፋን በማድረግ ሃገሪቷን በማራቆት ስራ ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ::አንዳንድ ባለስልጣናት ደሞ እንደ ቻይና ህንድ እና ቱርክ ከመሳሰሉ ከውጪ አገር ዜጎች ጋር የውስጥ ሽርክና በመፍጠር በጥቅም ትሥሥር ከመሬት ጀምሮ እስከ ማንኛውም ማተሪያሎች ከቀረጥ ነጻ ወደ ሃገር ውስጥ ሲገቡ በኢንቨስትመንት ስም ከሚመሰረተው ድርጅት ጋር የማይገናኙ ውድ እቃዎች ሳይቀሩ ገብተው ሃገሪቷ ማግኘት የሚገባትን እንዳታገኝ ባለስልጣናት ጋሬጣ ሆነዋል::
እንደባንክ ባለሙያዎች መረጃ ከሆነ የወያኔ ባለስልጣናት ቤተሰቦች እና ዘመድ አዝማዶች በላኪነት ስራ ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ በግልጽ የሚታወቅ ሲሆን ገንዘብን ምንም አይነት ዋስትና ሳያሲዙ በአነስተኛ ወለድ እየወሰዱ የማይከፍሉ እና ሰነድ የሚያስጠፉ እንዲሁም ያለምንም ቀረጥ እና ታክስ ወደ ውጭ ሃገር ምርቶችን በመላክ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሃገር ቤት ከማምጣት ይልቅ በተለያዩ የአውሮፓ እና የኢሲያ ሃገራት ባንኮች ይዶሉታል:: የባለስልጣናት ቀጭን የስልክ ትእዛዝ በአስር ሺዎች የሚቆጠር ዶላሮች ኢሮዎች እና ፓውንዶች ከባንክ ይወሰዳሉ።
ብሄራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬን ለመሸጥ እና ለመግዛት ዋጋ ቢወስንም የግል ባንኮች ግን የውጭ ምንዛሬ መግዣ ዋጋን ወደጎን በመተው ከወያኔ የላኪ ድርጅቶች የውጭ ምንዛሬ በመሸጫ ዋጋ እንዲሸምቱ ሲደረግ በዝምታ ታልፈዋል:: አንዳንድ ላኪዎች ከመንግስት ባንኮች የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሬ በተዘዋዋሪ ለግል ባንኮች ሲቸበችቡ እየታየ በዝምታ እየታለፈ ነው::በመተማ በሞያሌ በመልካ ጀብዱ በኩምሩክ በሁመራ በሃርትሼክ ወዘተ በኢትዮጵያ ዙሪያ ገባ የድንበር ከተሞች ላይ በከፍተኛ የኮንትሮባንድ ንግድ ላይ የተሰማሩት በአብዛኛው የወያኔ አባላት እና የአከባቢ ባለስልጣናት ካድረዎች ከሚወጡ የሃገር ውስጥ ምርቶች የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ለግል ጥቅማቸው እንደሚያውሉት ታውቋል::ይህም ጉዳይ በከፍተኛ ደረጃ ከብሄራዊ ባንክ ጀምሮ እስከ ድንበር ከተሞች የባንክ ቅርንጫፎች ድረስ በሙስና መረብ የተያያዘ የባለስልጣናት ስውር እጆች የተደባለቁበት ነው::
መሰረታዊ ለሆኑ የገቢ እቃዎች የጠፋው የውጭ ምንዛሬ በባለስልጣናት ሲዘረፍ ለሃገሪቱ የፖለቲካ ፍጆታ የመከላከያ እና የደህንነት መዋቅሮች ሲመደብ ማየት በህዝብ ጉሮሮ ላይ ቆሞ ስልጣንን በማስረዘም ሃገርን እየገደሉ መሆኑ በአደባባይ እያየነው ያለነው ሃቅ ነው:;የብሄራዊ ባንክ ከጊዜው የገዢ መደቦች ጋር በማበር የሃገርን ሀለቄታዊ የኢኮኖሚ ጥቅሞች አሳልፎ እየሰጠ ከባንክ አሰራር ውጭ ከፖለቲካው ጋር ግንኙነት ያሌላቸው አስመጪ ነጋዴዎች ማግኘት ያለባቸውን የውጭ ምንዛሬ ባለማግኘታቸው በሰላሳ እና አርባ ፐርሰንት ጭማሪ ምንዛሬዎችን በመግዛት ጋሬጣ የተፈጠረባቸው ሲሆን ይህ ሁሉ የገዢው መደብ አባላት የፈጠሩት የውጭ ምንዛሬ ዘረፋ በሃገሪቷ ላይ የኑሮ ውድነት እንዲሰራፋ አድርጎታል::

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)


ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ …ከኤርምያስ ለገሰ

በቅድሚያ መጵሀፉን ጊዜ ሰጥተህ በማንበብ አስደማሚ ምልከታ በመስጠትህ ከልብ አመሰግናለሁ ። የተጳፈበትም አንዱ አላማ ይህ ስለሆነ። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በእይታህ ላይ እነዚህ ጉድለት ይታይባቸዋል ብለህ ያነሳኸው እና የወደፊት ግምቶችህ ላይ የተወሰነ አስተያየት ለመስጠት የሚጋብዙ ስለሆነ ትንሽ ማለት ፈለኩ። በዚህ አጋጣሚ ሌሎች በመጵሀፉ ይዘት ላይ ዝርዝር ግምገማ ላደረጉ ሰዎች ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። ለእያንዳንዱ አስተያየት መስጠት ከጊዜ አኳያ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ የማልዘልቅበትን መንገድ ልጀምረው አልፈለኩም ። የጋዜጠኛ ተመስገንን በልዩ ሁኔታ መመልከት የፈለኩበት የራሱ ምክንያቶች አሉት። ተመስገን ሀገር ቤት ባለ አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ በድፍረት መጵሀፉን ማንበቡን በአደባባይ ገልጶ በመጵሄት ሳይቀር መክተቡ ልዩ ያደርገዋል ። አንዳንድ የቀድሞ ” የትግል ጓዶቼ! ” በሚስጥር ቢሮ እየቆለፉና እቤታቸው እየደበቁ ባነበቡበት ሁኔታ የተመስገን ፊትለፊት ማውራት ምንያህል የህሊና ራስ ምታት እንደለቀቀባቸው ማሰቤ ሁለተኛ ምክንያት ነው( ቢያንስ ሁለት “ሚኒስቴር ደረጃ ያሉ ሰዎች ” የተፃፈው ሐቅ ስለሆነ ማስተባበል አይቻልም ” የሚል አስተያየት መስጠታቸውን እርግጠኛ ከሆነ ምንጭ ሰምቻለሁ ። ማረጋገጥ ለምትፈልጉ ” የዲሞክራሲ ሐይሎች” በውስጥ በኩል ጠይቁኝ) ከዚህም በተጨማሪ ከወደ ካሊፎርኒያ የደረሰኝ ዜና የስርአቱ ደጋፊ የሆኑ ሰዎች መጵሀፉን ሲያዙ በአንድ ጊዜ እስከ ሀምሳ ኮፒ መጠየቃቸውን ነበር( መረጃውን ያደረሰኝ የዘወትር ተባባሪዬ ሔኖክ የሺጥላ ” እነዚህ ሰዎች ሊያነቡት ነው ወይስ ሊያቃጥሉት?” የሚል ጥያቄ ቢጠይቀኝም መልስ መስጠት አልቻልኩም ። መልስ ካላችሁ ተባበሩኝ።)
ሦስተኛው ምክንያት የተመስገን ፅሁፍ ሐገር ቤት በመጵሄት መልኩ ቢሰራጭም የመለስ ” ትሩፉቶች” ግን ህጋዊ በሆነ መንገድ እንድትባዛ ብትጠየቅም ሐገር ቤት ያሉ (ጥያቄው የቀረበላቸው) አሳታሚዎች ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል ። በዚህም ምክንያት ወደ ህዝቡ በሰፊው መሰራጨት አልቻለም። ( በዚህ አጋጣሚ ነጳነት አሳታሚ ኢትዮጵያ ለሚያሳትም ሰው ስክሪፕቱን በነፃ ለመስጠት ፍላጐት እንዳለው ገልጶልኛል።)
ይህን እንደ መንደርደሪያ ካነሳሁ ዘንዳ የጋዜጠኛ ተመስገን ምልከታዎች ላይ ያሉኝን አስተያየቶች ላስቀምጥ።
1• “መፈንቅለ መንግሥት”
ተመስገን ከሐገር የወጣሁበት ዋነኛ ምክንያት በአንድ ወቅት የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ተደርጓል ብዬ መናገሬ አቶ መለስን እንዳስቆጣው እና አቶ በረከት ይህን ተከትሎ ያለስራ እንዳንሳፈፈኝ፣ በዚህም ምክንያት ቅሬታ ቋጥሬ በትምህርት ሰበብ ከሐገር መኮብለሌን ገልፆአል ። ይህን ክስተት በመጵሀፉ ላይ መገለጵ እንደነበረበት አመላክቷል ።ይህ የተዛባ መረጃ ነው። ኢንፎርሜሽኑ ከውስጥ ወደ ውጭ ስለሆነ መዛባቱ ብዙም አልገረመኝም።
ጋዜጠኛ ተመስገን በመጵሀፉ የመጀመሪያ ገፅ ላይ ” የአሳታሚው ማስታወሻ” የሚለውን ክፍል ያነበበው አልመሰለኝም ። አሳታሚዎቹ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በመጀመሪያው መፅሐፍ ትኩረት የተደረገባቸውን የአዲሳአባና ተያያዥ ጉዳዬች ብቻ እንደሚያሳትሙ ፣ በቀጣይ በሌሎች ጉዳዬች ( መፈንቅለ መንግስቱን ጨምሮ) እንደሚመለሱ ገልፀዋል።
በማሰከተል ” የመንግሥት ግልበጣ” የምትለው ማእከላዊ መልእክት ጣጣ እንዳመጣችብኝ መገለጱ ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ ውሸት የመናገር ፍላጐት ቢኖረኝ ኖሮ ይህን የተመስገን አስተያየት ልክነው እል ነበር። ይህን የሚያክል ሀገርና አለም የሚያናውጥ መልእክት ቀርጬ የማስተላለፍ ስልጣን ቢኖረኝ ኖሮ ፣ የሃገሪቷን ስልጣን ” ከትግራይ የፈለቀው ገዥ መደብ” ጠቅልሎ ይዞታል የሚል አንደበት አይኖረኝም ነበር። እንደዚህ አይነት ማእከላዊ መልእክት የመቅረጵ ሚና ትላንትናም ሆነ ዛሬ እኔ፣ ሽመልስ ከማል፣ሬድዋን ሁሴን የለንም ። ጠቅላይ ሚኒስትር ሐይለማሪያምም የላቸውም / አይኖራቸውም ። በመሆኑም ከ ” መፈንቅለ መንግስት” ወደ ” ባለሥልጣናት ግድያ” ከዛም ወደ ” ቀቢፀ ተስፉ ” የሚል መልእክት የተቀረፀው ከአንድ ግለሰብ ነበር። መቼም ለምን? እንዴት? ምን ለማትረፍ የሚለው ጥያቄ አሁን እንደማይነሳ ተስፉ አደርጋለሁ ።
በማስከተል የአሜሪካ ጉዞዬን በተመለከተ ትምህርት የሚባለው መንግሥት ተደናግጦ በመጀመሪያው ሰሞን ያስተላለፈው ነበር ( በቅርብ ቀን ደግሞ ሌላ ነገር ብለዋል።) ሲጀመር ወደ አሜሪካ እንደምመጣ የተነገረኝ ኮሙዩኒኬሽን ጵ/ ቤት ከመቋቋሙ በፊት አደረጃጀቱን ለማስተካከል ስለ “Situation Room” አሰራር ለመመልከት አስቀድሞ የተያዘ ፕሮግራም ነበር። እኔ ብቻ ሳልሆን ከውጭ ጉዳይም ሌላ ሐላፊ አብሮኝ ነበር። በታህሳስ የታቀደው ጉዞ በአጣዳፊ ስራዎች ምክንያት ተላልፎ ሰኔ መጨረሻ ተቆረጠ።በርግጥ እንደ ማስታወሻ ፀሐፊ እስከ ሰኔ መቆየቴ አልከፉኝም( ድርጊቶቹ የግድ መፈፀማቸውና ሰለባዎች መኖራቸው እስካልቀረ ድረስ።) ወንድም ተሜ! መቼስ እንደራስህ የምትወዳቸውን እስክንድርና ሲሳይ አጌና ከውስጥ ወደ ውጭ ምን አይነት ሴራ ሲጠነሰስባቸው እንደነበር መስማት ትፈልጋለህ፣ መቼስ! የክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ የቀብር ስርአት ላይ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት አታካራ መስማት ትፈልጋለህ( አንተም ቢሆን በፍትህ ጋዜጣ ላይ ” ለምን አባረህ በለው ያንን አመጸኛ… ” ብለህ የጳፍከውን የፀቡ አንድ ክፉይ መሆኑን ቀብድ ያዝልኝ ፣ መቼስ! የአልበሽር ፣ የብርቱካን ሚደቅሳ፣የቴዲ አፍሮ፣… ወዘተ ጉዳዬች የወቅቱን የፓለቲካ ምህዳር አጣበውት እንደነበር አይዘነጋም። እናም ስለእነዚህ እና ሌሎች ጉዳዬች ለማውጋት እድሉን በማግኘቴ ጊዜውን እንደባከንኩ ይቆጠር ይሆን?
2• የፍትህ ጋዜጣ ባልደረባ ስለነበረው ማስተዋል ብርሐኑ በተመለከተ፣
ጋዜጠኛ ማስተዋል እንደገለፀው ቢሮ ጠርቼ አናግሬዋለሁ። እንደ ማስፈራራትም ከተመለከተው የስርአቱ ባህሪና እኔም የዛ ስርአት ውላጅ ስለነበርኩ ከዛ ውጭ ልሆን አልችልም። ለደረሰበት የስነ ልቦና ጫና ይቅርታዬን አድርስልኝ።( በነገራችን ላይ ስርአቱ ውስጥ በነበረኝ አስተዋጽኦ ይቅርታ መጠየቁ ችግር ያለብኝ ሰው አይደለሁም ።በተለይ በግለሰብ ደረጃ ከይቅርታም አልፌ በመጵሀፉ ምእራፎች መታሰቢያ ያደረኩት አለ። ” እውን ታሪክ ራሱን ደገመ? ” የሚለውን ምእራፍ ልብ ይሏል።)
ነገር ግን ከሃላፊነት ራሱን እንዲያገል ጠይቆኝ ነበር የሚለው ትክክል አይደለም ። እንደውም በወቅቱ የነበረው አቅጣጫ ጋዜጠኛን ወደ ኢህአዴግ መሳብ ስለነበር በተቃራኒው ሊሆን ይችላል ። መቼስ ወንድም ተሜ!ከፍትህ ጋዜጣ ጋር ኢሕአዴግ ለምን ተጣላ? ጋዜጠኛ ማስተዋልን በምን ጉዳይ አናገርኩት? ጋዜጣው ላይ ለምን እርምጃ ተወሰደ ( የነበርኩት ጥንስሱ ላይ ነበር)የሚለውን ቁምነገር አሁን እንደማትጠብቅ ተስፉ አደርጋለሁ። በነገራችን ላይ በጋዜጣህ ላይ እኔና ጋዜጠኛ ሳምሶን ( ካልጠፉ ሰው!!) አጃምላችሁ ” ሚኒስትር ዴኤታውና ጋዜጠኛ ሳምሶን ማሞ ሊከሰሱ ነው!” ብላችሁ በፊት ገፅ ያወጣችኃት በሀገረ አሜሪካ ኢምግሬሽን ጵ/ ቤት የጥያቄ መአት አዥጐድጉዳለች። ሂሳብ ማወራረድ ሳይጠይቅ አይቀርም!! እውነት እውነት እልሃለሁ የበግ ለምድ ከለበሰው ተኩላና ከጅምሩ ከምጠየፈው ሰው ጋር ማጃመላችሁ አሳዝኖኛል ። ጋዜጣዋ የወጣች እለት ለእሱ የወገንተኝነት ማረጋገጫ ብስራት፣ ለእኔ ደግሞ ሐዘን ነበር።እውነቴን ነው የምልህ ጋዜጠኛ (?) ሳምሶንን ኢህአዴግ ቢሮ ጀምሮ እጠየፈዋለው። ታዲያ እኔ ብቻ እንዳልመስልህ?…
3• የፓለቲካ ሁለተኛ እድል
ይህቺ አስተያየት የአንተ አይደለችምና ጣላት ። ነው ካልከኝም በድፍረት እነግርሀለሁ ። ተሳስተሀል። ይህ አጀንዳ ሆን ተብሎ በኢህአዴግ እና እጅግ በጣም ጥቂት የራሳቸው ሚና ያነሰ የመሰላቸው ( self ego) ባላቸው ሰዎች የሚቀነቀን ነው። አልፎ አልፎም ” የማንነት ሰርተፍኬት ሰጪና ነፉጊ ” አድርገው ራሳቸውን ከቆጠሩ ግለሰቦች የሚመነጭ ነው። ከኢህአዴግ ውጭ ያሉት የተዛባም ቢሆን ምክንያትና ተጨባጭ ተሞክሮ ስላላቸው የሚጣል አይደለም ። ተገቢ የማይሆነው ኢህአዴግ ይህን እንደ መደላድል እንዲጠቀም ለም መሬት ሆነው ማገልገላቸው ነው።
ወንድም ተሜ! ወጋችን ካንተ ጋር ስለሆነ ወደዛው ልመለስ ። እስቲ አንድ ጥያቄ ልጠይቅ? ከዚህ በፊት ከኢህአዴግ ጋር ከሰሩ እና ጥለው በመውጣት ተቃዋሚን ከተቀላቀሉ ግባብዳ ካድሬዎች ላይ ይህን እኔ ላይ ያነሳኸውን ጥያቄ አንስተሀል?
ግራም ነፈሰ ቀኝ እኔን በተመለከተ የየትኛውም ፓለቲካ ፓርቲ አባል አይደለሁም። አባል ያልሆንኩት ለጊዜው የድርጅት ተልእኮ የመሸከም አቅም ስለሌለኝ ነው ።ከዚህ በተጨማሪም ለተወሰነ ጊዜ ( ቢያንስ የጀመርኳቸውን መፅሐፍት እስክጨርስ) ያለድርጅት ተጵእኖ ነፃነቴን ጠብቄ መኖር ስለምፈልግ ነው። የድርጅት አባል መሆን ( በተለይ የተቃዋሚ) ቁርጠኝነት ፣ የአላማ ጵናት፣ ጊዜን መስዋዕት ማድረግ፣ ግለኛ አለመሆን… ወዘተ ይጠይቃል ። ለእንደዚህ አይነት ሰዎች( የትኛውንም የትግል ስልት ለሚጠቀሙ ) ልዩ አክብሮት አለኝ። መደገፍ አለባቸው የሚል እምነት አለኝ።
እንግዲህ በመጀመሪያው ምልከታህ ላይ ያሉኝ አስተያየቶች ከሞላ ጐደል እነዚህ ናቸው። ሁልግዜም የተላበስከውን የቁርጠኝነት ፀጋ አብሮህ እንደሚዘልቅ እምነቴ ነው።

Thursday, 4 September 2014

በተማሪዎች ላይ የኃይል እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ተገለጸ

UNiversity students
በትምህርት በኢህአዴግ ጽ/ቤትና በትምህርት ሚኒስትር ትብብር ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሚሰጠው ስልጠና በተማሪዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ተገልጾአል፡፡ በስልጠናው ሰነድ ላይም ተካትቷል፡፡ ‹‹የትምህርት ተቋማትን ወደ ትክክለኛው የትግል ስልት የመመለስ አስፈላነት›› በሚል አብይ ጉዳይ ላይ በተሳሳተ ስልት ይንቀሳቀሱ እንደነበር በመጥቀስ ‹‹ተማሪው ጥያቄውን የሚያቀርበው ትምህርቱን እየተማረ፣ የትምህርት ቤቱን ህግና ደንቦች እያከበረ ሊሆን ይገባል፡፡…..ህገ ወጥ ሆኖ ህጋዊ ምላሽ ማግኘት አይቻልም፡፡›› በሚል ‹‹ህገ ወጥ ከሆኑ›› ህገ ወጥ ምልሽ እንደሚጠብቃቸው ያስጠነቅቃል፡፡

ሰንዱ አክሎም ‹‹በተማሪው ማህበረሰብ ውስጥ አፍራሽ አዝማሚያ ያላቸው ተማሪዎች ነውጥን ለማስፋፋት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በጥብቅ በመታልና የንብረት ውድመት እንዳይደርስ በጥብቅ መታል ይገባል፡፡ በቅድሚያ ራስን መነጠል እና ቀጥሎም የነውጥ ኃይል አራማጅና ደጋፊ የሆኑትን ማጋለጥና ትግል ማድረግ ይገባል›› በሚል በተማሪዎቹ ላይ ሊወሰድ የሚችለውን እርምጃ ይዘረዝራል፡፡
ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/34261

Wednesday, 3 September 2014

ኑና እንወያይ

ኑና እንወያይ

የወያኔ ዘረኞች የግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ጸሐፊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸዉ ጽጌን ፍጹም ህገወጥ በሆነ መንገድ አስሮ ማሰቃየት ከጀመሩ እነሆ ሃምሳ ቀኖች ተቆጥረዋል። ሠላማዊ ዜጎችን ሽብርተኛ ብለዉ ካሰሩ በኋላ የፈጠራ ታሪክ እየጻፉ የቴሌቪዥን ድራማ መስራት የለመዱት ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በአቶ አንዳርጋቸዉ ላይም በዉሸት የተቀነባበረ ድራማ ሰርተዉ የዚህን ጀግና ሰዉ ተክለሰዉነት ጥላሸት ለመቀባት ሞክረዋል። ሆኖም ቆሻሻ ፈብራኪዎቹ የወያኔ ፕሮፓጋንዳ ተቋሞች ያሻቸዉን ድራማ ቢሰሩም በአለም ዙሪያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በአንድ ድምጽ “እኔም አንዳርጋቸዉ ነኝ” እያሉ ትግሉን በመቀላቀል ግንቦት 7 የዕልፍ አዕላፍት ድምጽ አንጂ የአንድና የሁለት ሰዎች ድርጅት አለመሆኑን በተግባር ለወዳጅም ለጠላትም አሳይተዋል። በእርግጥም ግንቦት 7 ወያኔ አንዳርጋቸዉን ካሰረ በኋላ ህዝብን ለማታለል እንደሞከረዉ ያበቃለት ድርጀት ሳይሆን ወያኔና ቆሻሻ ስርዐቱ ተጠራርገዉ ቆሻሻ መጣያ ዉስጥ እስካልገቡ ድረስ በየቀኑ እያደገ የሚሄድ ህዝባዊ መሠረት ያለዉ ድርጅት ነዉ።
ዛሬ ኢትዮጵያን ጨምሮ በየአህጉሩ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በአካል ሲገናኙም ሆነ በማህበራዊ ሜዲያዎች ሲሰባሰቡ አንድነታቸዉን የሚገልጹበትና የትግል ቃልኪዳናቸዉን የሚያድሱበት ቃል “እኔም አንዳርጋቸዉ ነኝ” የሚል ቃል ነዉ። ባለፉት ሃምሳ ቀኖች በዚህ መልኩ በወያኔና በተላላኪዎቹ ላይ ቁጣዉን ሲገልጽ የሰነበተዉ በዉጭ አገሮች የሚኖረዉ ኢትዮጵያዊ ወያኔን ባስቸኳይ ለማስወገድ በሚቻልበት መንገድ ለመምከርና ለእናት አገሩ ኢትዮጵያ ያለዉን ፍቅር በተግባር ለማሳየት ከፊታችን እሁድ ነኃሴ 24 ቀን እስከ መስከረም 4 ቀን ባሉት ሦስት ተከታታይ እሁዶች በ26 ታላላቅ የአለም ከተማዎች ዉስጥ በአይነቱ ልዩ የሆናና ከዚህ ቀደም ተደርጎ የማያዉቅ ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ ያደርጋል። የእነዚህ “እኔም አንዳርጋቸዉ ነኝ” በሚል መሪ ቃል የተጠሩ ስብሰባዎች ዋና አላማ አንዳርጋቸዉና ከሱ በፊትም ሆነ ከሱ በኋላ ለእናት አገራቸዉ ኢትዮጵያ አንድነት፤ ሠላምና ብለጽግና ሲሉ የታሰሩና የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉ ኢትዮጵያዉያን የቆሙለትን አላማ ከግብ ለማድረስ ምን ማድረግ አለብን የሚለዉን ትልቅ ጥያቄ በጋራ ለመመለስ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱና ለነጻነቱ የሚያደርገዉ ትግል ወደመጨረሻዉና ፈታኝ ወደሆነዉ ወሳኝ ምዕራፍ ዉስጥ መግባቱን ሁሉም ኢትዮጵያዉ የተገነዘበዉ ይመስለናል፤ ሆኖም በጋራ ለሚደረግ ህዝባዊ ትግል ህዝብ ቁጭ ብሎ በጋራ ካልመከረበትና ተስማምቶ ለድል የሚወስደዉን ጎዳና በጋራ ካልቀየሰ ትግላችን ወሳኝ ደረጃ ላይ መድረሱን መገንዘቡ ብቻ በራሱ ፋይዳ ይኖረዋል ብለን አናምንም። ስለሆንም በአነዚህ ብዙዎችን አቀራርበዉና አወያይተዉ ለህዝባዊ ትግሉ የሚበጁ ጠቃሚ ሀሳቦችን ያፈልቃሉ ብለን በምናምንባቸዉ ስብሰባዎች ላይ የአገሬ ጉዳይ ከግል ጉዳዬ በላይ ነዉ ብሎ የሚያምን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ተገኝቶ የበኩሉን አስተዋጽኦ አንዲያደርግ የዝግጅት ክፍላችን በዚህ አጋጣሚ አገራዊ ጥሪ ያደርጋል።
ለመሆኑ በአለም ዙሪያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ድምጻቸዉን ከፍ አድርገዉ በየአደባባዩና በየስብሰባ አዳራሹ “እኔም አንዳርጋቸዉ ነኝ” እያሉ ሲጮኹ ምን ማለታቸዉ ነዉ? ወያኔ ስልጣን ይዞ በቆየባቸዉ ባለፉተረ ሃያ ሦስት አመታት ዉስጥ አያሌ ኢትዮጵዉያን የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ አርበኞች ታሰረዋል፤ ዘግናኝ በሆነ መልኩ ተገርፈዋል ብዙዎች ደግሞ ተገድለዋል። ኢትዮጵያዉያንን እያፈሱ ማሰር በአንዳርጋቸዉ አልተጀመረም አንዳርጋቸዉ ስለታሰረም አያበቃም። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች እኛ በቃ ብለን ካላቆምናቸዉ በቀር እኛን ማሰርና መግደል በስልጣን ላይ የመቆየት ዋስትናቸዉ አድርገዉ ስለሚመለከቱ መግደላቸዉንና ማሰራቸዉን በፍጹም አያቆሙም። እንግዲህ “እኔም አንዳርጋቸዉ ነኝ” ስንል ኢትዮጵያ ዉስጥ በዘፈቀደ ዜጎችን ማሰርና መግደል እንዲቆምና አናሳዎች በሀይል የጫኑብን ዘረኛና አግላይ ስርዐት ተደምስሶ ሁሉን አቀፍ ህዝባዊ ስርዐት እንዲፈጠር ማድረግ የምንችለዉን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኋላ አንልም ማለት ነዉ። ይህ ማለት ደግሞ አንዳርጋቸዉ ጽጌ፤ እስክንድር ነጋ፤ ኡስታዝ አቡበከር፤ በቀለ ገርባ፤ ሠላማዊት ሞላ፤አዚዛ መሐመድ፤ ርዕዮት አለሙና ሌሎችም ለአገር አንድነትና ለህዝብ ነጻነት ሲታገሉ የዘረኞች ሰለባ የሆኑ ጀግኖቻችን የቆሙለትን አላማ አንግበንና ትከሻ ለትከሻ ተደጋግፈን ወደማይቀረዉ ድል እንጓዛለን ማለት ነዉ።
ዛሬ ሁላችንም በግልጽ እንደምንመለከተዉ ኢትዮጵያዉያን በያሉበት ቦታ ሁሉ ትግሉን እንዴት እንቀላቀል፤ ምን ላድርግ ወይም እንዴት ትግሉን ልርዳ የሚሉ ጥያቄዎችን በየቀኑ እየጠየቁ ነዉ። እነዚህ ጥያቄዎች ደግሞ አንዳርጋቸዉ ስለታሰረ ብቻ ሰኞ ተረግዘዉ ማከሰኞ የተወለዱ ጥያቄዎች ሳይሆኑ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሆድ ዉስጥ ከሃያ አመታት በላይ ታፍነዉ የቆዩና በአንዳርጋቸዉ መታሰር ፈንድተዉ የወጡ ጥያቄዎች ናቸዉ።
የወያኔ ተላላኪዎች አንደሚከስሱን የአገር ጥላቻ ሳይሆን የአገር ፍቅር ጥያቄዎች ናቸዉ፤ ዘረኝነትና ጎሰኝነት የቀሰቀሳቸዉ ጥያቄዎች ሳይሆኑ ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ የዘረጋዉን ያጋጠጠ የዘረኝነት ስርዐት ለማፍረስና በቦታዉ ሁሉንም የአገሪቱ ዜጎች በእኩልነት የሚመለከት ስርዐት ለመፍጠር የሚነሱ ጥያቄዎች ናቸዉ። ግንቦት ሰባት በሃያ ስድስት ከተማዎች ዉስጥ የጠራቸዉ ህዝባዊ ስብሰባዎች እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉ ጥያቄዎችን የሚመልሱ ስብሰባዎች ናቸዉ። እነዚህ ስብሰባዎች ከዚህ ቀደም እንደተለመደዉ ከመድረክ ላይ የሚወረወሩ ሀሳቦችን ብቻ አስተናግደዉ የሚበተኑ ስብሰባዎች አይደሉም። እነዚህ ስብሰባዎች የስብሰባዉ አዘጋጆችና የስብሰባዉ ተሳታፊዎች በአንድ መንፈስ ሆነዉ ይህንን የተበታተነ ህዝባዊ ትግል የሚያስተባብርና ትግሉን በተቀናጀ መልክ እንዴት ለድል ማብቃት እንደምንችል የምንመክርባቸዉ ሁሉን አቀፍ ስብሰባዎች ናቸዉ።
በእነዚህ ስብሰባዎች ላይ ወያኔ ግምገማ ወይም ስልጠና እያለ እንደሚያዘጋጃቸዉ መድረኮች ካድሬዎች መመሪያ እየሰጡ ህዝብ ደግሞ ወደደም ጠላ መመሪያዎቹን ተግባራዊ የሚያደርግበት የአንድዮሽ መድረኮች ሳይሆኑ ህዝብ በአገሩ ጉዳዮች ላይ በሚወሰኑ ዉሳኔዎችና በተግባራዊነታቸዉ ላይ ቀጥተኛ የሆነ ተሳትፎ የሚያደርግባቸዉ የሁለትዮሽ መድረኮች ናቸዉ። በሃያ ስድስቱም ከተማዎች ላይ የሚሰበሰበዉ ህዝብ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይጠበቃል? ከምሁራን ምን ይጠበቃል? ከሴቶች ምን ይጠበቃል? ከወጣቶች ምን ይጠበቃል ለሚሉ ጥያቄዎች መልስ ይሰጣል። የኢትዮጵያ ህዝብ ከወያኔ ዘረኞች ጋር የሚያደርገዉ የሞት ሽረት ትግል በአንድ ምዕራፍ የሚገባደድ፤ በጥቂት ሰዎች የሚሰራ ወይም አንዱ ታጋይ ሌላዉ ገላጋይ ሆኖ የሚታይበት ትግል አይደለም። ይህ ትግል ብዙ ምዕራፎች ያሉት፤ እልፍ አዕላፋት የሚሳተፉበትና ሁሉም የየራሱን አስተዋጽኦ የሚያደርግበት የጋራ ትግል ነዉ። ግንቦት ሰባት ይህንን እዉነታ የሚረዳ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ወደእነዚህ ስብሰባዎች በብዛት በመምጣት በአገሩ የወደፊት ጉዳዮች ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግ አገራዊ ጥሪ ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ
እናሸንፋለን!!