Saturday 29 June 2013

የአብዬን ወደ እምዬ

ወያኔና ከወያኔ አፍ የሰሙትን ሁሉ እንደበቀቀን እየደጋገሙ የሚያነበንቡ ሎሌዎች የራሳቸውን መልክ የሚያዩበት መስታወት የተቸገሩ ይመስላል። ወየኔና ሎሌዎቹ እራሳቸውን ማየት ስለተሳናቸው ህዝብም ልክ እንደ እነሱ ኣራሱን የማያይና እነሱንና እኩይ ስራቸዉን የማያዉቅ እየመሰላቸው ሄዷል፡፡ ለዚህም ነዉ በግፈኛ አገዛዛቸው ተንገፍግፎ የሚቃወማቸውን ሁሉ ጥላሸት ለመቀባትና በራሳቸው ስም ለመጥራት ሲንጠራሩ የሚታዩት።
የወያኔ ዘረኞች የኢትዮጵያን ተቃዋሚ ኃይሎች በሙሉ በፀረ-ኢትዮጵያዊነትና የአገርን ጥቅም ለባዕድ አሳልፎ በመሸጥ ሲከስሱ ስንሰማ አይናቸዉንና ፊታቸዉን ታጥበዉ አይነ ደረቅ ለመመሰል ስንት ኪሎ ጨው እንደፈጀባቸዉ መገመት ያዳግታል።
በአገራችን ታሪክ ውስጥ እንደወያኔ በኢትዮጵያ ህልውናና በወሳኝና ዘላቂ ጥቅሞቿ ላይ የዘመተ ኃይል ኖሮም ተፈጥሮም አያውቅም። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጀግኖች አባቶቻችን አጽም ያረፈበትን መሬት በስጦታ ለጎረቤት አገር እናካችሁ ብሎ የሰጠ ማነዉ? ማነው በሽፍትነት ዘመኑ ለተደረገለት ውለታና ተቀናቃኞቹን እንዲጠብቁለት በማሰብ የኢትዮጵያን ድንበር እንደ ዳቦ እየገመሰ ለባዕዳን የሸጠው?
ማነው የገዛ ወገኑን ከአያት ቅድመ አያት አጽመ ርስቱ ላይ እያፈናቀለ አንድ ሲኒ ቡና በማይገዛ ገንዛብ ለምለም መሬታችንን ለባእዳን የሚያቀራምተው? ማነው በህዝብ ስም በልመናና በችሮታ የተገኘን ገንዘብ እየዘረፈ ከአገርና ከህዝብ ደብቆ የባእድ አገር ባንኮችን የሚያደልበው? ኢትዮጵያ በሶማሊያ በተወረረችበት በ1970ዎቹ አመታት የሞቃዲሾን ፓስፖርት ተሸክመው ይንጎማለሉ የነበሩት የዛሬዎቹ የወያኔ አለቆች መሆናቸውን የኢትዮጵያ ህዝብ ገና አልረሳዉምኮ!
የዛሬዎቹ የወያኔ መሪዎች ትናንት የኢትዮጵያን ሰላምና አንድነት ማየት ከማይፈልጉ የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች ጋር እጅና ጓንት ሆነዉ የኛን የጎሳ ድርጅት እስከረዳችሁ ድረስ ኢትዮጵያን እናደክምላችኋለን የሚሉ ጸረ አገርና ጸረ ህዝቦች ነበሩ።እነዚህ የለየላቸዉ ከሀዲዎች ዛሬ አይናቸዉን በጨው አጥበዉ እራሳቸዉን የኢትዮጵያ ጥቅም አስከባሪ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነትና ለአገር አንድነት መከበር የሚታገሉትን ዉድ የኢትዮጵያ ልጆች የአገር ጠላት ብሎ ለመጥራት የሚያበቃ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያክል የሞራል ብቃት የላቸውም።
ወያኔዎች ስልጣን በያዙ ማግስት በጻፉትና እነሱን ሲጠቅም በሚጠቅሱት አገርንና ህዝብን ሲጠቅም ግን እየዳጡ በሚያልፉት ህገመንግስት ዉስጥ ደደቢት በረሃ የወሰዳቸዉን ዋነኛ አላማ መገነጣጠልን እንደ አገር ጥቅም በጹሁፍ ካልሰፈረ ብለው ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ የነበሩበትን ጊዜ እኛ የኢትዮጵያ ነገር የሚቆረቁረን ወገኖች አልረሳነውም። ለመሆኑ ሌሎችን በጸረ-ኢትዮጵያዊነት የሚከሰው ወያኔ እውነት ኢትዮጵያን ከወደደ መገነጣጠልን ለምን ተመኘላት? መገነጣጠልን የመሰለ አደጋ እንደ ብሔራዊ የአገር ጥቅም አይቶ የራሱን ምኞት በህግመንግስት ደረጃ ያጸደቀዉ ወያኔ እንዴት ሆኖ ነው ለኢትዮጵያ አንድነትና ክብር የሚጋደሉና የሚታገሉ ልጆቿን በሀገር ጠላትነት የሚከስሰው? የኢትዮጵያ ህዝብ ከወያኔ ጋር የሚደረገዉን ትግል ከመብትና ከነጻነት ትግል ባሻገር እንደ አገር አድን ትግል አድርጎ የሚመለከተዉ ይህንኑ ወያኔ በአገራችን ብሄራዊ ጥቅሞች ላይ በተደጋጋሚ ያሳየዉን ጠላትነት በመገንዘብ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔ ተቃዋሚ ኃይሎችን በጅምላ የአገር ጠላት ለማስመሰል በሚቆጣጠራቸዉ የመገናኛ አዉታሮችና በታማኝ ሎሌዎቹ በኩል የጀመረዉን የስም ማጥፋት ዘመቻ ከወዲሁ ተረድቶ “የአብዬን ወደ እምዬ” ብሎ ትግሉን ከቀጠለ ዉሎ አድሯል። ወያኔና ለሆዳቸው ያደሩ ሎሌዎች ሁለመናቸውን የወረሰውን የፀረ-ህዝብና ጸረ ኢትዮጵያዊነት እከክ ማንም ላይ ማራገፍ አይችሉም። ድፍን ኢትዮጵያ ማንነታቸውን አሳምሮ ያውቃልና።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ስብሃት ነጋ “እውነት” ሲያዳልጣቸው

June 28, 2013
sebehat nega one of the founders of TPLF
ከኢየሩሳሌም አርአያ
ሽማግሌው ስብሃት ነጋ ከጥቂት ቀናት በፊት በሰጡት ቃለ-ምልልስ አስበውት ይሁን ሳያስቡት “እውነት” አምልጧቸዋል። አጥብቀው ያነሷቸው የሙስና ጉዳዮች ራሱን የቻለ “አላማና ግብ” አላቸው። የመጀመሪያው በፓርቲያቸው ውስጥ ያለው ክፍፍል (የጥቅም) እንደተዳፈነ እሳት ውስጥ ለውስጥ እየተብላላ መሆኑን በግልፅ ያሳያል። ከተናገሩት የሚከተለውን እንመልከት፤ “በጤናማ ሁኔታ የሚገኙ ሰዎችን እንቆርጣለን፣ እናስራለን ወዘተ እያሉ ሲያስፈራሩ የነበሩ የፖለቲካ፣ የመንግስት ሰዎች ነን የሚሉ የፀጥታና የስነ አእምሮ ሁከት ፈጥረዋል። መቶ ሚሊዮን የሰረቁና ያስዘረፉ፣ 10ሺህ ብር የሰረቀውን ሲያገላብጡት ያታያሉ።” ብለዋል። « እንቆርጣለን » ያሉት መለስ ዜናዊ ናቸው፤ መለስ በአደባባይ ይህን ከመናገር አልፈው ሲያስፈራሩም እንደነበር እናስታውሳለን። መለስ ያንን ያሉት በ10ሺዎች የሚገመት ቡና ከመጋዘን ጠፋ በተባለበት ወቅት ነው። ያንን ቡና የሰረቁትና ባህር ማዶ ሸጠው ገንዙቡን ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ምንጭ ተጠቅሶ ይፋ ተደርጓል። እናም ስብሃት “መቶ ሚሊዮን የሰረቁ..» ያሉት አዜብ መስፍንን ሲሆን፣ « ያስዘረፉ» ያሉት ደግሞ ባለቤታቸው አቶ መለስን ነው። « 10ሺህ የሰረቁ..» የተባሉት በቅርቡ የታሰሩት የጉምሩክ ሰዎችን ሲሆን..እነዚህን በንፅፅር ያስቀመጡት የአዜብ (ተላላኪዎች) ስርቆት መጠነሰፊ መሆኑን ለማመላከት ነው። ስብሃት እስካሁን አድፍጠው ቆይተው በዚህ ሰሞን ይህን መናገራቸው ..« አዜብ የከተማዋ ም/ል ከንቲባ ይሆናሉ» የሚባለውን በመስማታቸው ሆን ብለው ያደረጉት ነው፥ ይላሉ ታዛቢዎች። በተለይ ሽማግሌውን በቅርብ የሚያውቋቸው የፓርቲው ሰዎች « ስብሃት ከበረሃ ጀምሮ በቀለኛ ነው። ጥርሱ ውስጥ የገባን ሰው ካላስወገደ እንቅልፍ አይወስደውም፤ ብዙ ሰው አጥፍቶዋል። አሁንም አዜብን እግር በእግር የሚከታተለው ለዚሁ ነው» ይላሉ። በማስከተልም ፥ « ሙስና ከተነሳ ስብሃትም እስከአንገቱ ተነክሮበታል። በገርጂና ሳር ቤት የሚገኘው <ሉሲ አካዳሚ > በአሜሪካ በሚኖሩ ስጋ ዘመዶቹ ስም እንዲሁም በቀድሞ የአየር ሃይል ጄ/ል ሰሎሞን ስም የሚንቀሳቀስ ግን የስብሃት የግል ንብረት መሆኑን የማይታወቅ መስሎት ነው?….ጎንደር -ሑመራ ያለው የሰሊጥ እርሻ የስብሃት አይደለም?…በ10ሚሊዮን ብር በሚገመት በመቀሌ (አፓርታይድ መንደር) ስብሃት ዘመናዊ ቪላ እንደሚገነባ አይታወቅም ብሎ ይሆን?…» ሲሉ እነዚህ ወገኖች የስብሃትን ሙስና በከፊል ይጠቅሳሉ።
ስብሃት በዚህ አላበቁም፤ « ..እስካሁን ከፍተኛ ሙሰኞች ትንሹን ሙሰኛ ከሰው አሳስረው ያስፈርዱና ያሰቃዩ ነበር ይባላል። ከፍተኛ ሙሰኞች ከመርማሪው ጀምረው አቃቤ ሕጉም ዳኛው፣ ምስክሩም ይቆጣጠራሉ። ትንሽ የሰረቀም ምንም ያልሰረቀም ሲሰቃዩና ሲያደኸዩ የነበሩም፤ አሉም ይባላል። ስልክ እየደወሉም ይፈርዱ ነበር ይባላል።» ብለው አረፉት ስብሃት። ትክክል ናቸው!! ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ « ይህን ካልፈረድሽ በመኪና ገጭተን ነው የምንገድልሽ » ተብላለች። ያውም ከቤተ መንግስት ተደውሎ። አባተ ኪሾ ከደቡብ ባጀት ተመላሽ የሆነ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000) ለመንግስት ተመላሽ ሊያደርጉ ሲሉ …« ወዲህ በል..የምን መንግስት ነው?» በማለት ተቀብለው ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን አባተ ፍ/ቤት ጭምር ያጋለጡት ነው። ስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ደግሞ ታምራት ላይኔ በውሸት እንዲመሰክር አምስት ጊዜ አግባብተውት እንቢ ሲል ከማስደብደባቸው በተጨማሪ ሌላ ክስ እንዲመሰረትበት አድርገዋል። አቃቤ ሕግ የነበረው ዮሃንስ ወ/ገብርኤል የነስብሃትን የውሸት ክስ ተቀብዬ ተግባራዊ አላደርግም፤ ህሊናዬ አይቀበለውም .. በማለቱ ብቻ ለአምስት አመት እንዲታሰር አላደረጋችሁም?…ብዙ ማስረጃና መረጃ መደርደር ይቻላል።..
አሁን ስብሃት ተናገሩት እንጂ…ህዝቡ ብሎ-ብሎ የታከተው ነገር ነው!! እነ እስክንድር፣መሃመድ አቡበከር፣ አንዷለም አራጌ፣ ርእዮት አለሙ….ወዘተ በርሶ ጓደኞች በስልክ ትእዛዝ የተፈረደባቸው ናቸው!!… «ፍትሃዊ ስርአትና መንግስት አለ..» እያሉ ህዝብን የሚያደነቁሩት እነበረከትና የጋሪ ፈረስ የሆኑት ሃ/ማሪያም እርቃናቸውን የሚያስቀር ነገር ነው በስብሃት የተቀመጠው።

The Ethiopian Opposition: On Keeping the Momentum

June 28, 2013
by Teklu Abate
For the last two decades, the ruling party, EPRDF, set the agendas for political discourse, putting the opposition to a clear defensive position. The former drafted, ratified, and implemented rulings and laws solo several of which are calculated to contain and neutralize any form of public dissent. The opposition has had nothing to do about it but to mildly shout that the political playing field was and is too narrow to play. Discourses related to national economics and development were/are also the exclusive business of the ruling party. Moreover, it was/is the EPRDF only who re-defined/s our border lines and our relations to neighboring countries. The opposition reacted in some forms to such maneuverings. Generally, one could safely argue that the EPRDF and the opposition have respectively assumed their offensive and defensive roles for years.
The spirit of claiming natural and constitutional rights in EthiopiaVery recently, we happen to witness bits and pieces of developments that conjointly point to a different scenario where the opposition seem to manage to put their agendas on table. The public demonstrations called up on by the Blue Party last May just broke the silence. Although the event itself was neither an outcome nor an output, it was found significant in several ways. Several writers excellently lamented its implications and I also managed to outline some of the important lessons learnt from it in my May short commentary. Stated simply, the rallies could be considered an ice breaker; they effectively teared down that big blanket of fear and silence from the Ethiopian political horizon.
And that spirit of claiming natural and constitutional rights does not stop there. The Blues vow to come back to the streets again and again until their demands are met. They sort of have given the ruling party a three-month grace period to act. Moreover, the Unity for Democracy and Justice party (Andinet) are also coming to the fore again. They are planning rallies that are to take place in regional towns first and finally in Addis Ababa. Other parties and fronts might join hands and make serious and series of demonstrations that could put EPRDF at the defensive. If the regime does not effectively respond to the demands, the sizable rallies could have huge potential for bringing a massive and peaceful popular uprising that could be lethal to the ruling party. In a way, the refreshed demands of the opposition seem to appear a nuisance to the ruling party- they tend to defend this time around.
Before the opposition reach at that stage, a stage where they clearly and in a sustained way take the offensive position, they must identify and deal with a whole array of challenges and hurdles put forward by the EPRDF. The power of the opposition to maneuver and to bring their efforts in scale would define the trajectory of Ethiopian politics for years to come. The opposition (here I refer to those based in Ethiopia) need to regularly and well ahead of time reflect up on a host of challenges and issues.
Several writers created possible scenarios and offered recommendations. To me, if the opposition adequately, timely, in a sustained way, and at scale do or meet the following, success (genuine democratic governance, freedom, the rule of law, and justice) is very likely to come. The recommendations below relate to the content and method of peaceful struggle as well as the nature of leadership deemed appropriate for the time.
Injustice as the enemy
We know that the ruling party is behind the state of affairs wherein Ethiopia finds itself since 1991. Still, the enemy of the Ethiopian people is not EPRDF/TPLF as such. Any peaceful and meaningful political struggle must thus aim at combatting such real enemies as injustice, corruption, killings, nepotism, random detention, persecution, lack of freedom, backwardness, stagnation, unaccountability, and the like. If struggles aim at EPRDF as an entity, there would not be any guarantee that we would have democratic culture once the regime is gone. Plus, if struggles focus on the real enemies, those in the EPRDF circle might feel that they are not singled out and hence they might, after some time, decide to change their political lanes. This way, it is possible to create a future where the opposition, EPRDF sympathizers and members, and the general public live in peace and tranquility. This is what we could learn from Nelson Mandela of South Africa, to forgive for the sake of cohesion and lasting change. Fight to bring justice and freedom and not to liquidate a group.
National reconciliation
Yes, because of EPRDF’s policies and propaganda, we suffer a lot. We tend to look through ethnic lines only. We fought each other several times and thousands are gone forever. And many still languish in such earthly hells called Kaliti and maekellawi. And many have left their country to escape from everything. Despite all these, the opposition must tolerate and preach peaceful co-existence. Ethiopia should be home not only to those who fight to bring change but also to those who are very responsible for all the mess. That spirit of forgiveness must be at the core of any political struggle. We cannot bring lasting peace by killing or persecuting the oppressors but by forgiving them. Of course, those few at the top of the EPRDF power echelon might be held accountable to their deeds through a free and fair justice system. But a national reconciliation that includes all groups and parties and individuals is for sure a panacea for solving every other problem. And this is not a tried and tired approach in Ethiopia. The opposition could benefit if they consider this as an option.
Inclusiveness
Nearly all EPRDF seminars and conferences at home and in the Diaspora are reserved for supporters and members. That created the gulf between the regime and the populace in general. The opposition must be significantly different from the ruling party in this regards, too. Reconciliations, workshops, conferences, seminars, and other party moves must accommodate all. The youth, the elderly, the rural and urban population, the educated, the business people, EPRDF members and sympathizers, and the Ethiopian Diaspora need to be considered while planning, implementing, and evaluating programs or projects. If struggles are dubbed peaceful, there is nothing to hide from EPRDF people. By inviting them to opposition forums, it is possible to show transparency and accountability and to enter in to discourse. Let’s create that culture of debate as it is the opportunity to positively influence and be influenced.
Practical and strategic
To win the hearts and minds of the people, the opposition need to focus on the now and the future simultaneously. Problems and concerns include poverty and starvation, corruption, nepotism, lack of freedom of all sorts, imprisonment, exodus of the youth to the Arab world, scramble of our fertile lands by irresponsible investors, forced eviction of people, our border lines and relation with neighbors and internationally, and the like. The opposition must come up with their plans as to how to solve all these bottlenecks. The people want to see smarter solutions that outachieve EPRDF’s. Meaning, political struggle is as intellectual and discursive as it is pragmatic. This of course requires quality leadership and resource pool.
Competent leadership
Leadership plays a crucial role in bringing change. Unfortunately, we happen to see some of the most incompetent leaders in several of the political parties back home. They are usually made leaders based on family ties, ethnic considerations, seniority, and even gender. Some assumed leadership for decades and still claim that no one is competent enough to replace them. Others seem to ‘own’ political parties through infusing their private resources into party activities. They expect any decision to be made in accordance with their tastes. These kinds of guys should be stopped systematically. If the opposition aspire to succeed, they must make sure they are being led by some of the most competent workforce. People who do not have the knowledge, skill, know-how, and sincerity should not be allowed to enter the leadership rank. As they would retard and at worst divide the struggle. Youngsters must be recruited, trained, and given the opportunity to lead for a very fixed term.
Leadership contracts
Regularly but in a stable way changing leadership might work well in the Ethiopian context for several reasons. One, it would discourage long-time rule and dictatorship. Two, leading political parties cost a lot in terms of resources, time, energy, and other sacrifices including imprisonment and persecution and prosecution. Changing leadership regularly is tantamount to sharing the burden. Three, it would be a challenge to the ruling party to jail and prosecute all the generations of leaders. Four, it would send to the public a message that the opposition is governed by rules and limits. Five, leaders would not have the energy and time to create their own personal networks as they know that they would step down soon. Six, new leaders could perform with all their energy and competence. Seventh, this formula will produce a great number of experienced leaders in the end who could easily influence the public at various levels.
Involve the people
Ideally, parties are created by the people to the people. But once leaders assume their positions, the public is relegated to making financial contributions only. There is little opportunity to the populace to get involved in decision making and usually lack the means to ensure accountability and transparency of the leadership. To me, the people must be educated to lead themselves. A political awareness program should be created so that 1) people know their rights and obligations quite well, 2) people could defend themselves against injustices of all sorts, 3) people could continue the struggle even when their leaders are jailed or persecuted, 4) the governing party could not imprison the entire or majority of the population but to surrender to their demands or to step down. In fact, the opposition should work a lot on this as it is the absolutely powerful way of bringing, sustaining, and scaling up democratic governance and real changes in economic and social realms. This is the least tried approach in Ethiopia.
Democratic practices
Some parties complain that EPRDF is undemocratic and oppressive. This is true but they themselves are equally undemocratic and oppressive. The way they elect their members and leaders, the way they make decisions, and the way they relate to their members is hardly democratic most of the time. Several of the divisions among the parties could partly be explained by this cause. If they could not govern their small parties well, how are they going to rule over the great nation? Democratic culture seems to be checked by egoistic tendencies, ignorance, and stubbornness. It is hard to bring meaningful change if parties remain secretive, divisive, and autocratic.
Stay collaborative
Inter-party collaborations are crucial as they could ensure resource and spirit mergers. We happened to see fronts and forums that membered several political parties. But they did not bring the struggle to the next higher level. If lasting and inclusive change is to be brought about, there must be a genuine and lasting alliance of some sort. We observed that some parties were reluctant to officially recognize or endorse the rallies called by the Blue Party. Others finally decided to join hands. Although each party has its own plans and resources, failing to collaborate with other parties on issues of national importance is simply unexplainable. Parties could identify areas (e.g. staging rallies) where they could work together while staying near and dear to their own routines.
Networking
Peaceful struggle requires resources, patience, courage, and networking. Those parties back home need to jointly develop projects and communicate them to the Ethiopian Diaspora for support including possible funding. Supporting and funding joint projects is more efficient and easier than supporting each and every political party. Information and communication technologies could be used to reach the otherwise unreachable.
Final notes
I tried to highlight the issues and challenges the Ethiopian opposition need to deal with if they aspire to bring meaningful political change. I want to make several points in relation to that though. One, I am not saying that what I presented is the only magic formulas for success. Two, I am not claiming that the opposition do not know or enact them at all; am focusing on scalability and sustainability. Three, some of the points raised have sharp double-edges: they require change both from the opposition and the ruling party. Four, some of them require making sacrifices of some sort from opposition leaders and supporters. Fifth, some of them require time and investment before seeing any result. Lastly, one could be fairly certain that meeting the aforementioned qualities could bring genuine and lasting changes to the political scene in Ethiopia. The opposition must keep the momentum and put the ruling party at the defensive. That way, they could force EPRDF either to play free and fair or to leave the political scene for good.

Wednesday 26 June 2013

ማነዉ ፈሪዉ ተቀዋሚ ወይስ ህወሃት/ ኢህአደግ..

ሰላም ፍቅሬ / ከጀርመን
ሰሞኑን በ20/06/2013 በአሜሪካ ኮንግረስ በኮንግረስ ማን የተከበሩ ሚስተር ስሚዝ ኢትዮጵያ ከመለሰ በኋላ ፦የወደፊት ዲሞ ክራሲና የሰበአዊ መ ብት በሚ ል ርዕስ በተደረገዉ  የም ስክርነት ቃል ላይ የተከበሩ አም ባሳደር ያማ ማ ቶ በተቃዋሚ ዎች ዙሪያ ሲናገሩ በራሳቸዉ  ስለማይተማ መኑና ስለሚፈሩ ነዉ ብለዉ መናገራቸዉን አድምጠናል።
በዚህ ጉዳይ ብዙ ማለት ይቻላል ፤ ይሁንና ለዛሬ በቅርብ የሆኑትንና በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ ላተኩር።
እዉነት አምባሳደር ያማማቶ እንዳሉት ፍርሃት ያለዉ በተቀዋሚ ጎራ ነዉ ፤ በህወሃት አካባቢ ነዉ ፤ ወይስ አሜሪካ የኢትዮጵያ ጉዳይ እያስፈራት መጣጉዳዩን ለፖለቲካ ጠበብቶች እተወዋለሁ ።
እድሜ ለሰማያዊ ፓርቲ አምባሳደር ያማማቶ ከመናገራቸዉ በፊት ቀደማቸዉ እንጂ ሁሉንም ፈርታችሁ ነዉ ይሉ ነበር። አንድ ነገር አምባሳደር ያማማቶን ልጠይቃቸዉ ለመሆኑ ፍርሃት ዝም ብሎ ይመጣል? ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ  ህዝቡ ግንባር ግንባሩን እየተባለ ሲገደል ባያዩ እንኳን አልሰሙም ታዲያ አሁንስ ህወሃት ጥቅሞቹ እንዳይነኩበት ለ39 ዓመታት ያከማቸዉን የጭካኔ ልምድ የሰማና ያየ ለምን አይፈራ 
ግን እኮ አምባሳደር ያማማቶ እዉነታቸዉን ነዉ፤ ከፍርሃት ዉጡና ታገሉ ማለታቸዉ እንደሆነስ? ካለ ትግል ድል የለምና ከፍርሃት ወጥቶ መ ታገል የድል መሰረት በመሆኑ ጥቆማቸዉ ዋናና ጠቃሚ ጉዳይ ነዉና በጥሩ ጎኑ ብናየዉስ
የኢትዮጵያ መንግስት ለ8ዓመታት በግዳጅና በማስፈራራት ይዞት የቆየዉን የሰላማዊ ሠልፍ ፍቃድ ክልከላ ሳይወድ በግድ መፍቀዱን መንግስትና ሰማያዊ ፓርቲ ባሳዩት እንቅስቃሴ ለማወቅ ችያለሁ።
ሠማያዊ ፓርቲ የተከበሩ አምባሳደር ያማማቶ በዚሁ የምስክርነት ቃል ላይ የተናገሩትን አስቀድሞ ያወቀ ይመስላል። ምክንያቱም  ፓርቲዉ ምንም ፍርሃት ሳይገባዉ ህወሃት/ ኢህአደግን ብቻ እያስፈራራ ሰላማዊ ሰልፉን አድርጓል። ከሰልፉም ፍርሃቱ የቱጋ እንዳለ አሳይቷል።
ህወሃት/ ኢህአደግ ግን ይፈራል?።አዎ ይፈራል። ህወሃት ለምን ይፈራል? የስንቶች የንጹሃን ደም በእጁ አለ፣ሰንቶችን አስለቅሷል፣ ስንቶችን አሳብዷል፣ ስንቶችን የአልጋ ቁራኛ አድርጓል፣ ስንቶችን ንጹሃን ከመቃብር በታች አድርጓል። ስንቶችን በዘር መሰረታቸዉ አሳድዷል ፣ ከቦታቸዉ አፈናቅሏል፣ንብረታቸዉን ነጥቋል፣አለጥፋታቸዉ አስሯል። ስንት በኢትዮያውያን ህዝብ ስም የመጣ ሃብትና ንብረት ተበዝብዟል፤በዚህም ሰንቶች ህወሃቶች ሃብት አጋብሰዋል።እነዚህ ብቻ አይደሉም  ህወሃት የሰራቸዉ ሃጥያቶችና ወንጀሎች ብዙ ናቸዉ ።
ሌላ ህወሃት የሚፈራበት ነገር አለ ወይ? አዎ። ምን?ይህ ዘመን አምባገነኖችን ያንቀተቀጠ ዘመ ን መሆኑና አምባገነኖችን እረፍት መንሳቱ አንድ ቀን ለእነሱም እንደማይቀር ስለገባቸዉ ፤ በአረቡ አለም የወደቁት አምባገነኖች የነበራቸዉ ትጥቅ ከህወሃት ትጥቅ በላይ መሆኑና ያላዳናቸዉ መሁኑን ህወሃት ጠንቅቆ ስለተረዳ፤ በሌሎችም አገሮች ለምሳሌ በአሁኑ ወቅት በብራዚል እና በቱርክ ህዝብ ምን ሊያመጣ እንደሚችል ስለሚያስረዳቸዉና የህዝብን ብሶት መሳሪያ እንደማይገድበዉ ህወሃት ስለተማረ።
ታዲያ ምን ያስፈረዋል? ለምን አያስፈራ? ህዝቡ ትግሉን ወደ ከፍተኛ ደረጃ ካደረሰዉ ለህወሃት ትልቅ አደጋ ስለሆነ ነዉ ።
ህወሃትን አሁን የሚያስፈራዉ የኢትዮጵያ መኖር አለ መኖር ሳይሆን ፤ የዘረፉት ንብረት ፣ በፓርቲያቸዉ ስር ያለዉ  ግዙፍ የንግድ እንቅስቃሴና ሌሎች ሊያስጠብቋቸዉ የፈለጋቸዉን ፤ስዉር ዓላማዎቻቸዉን ሁሉ የሚጠራርግ ማዕበል እየመጣ መሆኑ ስለገባቸዉ ለምን አይፈሩም
አንዳንድ ተቀዋሚ ፓርቲዎች ሰማያዊ ፓርቲ አብረን ሰላማዊ ሰልፍ እንውጣ ባለ ጊዜ ምክንያት እየደረደሩ አስቸግረዉ ነበር ይባላል።ይሁንና አሁን ከሰልፉ በኋላ ፦ይህም አለ እንዴ ? ያሉ ይመስላል።አሁንም ትግሉን መደገፋቸዉና መጀመራቸዉ ይበል የሚያሰኝ ጅምር በመሆኑሊበረታታ ይገባል።መነሻዉ የትም ይሁን የት መጀመሩ በራሱ አበረታች ነዉ ።ከፍርሃት ወጥተዋል ማለት ነዉ።
አንድነት ፓርቲ የሚሊዬኖችን ድምጽ ለማስጠበቅ በሚል መነሳታቸዉን እየሰማን ሲሆን ይህም ማነዉ ፈሪዉ የሚለዉን ለማወቅ ጊዜዉ እየደረሰ መ ሆኑንና ሰላማዊ ትግሉ ሊቀጥል እንደሆነ ይታያል። እንግዲህ ህዝቡ ወደ ጨዋታዉ ሜዳ በመጠጋት ድጋፉን እንደሚሰጥ የሚጠበቅ ሲሆን፤መሪ አጣን ለሚሉም ቀጥተኛ መልስ መገኘቱ ታዉቋል።
ትግሉን ከግብ ለማድረስ ከፍርሃት ዉጭ  ሆኖ ስራን መፈጸም ይጠይቃልና ከሰማያዊ ፓርቲ ትምህርት መዉሰድ የበታችነት ሳይሆን ብልህነት ነዉ።ትምህርት ትልቅ ጉልበት ይፈጥራል፤ተጨማሪም የሞራል ዝግጅት ማድረግ ያስችላልና፤በዚህ ዙሪያ ቆራጥነትንና ሌሎች የልምድ ግብአቶችን መጋራት ጠቃሚ ነዉ እላለሁ።
ለራሳችን መ ፍትሔ የምናመጣዉ  በእርግጥ እራሳችን ነን፤ አንድ ትልቅ ነገር ለተቀዋሚ ዎች እመክራለሁ ። እርሱም  ከየዋህነት እንድንወጣ ። በየዋህነት ህወሃትን ማሸነፍ አይቻልም ። የህወሃትን የክፋት መጠን የሚመጥን እና የሚቋቋም የትግል ስልትና አቋም ይዞ መነሳት ህወሃትንም ላይቀርለት ወደ ፍጻሜ ያቀርበዋል።
የኢትዮጵያ ህዝብም  ፤ በአገር ዉስጥም  ሆነ ከሃገር ዉጭ  ያሉ ሁሉ ተገቢዉን ድጋፍ  ለትክክለኛና ለእዉነተኛ ተቃዋሚዎች በመ ስጠት ህወሃትን ከጫንቃችን ላይ እናዉርድ ፤በዚህም የእፎይታ ዘመናችንን እናፋጥን ። ካልሆነ ግን መንግስትም የራሱን ጥላ  ባየ ቁጥር ሰዉ ከሚገልና ቃሊቲ ከሚወረዉር፤ተቃዋሚም ፈርቶ በመንግስት ከሚያላክክ ፤ ህዝብም ፈርቶ የሚመራን አጣን እያለ ከሚያዝን፤ ትግሉ ይጀምር፣ይቀጥል፥ ለጥያቄዉ መ ልስ ይገኝ። ሁሉም  ከፍርሃት ይዉጣ ።
ኢትዮጵያ የነጻነት ፣የዲሞክራሲና የብልጽግና አገር ትሁን።ለራሳችንና ለትዉልዳችን ጥቅም ሲባል ቢያንስ ተቃዋሚዉ ከፍርሃት ይውጣ ። በመጨረሻም ፈሪዉ ማን እንደሆነ ይታወቅ።
አም ላክ ኢትዮጵያን ይባርክ 

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባዎ

• በሚኒስትር ማዕረግ ሦስት ምክትል ከንቲባዎች ይሾማሉ እየተባለ ነው
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣይነት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ በሚሾም አንድ ከንቲባና በሚኒስትር ማዕረግ በሚሾሙ ሦስት ምክትል ከንቲባዎች እንደሚመራ ምንጮች ጠቆሙ፡፡
ምንጮች እንደሚሉት፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ ለከተማው ከንቲባ ሆነው የሚሾሙት አቶ ድሪባ ኩማ ናቸው፡፡ አቶ ድሪባ በአሁኑ ወቅት የትራንስፖርት ሚኒስትር ሲሆኑ፣ መሰንበቻውን ከወቅቱ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ኩማ ደመቅሳ ጋር በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እየታዩ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
በሚኒስትር ማዕረግ የከተማው ቀጣዮቹ ምክትል ከንቲባዎች የሚሆኑት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሩ አቶ መኩርያ ኃይሌ፣ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበውና የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ናቸው ሲሉም ምንጮች ይገልጻሉ፡፡
ነገር ግን ወ/ሮ አዜብ በየትኛውም ቦታ መሾም እንደማይፈልጉ እየገለጹ መሆናቸውን ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ ሪፖርተር በዚህ የመዋቅር ለውጥና ሹመት ጉዳይ ማረጋገጫ ለማግኘት ለአዲስ አበባ ኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ጥያቄ ቢያቀርብም፣ እየተካሄደ ያለውን ሥራ በዝርዝር መግለጽ ባለመፈለጉ አልተሳካም፡፡
ምንጮች እንደሚያብራሩት፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ ቢሮዎችን በኃላፊነት የሚመሩት ዕጩ ተሿሚዎች በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ እንደሚሾሙ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ቻርተር የሚፈቅደው አንድ ምክትል ከንቲባ በመሆኑ፣ ከአንዱ ዕጩ ተሿሚ በስተቀር ሁለቱ ተሿሚዎች በምክትል ከንቲባ ማዕረግ እንደሚሾሙ አመልክተዋል፡፡
ምንጮች እንደሚገልጹት፣ ኢሕአዴግ መራሹ መንግሥት ይህንን ያደረገበት ምክንያት አዲስ አበባ ላይ የተጀመሩና በቀጣይ የሚጀመሩ የልማት ሥራዎች ሰፊ በመሆናቸው፣ ይህንን የሚሸከም የአስተዳደር የሥልጣን እርከን ማደራጀት ያስፈልጋል በሚል ነው፡፡
የአዲስ አበባ ኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጀማል ረዲ መዋቅሩንና አሿሿሙን ባይገልጹም፣ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሚያስተዳድረው የሰው ኃይል በከፍተኛ ደረጃ እየተዘጋጀ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
አዲስ አበባ ከተማ በማደግ ላይ ያለች ከተማ ብትሆንም፣ በከተማዋ ውስጥ አፋጣኝ ምላሽ የሚፈልጉ ጥያቄዎች በርካታ ናቸው፡፡ ኅብረተሰቡ አምርሮ ከሚጠይቃቸው ጥያቄዎች መካከል የመኖርያ ቤት እጥረት፣ የኑሮ ውድነት፣ የመጠጥ ውኃ አቅርቦት ችግር፣ የትራንስፖርት እጥረትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ተጠቃሾች ናቸው፡፡
የከንቲባ ኩማ ደመቅሳ አስተዳደር እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የተለያዩ ተግባራትን ቢያከናውንም አዲስ አበባውያን ሊረኩ አልቻሉም፡፡ ኢሕአዴግ የኅብረተሰቡን ችግሮች ለመቅረፍ መወሰኑን በሚያመለክት ደረጃ ለአዲስ አበባ ከተማ ትኩረት እየሰጠ እንደሆነ በተለያዩ ጊዜያት ይናገራል፡፡
ኢሕአዴግ ከፍተኛ አመራሮቹን ከፌደራል ወደ አዲስ አበባ በሚያዝያ ወር በተካሄደው ምርጫ አማካይነት ቢያዛውርም፣ በእነዚህ ሹማምንት ምክንያት የተፈጠረውን የፌዴራል መንግሥት የአመራር ክፍተት የመሙላት ሌላ የቤት ሥራ ይጠብቀዋል፡፡
ethiopian reporter

“ምስጢር ካወጣህ ቤተሰቦችህን እንፈጃቸዋለን”

“ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል”
tesfaye


“የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል”
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ በዝዋይ እስር ቤት ለወራት ስቃይ የተፈፀመበት
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ይባላል፤ አርሲ አርባ ጉጉ ተወልዶ አዳማ/ናዝሬት አድጎ፣ በ1998 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ተመርቋል፡፡ በ2000 ዓ.ም በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር በሲኒየር ካልቸራል ኤክስፐርትነት የስራ መደብ እስከ ሚያዝያ 2003 ሰርቷል፡፡ ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በግልፅ ባልተረዳው ምክንያት የመንግስት ደህንነት ሀይሎች ተይዞ ለ23 ወር በዝዋይ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየተፈፀመበት መቆየቱን ይናገራል፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከእስራት ሲለቀቅም አንድ ጊዜም እንኳን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ከወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ጋር ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉን፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ማን ነበር ያሰረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በማለዳ ቤቴ ተንኳኳ፤ ተነስቼ ከፈትኩኝ፡፡ የማላውቃቸው ሰዎች ናቸው፡፡ “ና ውጣ፤ ልብስህን ለብሰህ ውጣ” አሉኝ፡፡ እኔ እናቴ ሞታ ሊያረዱኝ የመጡ መስሎኝ “ምነው ቤተሰብ ደህና አደለም? የተፈጠረ ችግር አለ?” አልኳቸው “ዝም ብለህ ናውጣ” አሉኝ፡፡ ልብሴን ለበስኩኝና ወጣሁ፤ አንቀው መኪና ውስጥ ከተው ወደ ማዕከላዊ ወሰዱኝና 3 ወር አሰሩኝ ከዛም አንድ አመት ከ8 ወር ዝዋይ ማረሚያ ቤት፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- መታሰርህን ለቤተሰብ ተናግረሀል?
ወጣት ተስፋዬ:- ለማንም ሰው እንድናገር አልፈቀዱልኝም፤ መስሪያ ቤቴ አልጠየቀኝም፣ ደሃዋ እናቴ ያለችው ናዝሬት ነው እሷም የምታውቀው ነገር አልነበረም፡፡ አባቴ አቶ ተካልኝ አስተማሪ ነበር አርባ ጉጉ ላይ ነው በ1985 ዓ.ም በነበረው ግጭት ነው የተገደለው፡፡ ማንም ሳይጠይቀኝ፣ፍ/ቤት ሳልቀርብ 23 ወር ታሰርኩ ልብስ ምግብም የሚያመጣልኝ ሰው አልነበረም፡፡ እናቴም መታሰሬን እንኳ አታውቅም መስሪያ ቤቴም ስኮላርሽፕ አግኝቷል፤ ወደ ውጪ ሃገር ሊማር ሊሄድ ነው የሚባል ነገር ስለነበረ አልጠየቁኝም፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- የት ነበር ስኮላርሺፕ ያገኘኸው?
ወጣት ተስፋዬ:- የዛሬ 2 ዓመት አካባቢ የራስመስ ሙንደስን ስኮላርሽፕ አግኝቼ ነበር፡፡ ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ካሊፎርኒያና ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ቶክዮ ባሉ ምሁራን ሪኮመንድ ተደርጌ በጣሊያኑ ፌራሪ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ተዘጋጅቼ ነበር፡፡ እንደተፈታሁ ሄጄ ስጠይቃቸው ብዙዎቹ ጓደኞቼ በጣም ደነገጡ፡፡ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ቅማል ተወርሬ … ባካችሁ ተውኝ … ምንም የሌለ ነገር የለም በጣም ተጎድቻለሁ፡፡ ከማረሚያ ቤት እንደወጣሁ እናቴ ጋ ስሄድ በጣም ደነገጠች፣ በሕይወት ያለሁ አልመሰላትም 23 ወር ሙሉ ከቤተሰብ ስለተለየሁ ግራተጋባች፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- በእስር ወቅት የደረሰብህ ድብደባና ማሰቃየት ነበር?
ወጣት ተስፋዬ:- ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብኛል፡፡ በኤሌክትሪክ ጀርባዬ ላይ አቃጥለውኛል፣ በብልቴ ላይና በኩላሊቴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ስላደረሱብኝ ሽንት ችዬ አልሸናም፣ ሽንቴን መቆጣጠርም አልችልም፡፡ ኩላሊቴንም በጣም ያመኛል፡፡ ውሃ ውስጥ እየነከሩ በጣም ደብድበውኛል፡፡ አሁን ስናገር ያመኛል ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- እንደው ስታስበው ለእስር ያበቃህ ወይም ከመንግስት ጋር ያጋጨህ አጋጣሚ ነበር?
ወጣት ተስፋዬ:- መስሪያ ቤቴ ውስጥ የኢህአዴግ አባላት ነበሩ፤ በጣም ይከታተሉኛል፡፡ በቢ.ፒ.አር ላይ ስብሰባ በተደጋጋሚ ይጠራ ነበር፡፡ እኔም ሠራተኛ ላይ ተፅእኖ የሚያደርሱ ነገሮች ሲመጡ እኔ አልቀበልም በግልፅ እናገር ነበር፤ ሠራተኛውም እኔን ይደግፋል፡፡ ከመታሰሬ ጥቂት ጊዜ በፊት ገነት ሆቴል ስብሰባ ነበረን፡፡ በዛ ስብሰባ ላይ በጣም ተከራከርኩ፤ ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር አቶ ፀጋዬ ማሞ የሚባሉ አሰልጣኝ፣ ከውጭ ጉዳይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲና ከንግድና ኢንዱስትሪም የመጡ ነበሩ ስማቸውን የማላስታውሳቸው ባለስልጣን ነበሩ፤ እዛ ላይ ሀሳብ አንስቼ ተከራክሬ ነበር፡፡ “የሠራተኛን ሀሳብ ዳይቨርት ያደርጋል” ይሉኝ ነበር፡፡ መቼም ግን ሀሳቤን በመናገሬ ይህን የመሰለ ስቃይ ይደርስብኛል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ “አሸባሪ፣ ግንቦት ሰባት” እያሉ እኔ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ፍርድ ቤት ሳልቀርብ ያለምንም ፍርድ በርሜል ውስጥ ውሃ ጨምረው እያስተኙ አሰቃዩኝ፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- እንደዚህ ያሰቃዩህ ምን አይነት ምንም አይነት መረጃ ሳያገኙ ነው?
ወጣት ተስፋዬ:- እኔን ጥፋተኛ የሚያስደርግ ምንም መረጃ አላገኙም፣ እኔን አስረው ወደ መስሪያ ቤት በተደጋጋሚ ይደውሉ እንደነበር ይነግሩኝ ነበር፡፡ የኢሜይል አድሬሴንም ተቀብለው በርብረዋል ግን ምንም አላገኙም፡፡ እኔ ከማንም ጋር ሊንክ የለኝም ኢሜሌ ላይ የስኮላርሺፕ መልዕክት ካልሆነ በስተቀር ምንም የለውም፡፡ በመስሪያ ቤቴ ሪሰርቸር ነበርኩ፣ በሶሲዮሎጂ ነው የተመረኩት፡፡ ሉሲ የተገኘችበት ሣይት ላይ አፋር፣ ጋምቤላ ብዙ ሳይቶች ሰርቻለሁ፡፡ ከአለቆቼ ጋር ያለኝ ግንኙነት ሰላማዊ ነው እነሱ ናቸው ስኮላርሽፕ ሪኮመንድ ያደረጉኝ፡፡ አንደኛው ፕሮፌሰር 25 ዓመት ሙሉ እዚህ አገር ሰርቷል፣ አርዲን ያገኘው እሱ ነው፡፡ ሄነሪ ጊልበርት ይባላል፤ እሱም ሪኮመንድ አድርጎኛል፡፡ እኔ በጣም የሚቆጨኝ ደሃዋ እናቴ አረቄና ጠላ ሸጣ ነው ያስተማረችኝ ምን ብዬ ልንገራት እንደዚህ አትጠብቀኝም ከበደኝ፣ አሁን እሷ የምትሰጠኝ ምግብ ራሱ ደምደም አለኝ… (ረጅም ለቅሶ)፡፡ ልጄ በደህናው አይደለም የጠፋው ሞቷል ወይም መኪና ገጭቶታል ብላ ነበር የምታስበው፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- የከመታሰርህ በፊት ፖለቲካ ተሳትፎ ነበረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- 1997 ዓ.ም የቅንጅት ደጋፊ ነበርኩ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበርኩ በ97 የነበረው ሁኔታ ስንት ሰው አለቀ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ነበር ታውቃላችሁ ምንም የምናደርገው ነገር አልነበረም ፡፡ በምርጫ አሸንፎ ሥልጣን መያዝ እንደማይቻል ተረዳሁኝ፡፡ ከ1997 ዓ.ም በኋላ የማንም የፖለቲካ ፓርቲ አባል አልሆንኩም፡፡ ከዚህ በኋላ ከምንም ነገር የተገለልኩ ሆኛለሁ፡፡ አንድ ብርጭቆ ሳትሰብር አሸባሪ ስትባል አስብ እንግዲህ አንድ ብርጭቆ እንኳን ሰብሬ አላውቅም ባለኝ እውቀት እንደውም ለእውቀት ነው የምጓጓው እውቀቴን አሳድጌ አገሬን ለመለወጥ ነው የማስበው እኔን ምንም የሚመለከተኝ ነገር የለም አሸባሪም ግንቦት ሰባትም አይደለሁም፡፡ስትደበደብ፣ ስትሰቃይ ያላደረከውን አድርጌያለሁ ትላለህ፤ በርሜል ውሃ ሞልተው ይከቱሃል ያሰቃዩሃል፡፡ አያሳዝንም ይሄ? እንዴት አድርጎ እዚህ አገር ይኖራል? 23 ወር ሙሉ አስረው ማሰቃየታቸው ሳያንስ የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል፡፡ እኔ ግን ከዚህ በላይ ሞት የለም ብዬ ነው የነገርኳችሁ፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- አሁን የት ነው የምትኖረው?
ወጣት ተስፋዬ:- መኖሪያ የለኝም … (ረጅም ለቅሶ)
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝን ለመርዳት የምትፈልጉ አንባብያን ከፍኖተ ነፃነት መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ (ምንጭ ፍኖተ ነጻነት)

Tuesday 25 June 2013

ባለ ሀገር እስከምንሆን ትግሉ ይቀጥላል

ሳምንቱ በስራ ውጥረት ሽው ብሎ እንዳለፈ ያወቅሁት እሁድ ማለዳ ከቤተሰቤ ጋር ሳሳልፍ ነው፡፡ ሳምንቱንም ሙሉ ትኩረት ሳልሰጣቸው በምትኩ ሃገራዊ ሃላፊነቴን አቅሜ በፈቀደው መጠን ለመወጣት በርከት ያለውን ጊዜ እንደሰጠሁ የገባኝም እሁድ እለት ነው፡፡
እንደዚህ ‹‹ቢዚ›› ያደረገኝ አንድነት ፓርቲ ሕዝባዊ ንቅናቄውን ይፋ ከማድረጉ በፊት ማለቅ የሚገባቸው በርከት ያሉ ተግባራት ስለነበሩን ነው፡፡ እነዚህን ተግባራት ከትግል አጋሮቼ ጋር የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሞት እንዲውጣቸው ስናጣፍጥ ሰነበትን፡፡ ሰንብተንም በእለተ ሐሙስ የሃገር ውስጥና የውጭ ጋዜጠኞች በተገኙበት ይፋ አደረግን፡፡ ባለ ሃገርነታችንን የነጠቀንን የፀረ-ሽብር ህጉንም ለማሰረዝ በይፋ ‹‹የሚልዮኖች ድምፅ ለነፃነትን›› አበሰርን፡፡ በግልፅም ሚሊዮኖች የሚሳተፉበት ንቅናቄ በግልፅ ተጀመረ፡፡
ይሄ ሁሉ የሚሆነው ለምንድነው? አዎ! ይሄ ሁሉ እየተደረገ ያለው ባለሃገር ለመሆን ነው፤ ከምንደኛነት (ተመፅዋችነት) ለመላቀቅ ነው፣ የሁላችንን ሃገር ኢትዮጵያን ለመፍጠር ነው፣ አንገታችንን ቀና አድርገን ለመሄድ ነው፣ እውነተኛ ልማት ለማ ምጣት ነው፣ አምባገነንነትን፣ ሙሰኝነትን፣ ጉልበተኝነትን ለመታገል ነው፤ በነፃነት የኖረችውን ሃገር ነፃነት ለማረጋገጥ ነው፣ መንግስትን ላለመፍራት ነው፣ ሃሳብን በነፃነት መግለፅ እንዲረጋገጥ ነው፤ የእምነት ነፃነት እንዲረጋገጥም ነው፡፡ በአጠቃላይ በሰጪና ነሺ የተዋቀረውን አገዛዝን ለማስተማር ነው፡፡ ይሄ ማለት ባለ ሃገር ለመሆን ነው፡፡
ሃገሩ የኔ ነው፡፡ ሃገሩ የእኛ ነው፡፡ የሁላችን፡፡ ሁላችንም ላባችንን የምናንጠፈጥፍበት፣ አባቶቻችን ደማቸውን ያፈሱበት እኛም ደማችንን ለማፍሰስ የማንሰስትባት ኢትዮጵያ የሁላችን ናት፡፡ የህዝባዊ ንቅናቄው ዓላማም ይሄ ነው፡፡ ብዕር ነጣቂ መንግስት ያላት ሃገር ጉድፏን እንዴት ታያለች? ስለ ኢትዮጵያ ገዥ ሃይል ብእር ነጣቂነት እማኝ ለመጥራት ሩቅ አልሄድም፡፡ ከተወዳጁ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጋር ሃሳባችንን እንዳንገልፅ ብእር ከተነጠቅነው መካከል ነኝ፡፡ በተወዳጇ ፍትህ ጋዜጣ አዲስ ታይምስና በኋላም ልእልና የጋዜጠኞች ብእር ተነጥቆ በጉልበት እስከሚዘጉ ድረስ በአምደኝነት ፖለቲካዊ ፅሁፎችን ጫጭሬያለሁ፡፡ ከብእር ነጠቃው በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ የፃፍኳት ፅሁፍ ይቺ ናት፡፡ የተነጠቀውን ብእር ማስመለስ የምንችለው በትግል ብቻ ነው፣ ባለ ሃገር ስንሆን ብቻ ነው፣ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ስንፈጥር ብቻ ነው፡፡ መፍትሄው ይሄው ነው፡፡ የፖለቲካ ትግል፡፡
ስለዚህ በአንድነት ፓርቲ በኩል ይፋ የተደረገ ሕዝባዊ ንቅናቄ አንድምታው ብዙ ነው፡፡ ባለ-ሀገር ለመሆን ለምንፈልገው ወሳኝ የትግል ምዕራፍ ነው፡፡ ምንደኛ ላደረጉንና ለማድረግ ለሚፈልጉት ሃይሎች ደግሞ ህመም ነው፡፡ ለህመምተኞች የሚያም ህመም፡፡ ኢትዮጵያን አጥብቀን ለምንወድድ ሁሉ ግን ብስራት መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል፡፡
የአንድነት ፓርቲ ህዝባዊ ንቅናቄ ካመማቸው የስርዓቱ ጥገኞች መካከል ሚሚ የተባሉት ግለሰብ አንዷ ናቸው፡፡ ሚሚ ስብሃቱ የተባሉት ሴትዮ የእሁድ ረፋድ ክብ ጠረጴዛ በተባለው ፕሮግራማቸው የፀረ-ሽብር ህጉን ለማሰረዝ የሚደረገውን ህዝባዊ ትግል እንደተለመደው ጥላሸት ለመቀባት ጥረት ሲያደርጉ ነበር፡፡ ሚሚ የተባሉት ግለሰብ ፕሮግራማቸው ሚዛናዊነት የጎደለውና ዘላፊ መሆኑ በአደባባይ የሚታወቅ ቢሆንም አንዳንድ ሰዎችን ለማደናገር ይችል ይሆናል፡፡ ሚሚና አፈ-ቀላጤዎቻቸው ‹‹ለምን የፀረ-ሽብር ህጉ ይሰረዛል፤ እንዴውም መጠናከር አለበት…›› በማለትና እንደ አለቆቻቸው አንድነትን ባልዋለበት ለማዋል መቁረጣቸው የፀረ-ሽብር ሕጉን እየጠቀሱ አፈናውና ነፃነት ገፈፋው እንዲቀጥል ያላቸውን ጥልቅ ምኞት ሲገልጡ ነበር፡፡ እኛ እያልን ያለነው ሁላችንም በነፃነት እንኑር ነው፡፡ ሁላችንም ባለ ሀገር እንሁን ነው፡፡
የሚሚና ቀላጤዎቿ ስህተት የፀረ-ሽብር ህጉ ከህገ-መንግስቱ ጋር ስንት ጊዜ እንደሚጋጭ አለማወቃቸው ነው፡፡ በአንድ በኩል ህገ-መንግስቱ ተናደ እያሉ ሲናገሩ የነበሩ ህገ-መንግስት የሚጥስ ህግ ምን ይሰራላቸዋል? ይሄ ህግ እየተጠቀሰ አንገታችንን እንድንደፋ የተደረግን ኢትዮጵያውያን ይሄ ህግ እንዲሻር እንታገላለን፡፡ ሁላችንም ባለ ሀገር እስከምንሆንም ትግሉ ይቀጥላል፡፡፡

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንቱ ስራ የሚ ለቁ ዳኞች ቁጥር መጨመሩን ተናገሩ

ሰኔ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና :-የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ተገኔ ኔታነህ ሰሞኑን ለፓርላማ የመ/ቤታቸውን የ11 ወራት ሪፖርት
ባቀረቡበት ወቅት  ዳኞች በርካታ ችግሮች የተጋረጠባቸው በመሆኑ መስሪያቤቱን እየለቀቁ ነው ብለዋል።
የዳኞች መኖሪያ ቤት ችግርን በዘለቄታነት ለመፍታት ሕንጻ ለመገንባት እየተደረገ ያለው ጥረት የተወሰነ መጓተት እንደሚታይበት ፕሬዚዳንቱ ጠቁመው እስከዚያ ድረስ እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ መንግስት የኪራይ ቤት መስጠቱን እንዲቀጥል የተላለፈውን ውሳኔ የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ተግባራዊ ባለማድረጉ ችግሩ ቀድሞ ከነበረበት ተባብሶ መቀጠሉን ፕሬዚዳንቱ  ገልጸዋል፡፡
የዳኞች እጥረትንም በተመለከተ አቶ ተገኔ ሲያስረዱ በዚህ ዓመት 58 ያህል ዳኞች በመሾማቸው የነበረውን የዳኞች
እጥረት በመጠኑም ቢሆን ለመቅረፍ የተቻለ ሲሆን ነገር ግን ቀደም ሲል በርካታ ዳኞች ፍ/ቤቶቹን የለቀቁ
በመሆናቸው ካለው ፍላጎት አንጻር በቂ ሆኖ አልተገኘም ብለዋል፡፡
በተለይ በድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች በኩል እያጋጠመ ያለው ፍልሰት ከፍተኛ ችግር መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡ ብዙዎቹ ሰራተኞች ስራ የሚለቁት በሚሄዱበት መ/ቤት የተሻለ ደመወዝና ጥቅማጥቅም በተለይም የሰርቪስና ሌሎች አገልግሎቶች በማግኘታቸው ነው ያሉት አቶ ጌታነህ በለቀቁ ሰራተኞች ምትክ ሰራተኛ ለመቅጠር የሚደረገው ሙከራ አብዛኛውን ጊዜ አይሳካም ሲሉ ምሬታቸውን ለፓርላማው
አስረድተዋል፡፡
ብዙዎቹ በክፍት ቦታዎች በሚወጡ ማስታወቂያዎች መሰረት ተወዳድረው ማሸነፋቸው ከተገለጸላቸውና የሐኪም ማስረጃ እንዲያቀርቡ ከተነገራቸው በኋላ በዚያው ነው የሚቀሩት ሲሉ ገልጸዋል፡፡
በማስቻያ ቦታና በቢሮ ጥበት በኩል ያለው ችግር አሁንም አለመቃለሉን ጠቅሰው እንደ አብነት የፌዴራል ከፍተኛው ፍ/ቤትን አንስተዋል፡፡ በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 33 ችሎቶች ተቋቁመው አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን ለነዚህ ችሎቶች መጠቀሚያ የሚያገለግሉ 15 የማስቻያ አዳራሾች ብቻ ናቸው፡፡ በዚህ ምክንያት ችሎቶች በፈረቃ ለመስራት ተገደዋል፡፡ ይህም ዳኞችን በሙሉ አቅማቸው እንዳይሰሩ ከማድረጉም በላይ ባለጉዳዮች እየተጉላሉ ነው ሲሉ
በሪፖርታቸው ጠቅሰዋል፡፡
ፍ/ቤቶች የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ፣መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን፣ለልማትና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ
እየተደረገ ባለው ጥረት ውስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ ችግሮቻቸው ሊቀረፉላቸው እንደሚገባ ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል፡፡
ብዙ ዳኞች በፖለቲካ ተጽኖ የተነሳ ስራቸውን በነጻነት ለመስራት ባለመቻላቸው ስራቸውን እንደሚለቁ የተለያዩ ጥናቶች ቢያመለክቱም፣ የፖለቲካውን ችግር ፕሬዚዳንቱ በሪፖርታቸው አላከተቱም። ኢትዮጵያ ውስጥ ነጻ የሆነ የፍትህ ስርአት አለመኖሩን በቅርቡ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ባወጣው አመታዊ ሪፖርት ላይ ተመልክቷል።

                  ESAT Daily News - Amsterdam June 25, 2013 Ethiopia


ምነዋ ማንዴላ!?

Former South African president Nelson Mandelaየግርጌ ማስታዎሻ : ከዘጠኝ አመት በፊት ያጣሁት አንድ ወንደም ነበረኝ ፣ ጋዜጠኛና ደራሲ መጽሐፈ ሲራክ የሚባል። መጽሐፈ የሃገር ፍቅር ልክፍቱን ብቻ አልነበረም ጥሎብኝ እስከ ወዲያኛው ያሸለበው ፣ የዘመናቸን ታላቅ የጥቁር ህዝብ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላን አበክሬ እንዳውቀው የረዳኝ ፣ ለነጻነት ክብር ለዲሞክራ ከቆሙት ጎን እንድቆም ፣ ሰብአዊ መብት ሲዳጥ ዝም እንዳልል፣ የግፉአንን ድምጽ እንዳሰማ የህይወትን ውርስ ያወረሰኝ ወንድሜ ለጥቁር ህዝብ አርበኛው ለኔልሰን ማንዴላ የነበረው ክብር ከፍ ያለ ነበር ! መጽሐፈ “ማንዴላ” እያለ በቀድሞው ለገዳዲ እና የኢትዮጵያ ራዲዮ ተወዳጁ የእሁድ መዝናኛ ተቀኝቶላቸውም ነበር ። ነፍሱን ይማረው እና ዛሬ ያ ወንድሜ በአካል ከእኛ ጋር የለም ! ማንዴላም ሁላችንም እሱ ወደ ሔደበት መጓዛችን ባንቀርም የታለቁ አባትን በጸና መታመም ስሰማ ወንድሜን አስታውሸ ፣ ማንዴላን ለማዘከር በፍጹም ስሜት “ምነዋ ማንዴላ ! ” ብየ ገጠምኩ !
በማለዳው . . .ሰኔ 2005 ዓ.ም June 24,2013 E.c ጅዳ ሳውዲ አረቢያ ተጻፈ
ከሰላምታ ጋር
ነቢዩ ሲራክ
ምነዋ ! ማንዴላችን ? !
ድምጽህ ቁርጥ ቁርጥ አለ አመመህ
ምነው ደከመህ በማረፊያህ ?
አፍሪካን ከአንባገንን ልጆቿ ጸድታ ሳታይ
ምነዋ መድከም ማሸለብህ ?
የኢትዮጵያን ስርየት ሳይበሰር
ምነዋ የመለየት ጉዞን መጀመርህ
ኢትዮጵያ ከደዌ ተላቃ ሳትጎበኛት
ምነዋ አትቀስቅሱኝ አልክ አንቀላፋህ ?
ምነዋ መልአከ ሞት ከበበህ
የስንብት መርዶ ጽልማሞት ግርማውን አለበሰህ
ምነዋ ጠንካራውን ጉልበትክን ፈተነብህ
የእማማን አፍሪካን ድህነት ማየቱ ታከተህ !
ምነዋ ማንዴላ?. . .

በረከት ስምኦን በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ እየዶለቱ ነው – (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

አቶ በረከት
በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ሊቀመንበርንት ከሚመራው ግንቦት ሰባት ጋር በተያያዘ በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ በረከት ስምኦን የሚመሩት የመንግስት አካል በምስጢር እየዶለተ መሆኑን ምንጮች ጠቆሙ። በቅርቡ በአንድ ድረገፅ ላይ የወጣውን የዶ/ር ብርሃኑን ንግግር በማስረጃነት ይዘው እየተንቀሳቀሱ ያሉት አቶ በረከትና ተከታዮቻቸው በአገር ውስጥ እየተንቀሳቅሰ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ « ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አለው፤ ከግንቦት ሰባት የገንዘብ ድጋፍ ይደረግለታል» በሚል እነበረከት ድምዳሜ ላይ መድረሳቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ የፓርቲውን አመራሮች «ከሽብረተኛ ቡድን ጋር በመገናኘት» ብለው ለመክሰስ ሴራ እያበጃጁ መሆኑን አስውታውቀዋል። የፓርቲው አመራሮችን ከማሰር ባለፈ «ሰማያዊ ፓርቲ በሽብርተኛ ድርጅት የሚረዳ ነው» በሚል በአገር ውስጥ የሚኖረውን የፓርቲው ቀጣይ ህልውና ለማክሰም ጭምር እየዶለቱ መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል። ከበረከት በተጨማሪ ደብረፂዮን ይህንን ሴራ በበላይነት እየመከሩበት እንደሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አሜሪካ ለሚገኝ አንድ ጋዜጠኛ ከገዢው ባለስልጣናት ዳጎስ ያለ ገንዘብ እንደተላከለት የቅርብ ምንጮች አጋለጡ። መጀመሪያ 250.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) ፣ በማስከተል 50.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) ሃዋላ እንደተደረገለትና ባጠቃላይ 300.00 (ሶስት መቶ ሺህ ብር) በዶላር ተመንዝሮ በእጁ እንደደረሰው ምንጮቹ ጠቁመዋል። ገንዘቡ ከነበረከት በኩል በምስጢር የተላከ መሆኑን ያጋለጡት ምንጮቹ በዚሁ መሰረት ጋዜጠኛው ለሕወሐት/ኢህአዴግ ማገልገል መቀጠሉንና በተለይ አሁን በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ እየተሸረበ ያለው ሴራ መነሻው ይህ ሰው እንደሆነ አያይዘው ገልፀዋል።

ቦይኮት (AESAONE)!

Boycott the illegitimate AESAONE festival
አገራችንን እና ህዝባችንን አንቆ ከያዘው ከዘረኛው (TPLF) አምባገነን ስርዓት ጋር እጅ እና ጓንት ሆነው በተፈጥሮ ሃብቷ የሚበለጽጉ ሙሰኛ ባለጸጎች (crony tycoons) በህዝባችን ላይ አየደረሰ ላለው ፍትህ ማጣት፤መንገላታት፤መቸገር፤መታሰር፤መፈናቀል እና ማንኛዉም አይነት ግፍ ከስርዓቱ እኩል ተጠያቂዎች ናቸው።
በንዋይ ሃይል ብልሹ ስነምግባራት ስንፈት፤ ዉሸት፤ ሌብነት፤ ሴሰኝነት ወዘተ (social decadence) በህዝባችን በተለይም በወጣቱ ትውልድ መካከል እንዲስፋፋ ምክንያት እየሆኑ ያሉ እነዚህ የበዝባዥ ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ስርዓት (Extractive Political and Economic System) ከበርቴዎች የምያካብቱትን ሃብት የጥቅማቸው ምንጭ የሆነዉን ስርዓት እድሜ ለማስረዘም ሲሉ በስፖርት ስም ወደ ዲያስፖራው የሚረጩትን የደም ገንዘብ እኛ የወገናችን ሰቆቃ የሚሰማን ኢትዮጵያዊያን አጥብቀን የምንቃዎመው እና የምንታገለው ነው።
ለሰላሳ አመታት ኢትዮጵያኖች ተንከባክበው ያቆዩትን የሰሜን አሜሪካ የስፖርት ፌዴሬሽን (ESFNA) ለስርዓቱ አገልጋይነት ለንዋይ ተገዢ ለማድረግ ሞክረው ያልተሳካላቸው ጥቂት ስብእናቸዉን ለገንዘብ ያስገዙ ግለሰቦች ህዝብን ለመከፋፈል ብሎም የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት ትግል አጋር የሆነውን ዲያስፖራ ኮሚኒቲ ለመቆጣጠር (AESAONE) በሚል ስም የሚያደርጉትን እኩይ ተግባር ወገኖቻችን በማወቅም ሆነ ባለማዎቅ እንዳይደግፉ ጥሪ እናቀርባለን።
ይህንን የህዝብ ጥሪ ችላ ብለው በዚህ ጸረ ህዝብ ድርጊት ላይ ለሚሳተፉ የንግድ ባለቤቶች ፤ የሙዚቃ ባለሙያዎች ወይም ማንኛዉንም አይነት ንግድ ከህብረተሰቡ ጋር የሚያካሂዱ ወገኖችን ተከታትለን የምናሳውቅ እና ማህበረሰባችን ትብብር እንዲነፍጋቸው (boycott) የምንጠይቅ መሆኑን አስቀድመን ማሳወቅ አንፈልጋለን።

Friday 21 June 2013

የአባይ ግድብ ዲፕሎማሲ አጀንዳ!

ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)

መሬታቸው የተወሰደባቸው ከ50-60 የሚጠጉ የመተማ አርሶአደሮች ጫካ መግባታቸውን ሲያስታውቁ ከ30 ያላነሱት ደግሞ ታስረዋል

ሰኔ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- በመተማ ዮሐንስ እና በኮኪት ቀበሌዎች የሚኖሩ አርሶአደሮች መሬታችን አድሎአዊ በሆነ መልኩ ለባለሀብቶች እየተሰጠብን ነው” በማለት ተቃውሞአቸውን ማሰማታቸውን ተከትሎ ጸረ ሽምቅ እና ልዩ ሀይል የሚባሉ የመንግስት ታጣቂዎች ከ30 ያላነሱትን የአካባቢውን ሰዎች ሲያስሩ፣ በታጣቂዎች ከሚፈለጉት መካከል ደግሞ ከ50- 60 የሚሆኑት አርሶደሮች ጫካ መግባታቸውን አስታውቀዋል።
ባለፉት ሳምንታት  አቤቱታቸውን አዲስ አበባ ተገኝተው ለም/ል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እንዲሁም በባህርዳር ለአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው ጎበዜ ካቀረቡት የህዝቡ ተወካዮች መካከል የተወሰኑት በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ፣ ሌሎች ደግሞ ጫካ መግባታቸውን የህዝቡ ተወካይ የሆኑት እና በአሁኑ ጊዜ ጫካ መግባታቸውን የገለጹት አንድ አርሶአደር ገልጸዋል።
የመንግስት ባለስልጣናት በዛሬው እለት 30 የሚሆኑ እስረኞችን ከመተማ አውጥተው ወደ ሌላ ቦታዎች ለመውሰድ ሲሞክሩ፣ የአካባቢው ህዝብ አናስወስድም በማለት ተቃውሞውን አሰምቷል። ይህን ዘገባ እሳከጠናከርንበት ጊዜ ድረስ በህዝቡና በመንግስት ባለስልጣናት መካከል የተፈጠረው ውዝግብ በምን ሁኔታ እንደተቋጨ ለማወቅ አልተቻለም።
በአሁኑ ሰአት ሽፍትነትን መርጠናል፣ ከማንኛውም የመንግስት ሀይል የሚመጣውን ጥቃት ለመመከት ተዘጋጅተናል” በማለት  አስተባባሪው ገልጸዋል ።
ከተያዙት መካከል ከህዝቡ ጋር አብራችሁ መንግስትን ወግታችሁዋል የተባሉ  ጥጋቡ አቸነፍ የተባለ የመተማ ወረዳ የሚኒሻ ኮማንደር እና ውብሸት የተባለ የቀበሌ ሹምም በቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግስት መሬት በብሎክ የመከፋፈል አሰራር ተግባራዊ ማድረጉን ተከትሎ  የአካባቢው ባለስልጣናት ለም የሆኑ መሬቶችን ለባለሀብቶች እና ለእነሱ ቀረቤታ ላላቸው ሰዎች ሰጥተዋል በሚል ተቃውሞ መቀስቀሱ ይታወቃል ።
የአካባቢውን ባለስልጣናትን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካም።

ዓባይና የአሜሪካ ጨዋታ

መስፍን ወልደ ማርያም
ሰኔ 2005
በአሥራ ዘጠነኛው ምዕተ-ዓመት አስተሳሰብ ከዚህ ቀጥሎ የተጠቀሰው ዓላማ ለአውሮፓ ቄሣራውያን ዋና ግባቸው ሆኖ እስከሃያኛው ምዕተ-ዓመት ዘልቆአል፤ አሀን ፈጽሞ በተለየ ዘመን አሜሪካ ይህንን አስተሳሰብ ይዞ የተነሣ ይመስላል።
ኢትዮጵያን የተቆጣጠረ ዓባይን ይቆጣጠራል፤ ዓባይን የተቆጣጠረ ግብጽን ይቆጣጠራል፤ ግብጽን የተቆጣጠረ ኃይልቀይ ባሕርን ከመግቢያና መውጫው ጋር ይቆጣጠራል፤ ቀይ ባሕርን ከመግቢያና መውጫው ጋር የተቆጣጠረ ኃይልዓለምን ይቆጣጠራል።
አሜሪካ በግብጽ ላይ የተከለው ጥፍሩ ሲነቃነቅ መነቀሉ አለመቅረቱን ስላወቀው ሌላ የሚተክልበት አገር ይፈልጋል፤ በአካባቢው የግብጽን ነፍስ የሚነካ ከኢትዮጵያ የተሻለ አገር የለም፤ ለአሜሪካ ዓለም-አቀፍ ዓላማ ኢትዮጵያ ስትመረጥ የአሁኑ የመጀመሪያው አይደለም፤ በመሀከለኛው ምሥራቅ የአረቦችን የተባበረ ኃይል ለመቋቋም የተመረጡ ሦስት አረብ ያልሆኑ አገሮች — ቱርክ፣ ኢትዮጵያና ፋርስ (ኢራን) — ነበሩ፤ በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የአሜሪካ ዓለም-አቀፍ ኃይል መሰማት በጀመረበት ጊዜ ኢትዮጵያን ከከበቡአት የአውሮፓ ቅኝ ገዢዎች ጋር የነበርዋትን የቆዩ ውዝግቦች ለመቋቋም የአሜሪካ ድጋፍ በጣም አስፈላጊ ነበር፤ አሜሪካን ከአውሮፓ አገሮች ጋር እየመዘኑና እያመዛዘኑ የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስከበር የተደረገው ዲፕሎማሲ (ዓለም-አቀፍ የሰላም ትግል) የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን መንግሥት በእውነት ከሚያኮሩት ተግባሮች አንዱ ነው፤ ይህንን ትግል አምባሳደር ዘውዴ ረታ ምስጋና ይድረሰውና የኤርትራ ጉዳይ በሚለው መጽሐፉ ግሩም አድርጎ አሳይቶናል።
ምናልባት ገና ያልተጠና ጉዳይ በዘመኑ ኢትዮጵያ የነበራት ታሪካዊ ክብር ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ታሪክና ዝና ጋር ተዳምሮ በአፍሪካ ተደማጭነት ነበራት፤ ይህንን ኢትዮጵያ በአፍሪካ አገሮች ላይ የነበራትን ጫና (የዛሬውን አያርገውና) በመጠቀም አሜሪካ አፍሪካን በሙሉ ለዓላማዋ ለማሰለፍ ኢትዮጵያን መሣሪያዋ ለማድረግ ትሞክር ነበር።
እየቆየ የኢትዮጵያ መንግሥት የነጻነት መንፈስን በማሳየት ለአሽከርነት አልመች በማለቱና ለአሜሪካም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች (የእውቀት ጥበቦች) በመፈጠራቸው ኢትዮጵያ ለአሜሪካ ዓለም-አቀፍ ዓላማ አስፈላጊነትዋ በመቀነሱ አሜሪካ ኢትዮጵያን ችላ ማለት ጀመረ፤ የ1966 ግርግር ከዚህ ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑን ጠለቅ ብሎ ማጥናት ያስፈልጋል፤ በዚህ መሀልም የሶቭየት ኅብረት ዓለም-አቀፋዊ ጉልበት እየተሰማ በመሄዱ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የነበረውን ዓላማ ቀስ በቀስ እየለወጠ ሄደ፤ ከዚህም ጋር የሶቭየት ኅብረት ተጽእኖ እያደገ ሄደ፤ የአሜሪካ አያያዝ እየላላ ሲሄድ የሶቭየት ኅብረት አያያዝ እየጠበቀ ሄደ፤ 1966 የአሜሪካ መውጫና የሶቭየት መግቢያ ሆነ ለማለት ይቻል ይሆናል፤ ከዚሁ ጋር አብሮ የሚታየው በኢትዮጵያ የባህላዊው ሥርዓት መሰነጣጠቅና የቆየው ትውልድ መዳከም ነው፤ የአሜሪካ መዳከም ሶቭየት ኅብረትን ሲያጠነክር፣ የአሮጌው ትውልድ መዳከም አዲሱን ትውልድ አጠነከረ፤ ይህ ማለት አሮጌው ትውልድ ከአሜሪካ ጋር የተያያዘውን ያህል አዲሱ ትውልድ ከሶቭየት ኅብረት ጋር ተያያዘ፤ የኢትዮጵያ የውስጥ ሁኔታ ብቻውን ለውጥ እንዳላመጣና ዓለም-አቀፍ ሁኔታዎችና የልዕለ ኃያላኑ ተጽእኖም ምን ያህል እንደነበረ አመላካች ነው።
የአጼ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት መውደቅና የአሜሪካ ተጽእኖ መዳከም በአንድ በኩል፣ የደርግ መፈጠርና የእነኢሕአፓና መኢሶን በአጋፋሪነት መውጣት ከሶቭየት ኅብረት ተጽእኖ መጠናከር ጋር በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ ሁኔታን ፈጠሩ፤ የአዲሱን ሁኔታ አዲስነት በግልጽና በትክክል መገንዘብ ያስፈልጋል፤ በኢትዮጵያ ለብዙ ሺህ ዓመታት ተከብሮና ታፍሮ የቆየው የዘውድ ሥርዓት ተናደ፤ ተዋረደ፤ በኢትዮጵያ ስር እየሰደዱ የነበሩ መሳፍንትና መኳንንት ከስራቸው ተመነገሉ፤ አዲስ የመሬት አዋጅ ወጣና የመሬት ከበርቴዎችን ሙልጭ አውጥቶ ገበሬውን በሙሉ እኩል ባለመሬት አደረገው፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ነጻ ወጣ ባይባልም የኢትዮጵያ መሬት ነጻ ወጣ፤ ወታደር፣ ገዢ ሰላማዊው ሕዝብ ተገዢ ሆነ፤ ትርፍ መሬትና ትርፍ ቤት ሁሉ ተወረሰ፤ ቤትን የሚያከራዩ የኪራይ ቤቶችና ቀበሌዎች ብቻ ሆኑ፤ ደሀዎችንና መሀከለኛ ገቢ ያላቸውን ሰዎች ኑሮ ለማቃለል ከሦስት መቶ ብር በታች የነበረው የቤት ኪራይ ሁሉ ተቀነሰ፤ ደርግ በሁለት ዓመታት ውስጥ የአብዛኛውን ገበሬ ኑሮና የአብዛኛውን የከተማ ነዋሪ ኑሮ የሚነኩ መሠረታዊ ለውጦችን አወጀ፤ እያደር ደርግ አስከፊ እየሆነና እየተጠላ ቢሄድም እነዚህ ሁለት አዋጆች ብዙ ኢትዮጵያውያንን እስከዛሬ ድረስ ለደርግ ባለውለታ አድርገዋል፤ እነዚህ አዋጆች ወያኔ ገና አፍርሶ ያልጨረሳቸው የደርግ ሐውልቶች ናቸው።
በውጭ አመራር ደግሞ የአሜሪካ ተጽእኖ ክፉኛ ተበጠሰ፤ አሜሪካ ማለት ስድብና ውርደት ሆነ፤ አሜሪካ ማለት በዝባዥነትና የቄሣራዊ ተልእኮ አራማጅ ማለት ሆነ፤ የአሜሪካ ማስታወቂያ ቢሮ ተዘጋ፤ ብዙ የአሜሪካ እንደወባ መከላከያ ያሉ የተራድኦ ድርጅቶች ተዘጉ፤ አሜሪካ ለዩኒቨርሲቲዎች ሲያደርግ የነበረውን እርዳታ አቋረጠ፤ በዚህ በተለይም የዓለማያ ዩኒቨርሲቲ በጣም ተጎዳ፤ የወባ ቢምቢም ከ‹‹ኢምፒሪያሊዝም›› ጭቆና ነጻ ወጣችና  አዲስ አበባ ደረሰች! ይባስ ብሎም አለማያ ዩኒቨርሲቲ ያፈራቸው አሉ የተባሉት በተለያዩ የእርሻ ሙያዎች የተካኑት አብዛኞች ሙልጭ ብለው ከአገር ወጡ።
አሜሪካ ከደርግ ጋር እየተጋገዘ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ክፉኛ አዳከመው፤ አያይዞም በኢትዮጵያ ዳር ዳር የሚነደውን እሳት አቀጣጠለው፤ በአንድ በኩል የውስጥ ተገንጣይ ቡድኖችን — የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት፣ የኤርትራ ነጻ አውጪ ድርጅት፤ የኦሮሞ ነጻ አውጪ ድርጅት — በሌላ በኩል በድንበርም ሆነ በሌላ ምክንያት ከኢትዮጵያ ጋር የሚፋለሙትን አገሮች ሶማልያንና ሱዳንን በግልጽ መርዳት ጀመረ፤ እንዲያውም ከግብጹ ፕሬዚደንት ሳዳት ጋር እየተመካከረ ኢትዮጵያን ለማዳከም ሞከረ፤ ከመሞከርም አልፎ ኤርትራን አስገነጠለ፤ የኢትዮጵያን ዙፋን ለወያኔ አመቻቸ፤ አሜሪካ ኮሚዩኒስት ነኝ የሚለውን ወያኔን በጎሣ ፖሊቲካ አስታጥቆ ቀለቡን እየሰፈረ በኢትዮጵያ ላይ ሠራው፤ ደርግ በሰይፍ ብቻ አንድነትን ለማምጣት መሞከሩና ሕዝቡን ለጦርነት ማነሣሣቱ አሜሪካንን አስደንግጦታል፤ ለአሜሪካ ደርግ የቀሰቀሰው የአንድነት ብሔራዊ ስሜት የኢትዮጵያን ድንበር አልፎ የሚፈስስ መስሎ ታየው፤ በዚህም ምክንያት የኢትዮጵያን የአንድነት ብሔራዊ ስሜት የማፈራረስ እቅዱን አወጣ፤ የሚያሳካለትንም ቡድን አገኘ።

ጣህሪር አደባባይና ዓባይ
ስንት ሰዎች በካይሮ ያለው አደባባይ ከዓባይ ጋር ግንኙነት አለው ብለው ያምናሉ? እስቲ ጠጋ ብለን እንመርምረው፤ ጣህሪር አደባባይ የግብጽ ሕዝብ የነጻነት ጥሪ ነበር፤ በአሜሪካ አጋዥነት ተጭኖት የነበረውን አገዛዝ ለማውረድ ቆርጦ መነሣቱን የገለጸበት አደባባይ ነው፤ የጣህሪር አደባባይን ማእከል ባደረገ ቆራጥ ትግል አገዛዙን አንኮታኩቶ አወረደው፤ በሰላማዊና ሕጋዊ ምርጫ የግብጽ ሕዝብ አዲስ መንግሥትን መሠረተ፤  የእስልምና ወንድማማቾች የሚባለው ቡድን አሸናፊ ሆኖ መውጣቱን አሜሪካም ሆነ እሥራኤል በጸጋ የተቀበሉት አይመስልም፤ ስጋት አላቸው፤ ለግብጻውያን ከአገዛዙ ጋር የሚወርድ ሌላ ጭነት አለባቸው፤ አሜሪካ ለራስዋም ዓላማ ሆነ ለእሥራኤል ዓላማ በግብጽ ላይ የምታደርገውን ከባድ ጫና ማንሣት ከትግሉ ዓላማዎች አንዱ ነበር፤ አሜሪካንና እሥራኤልን ያሰጋው የለውጡ ዓላማ አገዛዙን መጣሉ ሳይሆን በእነሱ ጥቅም ላይ ያነጣጠረውን ክፍል ነበር፤ በጦር መሣሪያ በኩል ግብጽ የአሜሪካ ጥገኛ ነች፤ ቀደም ሲል የሶቭየት ኅብረት ጥገኛ ነበረች፤ በአሁን በአለው የጊዜው ትርምስ አሜሪካ ግብጽ አንዳታመልጠው ይፈልጋል፤ ስለዚህም ስጋት አለው።
ግብጽን ሰንጎ ለመያዝና ለማስጨነቅ ከዓባይ የበለጠ ኃይል የለም፤ ዓባይን ሰንጎ  ግብጽን ለማስጨነቅ ከኢትዮጵያ  የበለጠ  ምቹ  አገር  የለም፤ በተጨማሪም ኡጋንዳን፣  ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን ከአሰለፈ ለአሜሪካ ሁኔታው ይበልጥ ይመቻቻል፤ ጫናው በግብጽ ላይ የጠነከረ ሊመስል ይችላል፤ አሜሪካ የግብጽን ወዳጅነት ለዘለቄታው ለማጣት ይፈልጋል? ለእኔ አይመስለኝም፤ አሜሪካ የአረቦችን ሁሉ ጠላትነት ይፈልጋል? ለእኔ አይመስለኝም፤ ታዲያ እስከምን ድረስ ነው አሜሪካ ግብጽን ለማስጨነቅ የሚፈልገው? ዋናው ጥያቄ ይህ ነው
ትልቁ የአስዋን ግድብ ሲሠራ የነበረውን ውዝግብና መካካድ ለማንሣት ይዳዳኛል፤ ግን ሰፊ በመሆኑ አልገባበትም፤ አንዳንድ ሁነቶችን ብቻ ልጥቀስ፡– የምዕራብ ኃይሎች በተለይም አሜሪካና ብሪታንያ ለግድቡ ሥራ አስተዋጽኦ ለማድረግ ቃላቸውን ከሰጡ በኋላ ሀሳባቸውን ለወጡ፤ የሶቭየት ኅብረት አንድ ቢልዮን ተሩብ ያህል ዶላር ለማበደር ዝግጁ ሆነ፤ ግብጽም ብድሩን ለመክፈል እንድትችል በዓለም-አቀፍ ኩባንያ ይተዳደር የነበረውን የስዌዝ ቦይ ብሔራዊ ሀብትዋ አድርጋ አወጀች፤ ይህንን በመቃወም ብሪታንያ፣ ፈረንሳይና እሥራኤል ግብጽን ወረሩ፤ በተባበሩት መንግሥታት ግፊት (አሜሪካና የሶቭየት ኅብረት በተባበሩት መንግሥታት መድረክ ላይ በአንድ ላይ የቆሙበት ብርቅ ሁኔታ ነበር፤) ወረራቸውን አቁመው ከግብጽ ወጡ፤ በኋላ ነገሩ ሁሉ ተገለባብጦ ግብጽ ሶቭየት ኅብረትን ትታ የአሜሪካ ወዳጅ ሆነች!
አሜሪካ የሶርያን ሳይጨርስ፣ የኢራንን ሳይጀምር ከግብጽ ጋር ውዝግብ ቢጀምር ምን ጥቅም ያገኛል? ደግሞስ በዓባይ ጉዳይ በኢትዮጵያና በግብጽ ውዝግብ የሚያሸንፈው አሜሪካ መሆኑ ያጠራራል ወይ? አሜሪካ ሲያሸንፍ ግን ከኢትዮጵያና ከግብጽ አንዳቸው ይወድቃሉ፤ ወይም ይቆስላሉ፤ ሁለቱንም እኩል አያቅፋቸውም፤ ደርግ አሜሪካንን በማስቀየሙ በአለፉት ሃያ ዓመታት በኢትዮጵያ መሬትና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ያስከተለው መዘዝ እያሰቃየን መሆኑን ልንረሳው አይገባንም
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያና በግብጽ መሀከል ያለው ጉዳይ አህያ ላህያ ቢራገጥ ዓይነት አይመስለኝም።