Sunday 28 April 2013

ኦባማ አርፍደው ወደ ኢትዮጵያ?


“በአፍሪካ ብዙ ስራ አለን” ጆን ኬሪ
በአፍሪካ ህብረት 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ከሚገኙት የተለያዩ እንግዶችና ባለስልጣናት በተጨማሪ አራት ታላላቅ መሪዎች እንደሚገኙ እየተነገረ ነው። በዋናነት የሚጠቀሱት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ኦባማ ሲሆኑ፣ የቻይና አቻቸውም ዋናውና ታላቁ እንግዳ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
1114የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ባለፈው ረቡዕ ለአሜሪካ ኮንግረንስ ኮሚቴ የተናገሩትን በመጥቀስ ዜናውን የላኩልን ክፍሎች እንዳሉት ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ ሊያመሩ ይችላሉ።
ውጪ ጉዳይ ሚ/ሩ ኦባማ ኢትዮጵያ ስለመሄዳቸው ፍንጭ ቢሰጡም ስለጉዞው ዝርዝር አለመናገራቸው ታውቋል። የቻይና በአፍሪካ ሚና መጉላት ውሎ አድሮ የጠዘጠዛት አሜሪካ፣ በመጪው ወር በሚካሔደው የአህጉሩ 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ በፕሬዚዳንቷ ለመወከል መወሰኗ “ጉባኤ አድማቂ” አሰኝቷታል።
“በአፍሪካ ብዙ የምንሰራው ስራ አለን” ሲሉ የተናገሩት ኬሪ “በድግሱ” ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል። እየተጣጣመ የመጣው የአፍሪካና የቻይና ፍቅር እንዲሁም ቻይና በአፍሪካ ያላት ሰፋ ያለ ኢንቨስትመንት ለአሜሪካ አሳሳቢ ከመሆኑ ባሻገር ቻይና የምትከተለው የንግድ ስልት በአጠቃላዩ ሁኔታ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩን ውጪ ጉዳይ ሚ/ር ኬሪ አልሸሸጉም፡፡ ዝርዝር ከመስጠት ቢቆጠቡም ጉቦ፣ ሙስና፣ አምባገነኖችን መርዳት በማለት የተወሰኑትን በግልጽ ከመጥቀስ አላለፉም፡፡
ኦባማም ወደ ኢትዮጵያ የሚያቀኑበት ጉዳይ አሜሪካ በአፍሪካ ለምትከተለው አዲስ እቅድ ማጠናከሪያ ካስማ ለመቸንከር እንደሆነ አብዛኞች ይስማሙበታል። “ቻይናን በቅርብ ሆኖ መቆጣጠር” በሚለው መርህ  የአፍሪካን አምባገነኖች ወታደራዊ ድጋፍ በመስጠት ልቡናቸውን የመስለብ እቅድ ይዛ እየሰራች ያለችው አሜሪካ፣ የቻይናና የአፍሪካ ግንኙነት “የፓለቲካ እባጭ” የሆነባት ቻይና ድፍን የአፍሪካ መሪዎችን ቤጂንግ ጋብዛ ወዳጅነቷን አደባባይ በማውጣት ጸሐይ ካስመታቸው በኋላ ነበር። በርካታ መረጃዎችም በዚሁ ዙሪያ ቀርበዋል።
በቤጂንጉ ጉባኤ ቻይና ዶላር ለሚናፍቁት የአፍሪካ መሪዎች ብድር ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ፣ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት፣ የቴክኖሎጂ፣ የመንገድ ግንባታ፣ የተለያዩ ርዳታዎች ለማድረግ፣ ከዚህም በላይ አምባገነኖች የስለላ መዋቅራቸውን እንዲያደራጁ የሚያስችላቸው በገሃድ እንዳይሰራጩ የተከለከሉ የአፈና መሳሪያዎችን ጭምር ለመስጠት ቃል ገብታ አፍሪካን የገበያዋ ሳሎን ስታደርግ አሜሪካና አውሮፓውያኖቹ ደነገጡ፤ ታመሙ።
በተመሳሳይ ቻይና ዘይትና የተለያዩ ማዕድኖችን ከአፍሪካ በመዛቅ የገበያ ድሯን ዘርግታ አፍሪካን ተጣባቻት። ዜጎቿንና የንግድ ተቋሞቿን አፍሪካ ምድር በትና ከላይም ከታችም ተቆጣጠረቻት። ከዚህ በኋላ ነበር መቀደሟ ያሳሰባት አሜሪካ ቻይናን በቅርብ መከታተል በሚል አዲስ ስልት የነደፈችው።
ባለሙያዎችና የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት አሜሪካ በኢኮኖሚና በገንዘብ ድጋፍ የአፍሪካን ሆዳም መሪዎች በማባበል ቻይናን ለመፎካከር በዛሬው ጊዜ አይቻላትም፤ በገሃድ እከተለዋለሁ የምትለውን ግብዝ ፖለቲካ ያበላሽባታል። እንደውም አታስበውም። ለዚህ ይመስላል የአፍሪካ አገሮችን ወታደራዊ ሃይል በማሰልጠን፣ በማደራጀት፣ በማስታጠቅ፣ የየአገራቱን ወታደራዊ እዝ ከበላይ ሆኖ በመምራት የቻይናን እንቅስቃሴ ለመበርበር የተንቀሳቀሰቸው። (ከዚህ በፊት “የኦባማ አስተዳደር መጪው የአፍሪካ ዕቅድ” በሚል የጻፍነውን እዚህ ላይ ይመልከቱ)
አምባገነኖች የመከላከያ ኃይላቸውን እንደ ብረት ለማጥበቅ ካላቸው የጸና ፍላጎት አንጻር አሜሪካ የነደፈችው ስልት የተዋጣለት እንደሆነ የሚናገሩ ክፍሎች “አሁን አሜሪካ ወታደራዊ ሃይልን ለማጠናከር በሚል ወደ አፍሪካ የገባችበት ስልት፤ ከአፍሪካ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እውቅና ውጪ የሚፈጸም ተግባር ስለሌለ መረጃ የማግኘት አቅሟ የቻይናን መስኮት በርግዳ ሳሎኗን የማየት ያህል ነው” ይላሉ፡፡
አሜሪካ አሁን ባለችበት ደረጃ አፍሪካ 50ኛ ዓመት በዓል ስታከብር በይፋ ባይረጋገጥም ኦባማ የመገኘታቸው ሚስጥር ከፖሊሲያቸውና ቻይናን በቅርብ ሆኖ ከመቆጣጠር አዲሱ ስልታቸው በመነሳት እንደሆነ የማያሻማ ነው። በጉባኤው ላይ አራት ከፍተኛ የአገር መሪዎች እንደሚገኙ የኢህአዴግ አንደበት ፋና ጠቁሟል ግን ዝርዝር አላቀረበም። ጆን ኬሪ “ከአፍሪካ ጋር ባለን ግንኙነት ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመሙላት ከአህጉሪቷ ጋር ያለንን ግንኙነት ለማሻሻል እንሰራለን” ማለታቸውን ፋና ምንጭ ሳይጠቅስ አስፍሯል።
ፋናም ሆነ ሌሎች የመንግስት ሚዲያዎች ይፋ ባያደርጉትም የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ባለስልጣናትና የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የስብሰባው ታላቅ እንግዳ እንደሚሆኑ ፖለቲከኞች ቅድመ ግምታቸውን አኑረዋል። በኢህአዴግ ጉባኤዎች ላይ የክልል አንድ ልዩ ዞን ተወካይ እስኪመስል ልዑክ በመላክና የቻይንኛ ቀረርቶ በማሰማት ተሳትፎ ያላት ቻይና ለአፍሪካ ህብረት ታላቅ ስጦታ ማቅረቧ የሚታወስ ነው።
የአፍሪካ ኅብረትን ዘመናዊ ህንጻ በራስዋ ወጪ ያስገነባቸው ቻይና በቤቷ፤ ኦባማም ከተገኙ በእንግድነት የኅብረቱን የምስረታ ዘመን አስመልክቶ ቻይና በነጻ ገንብታ ባስረከበችው ህንጻ ውስጥ ሆነው ህንጻውን እያደነቁ ይደሰኩራሉ።
ምንጭ…ጎልጐል የድረገጽ ጋዜጣ

የኤርትራ አየር መንገድ ከበረራ ደኅንነት ሥጋት ጋር በተያያዘ ወደ ማንኛውም የአውሮፓ አገር እንዳይበር የአውሮፓ ኅብረት አገደ፡፡


የኤርትራ አየር መንገድ ከበረራ ደኅንነት ሥጋት ጋር በተያያዘ ወደ ማንኛውም የአውሮፓ አገር እንዳይበር የአውሮፓ ኅብረት አገደ፡፡
Eritrean_Airlines_Airbus_A320_Bidini
የአውሮፓ ኅብረት በየዓመቱ ዓለም አቀፍ የበረራ ደኅንነት ሥርዓትን በአግባቡ አላሟሉም የሚላቸውን አየር መንገዶች ወደ አውሮፓ የአየር ክልል እንዳይበሩ የሚከላከል ሲሆን፣ የአየር መንገዶቹን ስም ዝርዝር ያሳውቃል፡፡ የስም ዝርዝሩም የአውሮፓ ኅብረት የበረራ ደኅንነት ጥቁር መዝገብ በመባል ይታወቃል፡፡ 
ኅብረቱ በቅርቡ ያወጣው የበረራ ደኅንነት ጥቁር መዝገብ የኤርትራ ብሔራዊ አየር መንገድ የሆነው የኤርትራ አየር መንገድ “ኤር ኦፕሬተር ሠርቲፊኬት” ቁጥር “AOC” No 004 የዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት መለያ ቁጥር “ERT” የተመዘገበውና ናስኤር ኤርትራ የተባለው አየር መንገድ “AOC” No 005 የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት መለያ ቁጥር “ኤንኤኤስ” ወደ ማንኛውም የአውሮፓ አገር እንይይበሩ መታገዳቸውን ይጠቁማል፡፡ መዝገቡ በኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ፈቃድ የተሰጠው ሌላ ማንኛውም አየር መንገድ ወደ አውሮፓ መብረር እንደማይችል ያሳያል፡፡ 
እ.ኤ.አ. በ1991 የተመሠረተው የኤርትራ አየር መንገድ በ2003 ዓ.ም. በተከራየው አንድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን ሥራ የጀመረ ሲሆን ወደ ሮም፣ ካይሮ፣ ጅዳ፣ ዱባይ፣ ፍራንክፈርት፣ ካራቺ፣ ኬፕታውንና ካርቱም ሲበር ቆይቷል፡፡ አየር መንገዱ ከአስመራ ወደ አሰብና ምፅዋ ይበራል፡፡ 
የኤርትራ አየር መንገድ አንድ ኤርባስ 319-200፣ ሁለት ኤርባስ 320-200 እና አንድ ቦይንግ 767-200E አውሮፕላኖች ተከራይቶ ይሠራል፡፡ 
በበረራ ደኅንነት ሥጋት ምክንያት የአውሮፓ ኅብረት በጥቁር መዝገቡ ውስጥ ካሰፈራቸው አየር መንገዶች 100 ያህሉ የአፍሪካ አየር መንገዶች ሲሆኑ፣ ከእነዚህም መካከል 42 ያህሉ በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ የሚገኙ ናቸው፡፡ ከአንጎላ 13፣ ከጎረቤት አገር ሱዳን 12 አየር መንገዶች በአውሮፓ ኅብረት ጥቁር መዝገብ ውስጥ ሰፍረዋል፡፡ ከኢትዮጵያ በጥቁር መዝገቡ ውስጥ የገባ አንድም አየር መንገድ የለም፡፡

ሰበር ዜና! ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን ዛሬም በኦስሎው፣ ታሪክ ሰሩ!


ወያኔ በልማት ስም ገንዘብ ለመቃረምና ደጋፊ ለመመልመል አቅዶ ከሳምንት በፊት በስታቫንገር አንዲሁም በዛሬው እለት ደግሞ በኦስሎ ስብሰባ ለመጥራት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካላቸው የውርደት ካባቸውን ለብሰው መሄድ እጣፋንታቸው እንዲሆን የግድ ሆኗል፡፡ እንደሚታወቀው ባለፈው ሳምነንት ማለትም እንደ ኢሮፓ አቆጣጠር ሚያዝያ 20፣ 2013 በነበረው ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያዊያን ከየተለያዩ ቦታዎች በመሰባሰብ የወያኔ አምባሳደር በስዊድን የሆኑትንና የዲያስፖራ ተወካዩን ከስብሰባ በማባረር ከፍለውበት የነበረውን አዳራሽ ተረክቦ ኢትዮጵያዊያን የራሳቸውን አጀንዳ እና ለተፈናቀሉት ወገኖቻችን እርዳታ የሚሆን ገቢ እንዲሰበሰብና ይህን አምባገነንና ዘረኛ ቡድን መታገል የሚቻለው በ አንድነት መሆኑን ሁሉም የሚስማሙበትና እጅ ለእጅ ተያይዘን መታገል እንዳለብን አስምረው፣ ከ አንድ ሳምንት በሗላ ለሚደረገው የወያኔ ገቢ ማሰባሰቢያ ይህንኑ ድል መደገም ያለበት መሆኑን በመስማማት ነበር የተለያዩት፡፡
ይህንንም ተከትሎ የስታቫንገሩን የወያኔ ፕሮግራም ለማክሸፍ ከፍተኛው ሚና የተጫዎተውን ግብረ-ሓይል በማጠናከር ሳምንቱን ሁሉ ውጤታማ ሥራ ለማድረግ የሙስሊም ወንድሞቻችንን፤ ኦሮሞና ሶማሌ ኢትዮጵያዊያንን በማስተባበር ሌት ከቀን  ሲሰራ ሰነንብቷል፡፡ የጀግኖች ኢትዮጵያዊያንን ከፍተኛ ዝግጅትና ቅስቀሳ ሲከታተሉ የነበሩ የወያኔ ቅጥረኞችና አገላጋዮች ስብሰባ ሊደረግ ታቅዶበት የነበረውን አዳራሽ የስብሰባው ሰዓት ሊደርስ አንድ ሰዓት ተኩል ሲቀረው የመሰብሰቢያው አዳራሽ በፀጥታው፣ በጥራቱና በደህንነቱ በታወቀው ራድሰን ብሉ ሆቴል እንደሚካሄድ አስታውቀው፣ ስብሰባውን ለመሳተፍ ግን ህጋዊ መታወቂያ እንደሚያስፈልግ ተገልፆ የሞባይል አጭር መልዕክት ተላለፈ፡፡ ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን ስብሰባው ይካሄድበታል ተብሎ ከታሰበበት አዳራሽ አካባቢ ከአስር ሰዓት ጀምሮ ወደዚያ የሚያልፈውን የወያኔ ቅጥረኛ ለመቃኘት ወረውት የነበረ ቢሆንም ዘግይቶ የመጣውን አጭር የሞባይል መልዕክት ማለትም የስብሰባ ቦታ መቀየር በመረዳት፣ ወደዚያው ተመመ፡፡
ብዙዎቹ ኢትዮጵያዊያን ከመድረሳቸው በፊት በገቡት የወያኔ ተወካዮች በመበሳጨቱ ወደ ሆቴሉ ለመግባት በነበረው ግብግብ፣ ምንም ዓይነት ሰው እንዳይገባ ተከለከለ፡፡ ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያዊያንን ቁጣ ለማስቆም ከ15 መኪና በላይ የፖለስ ሃይል የተጨመረ ቢሆንም የጀግኖች ኢትዮጵያዊአንን ቁጣና እልህ መቋቋም አልቻሉም ነበር፡፡ አካባቢው የግልና ተቃውሞውም ህገወጥ እንደሆነ በማስረዳት  ከአካባቢው ገለል ለማድረግ ቢሞክሩም አልተቻለም፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ በሆቴሉ የታደሙት የወያኔ ቅጥረኞት ወጥተው ካልሄዱ አካባቢውን ለቀን አንሄድም፤ ይውጡ እንለቃለን፤ ይውጡ እንለቃለን፤ ይውጡ እንለቃለን፤ ይውጡ እንለቃለንበማለት አብዘተው ጮሁ፡፡ ይህንንም ተከትሎ ሁለት ሴቶች እህቶቻችንና ዘጠኝ ወንድሞቻችን ለሰዓታት ታስረው የተፈቱ ሲሆን፤ ፖሊስም የተቃውሞውን ሓይለኝነት በማየት የወያኔ ተወካዮችንና የስብሰባው አስተባባሪዎች በጓሮ በር ማለትም በመኪና ማቆሚያ በኩል ከህዝብ ሰውረው ከሆቴሉ ሸኝተዋቸዋል፡፡
ከዚያም ኢትዮጵያዊያን አያ ሆሆ ማታ ነው ድሌ፤ አያ ሆሆ ማታ ነው ድሌ፤ አያ ሆሆ ማታ ነው ድሌ እያሉ በመዝለል ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡ የሚከተሉትን የፎቶ ትዕይንት ይመልከቱ፡፡
DSC_0010DSC_0012DSC_0015DSC_0922DSC_0931DSC_0938Arrestationarrestation 2.

Friday 26 April 2013

የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ዋና መምሪያ በሙስና መጨማለቁን አንድ ጥናት አመለከተ


መጋቢት ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በብሔራዊ የመረጃ ደህንነት አገልግሎት የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ዋና መምሪያ የመንገደኞች የይለፍ ማረጋገጫ
አሰጣጥ እና የአገልግሎት ክፍያ ገንዘብ ገቢ አሰባሰብ የአሰራር ሥርዓት በሙስናና ብልሹ አሰራር የተጨማለቀ
መሆኑን ከፌዴራል የስነምግባርና የጸረ ሙስና ኮምሽን የተገኘ አንድ ጥናት አመለከተ፡፡
በመምሪያው በይለፍ ማረጋገጫ አሰራር ስርዓት ላይ ለሙስናና ብልሹ አሰራር የሚያጋልጡ ተብለው በጥናቱ ከቀረቡት
ሁኔታዎች ውስጥ የመረጃ አያያዝና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደካማ መሆን፤የሙስናና ብልሹ አሰራር
መንሰራፋት፣የሰለጠነ የሰው ኃይል አለመመደብ፣ግልጽ የስራ መመሪያና ማኑዋል ያለመኖር የሚሉት ተጠቅሰዋል፡፡
ለሠራተኞች የሚያገለግል የሥነምግባር መመሪያ ባለመኖሩ ጠንካራና አስተማሪ የሆነ አስተዳደራዊና የዲሲፕሊን እርምጃ ለመውሰድ ባለመቻሉ  ደላሎች፣ የካውንተር ሠራተኞችና ኃላፊዎች ተባባሪና የጥቅም ተጋሪ በመሆን መንገደኞች በፎርጅድ ፓስፖርትና ቪዛ ከአገር እንዲወጡ ያደርጋሉ። ቪዛ በሕገወጥ መንገድ ከተለያዩ ኤምባሲዎች እንዲወጡና ቪዛ ከሌሎች አገሮች እንዲመጣ በማድረግ መሸጥ፣ ቪዛ የሚሰጡ አገሮች  ለተጓዦች የሰጡትን የቪዛ ሊስትና ቁጥር ለኢሚግሬሽን በሚልኩበት ጊዜ ቦሌ አንዳንድ የመ/ቤቱ ሠራተኞች ዝርዝሩን የመሰረዝና የመፋቅ፣ ከዚያም በማመሳሰል ቪዛውን ፓስፖርት ላይ በመምታት ገንዘብ እንደሚያጋብሱ ተመልክቷል።
እንዲሁም ደላሎችና የካውንተር ሠራተኞች በምን ሰዓት ማን እንዳለ በተለምዶ በመለየት መንገደኛውን በመላክና በሕገወጥ መንገድ እንዲያልፍ በማድረግ፣ ቪዛ በማያስፈልገው የኬንያን በመሳሰሉ ፓስፖርቶች በመጠቀም  መንገደኛው በቦሌ በኩል ካለፈ በኋላ ኬንያ ሲደርስ የሌሎችን አገሮች ቪዛ በመለጠፍ ትራንዚት ነን እንዲሉ በማድረግ፣ ከተለያዩ አገሮች የተባረሩ ተጓዦችን ኤርፖርት ከያዙና አስፈላጊውን መረጃ ከሰነዳቸው ላይ ከወሰዱ በሁዋላ ምርመራ መከናወን ሲገባው በጥቅማጥቅምና በቸልተኝነት እንዲበተኑ በማድረግ ገንዘብ እየተዘረፈ መሆኑ ተመልክቷል።
መ/ቤቱ ለመንግሥት ከፍተኛ ገቢ ከሚሰበስቡት ተቋማት መካከል አንዱ ቢሆንም  የፋይናንስ አስተዳደርና
ሌሎች ጉዳዮች ላይ ተገቢውን ክትትልና ቁጥጥር ለማከናወን የሚችል የውስጥ ኦዲት የሥራ ክፍል የለውም፡፡ በዚህም የተነሳ ይላል ጥናቱ ወቅታዊና ድንገተኛ ኦዲት በአግባቡ ለማድረግ ባለመቻሉ የሚሰበሰበው ገቢ በትክክል ለመንግስት ገቢ መደረጉን ለማረጋገጥ አልተቻለም።  በሚፈጠሩ ችግሮች ላይ ወቅታዊ የማስተካከያ እርምጃ አለመውሰድ፣በፌዴራል ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ዓመታዊ ኦዲት ሪፖርት መሠረት የማሻሻያ ሥራ አለማከናወን የአሰራር ስርዓቱ ለሙስናና ብልሹ አሰራር የተጋለጠ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
በመ/ቤቱ በሁለቱም የሥራ ክፍሎች ተመድበው የሚሰሩ አብዛኛዎቹ ሠራተኞች ብቃታቸውና ክህሎታቸው አነስተኛ
መሆኑም ተመልክቷል።
ለሰራተኞች የስራ ላይ ሥልጠና የሚሰጥ ቢሆንም እንኳን የፎርጀሪና ማጭበርበር መንገዶች እንደ ወቅታዊ ቴክኖሎጂ ደረጃ የሚሻሻሉና የሚለወጡ በመሆኑ በብቃት ለመከላከል የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት አለመዘርጋቱን በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡
የአሰራር ሥርዓት ችግሩን ለመፍታት በሥራ ክፍሎች አሰራር ሥርዓት ላይ በባለሙያ እጥረት ምክንያት እያጋጠመ
ያለውን ችግር ለመቅረፍ ብቃትና ክህሎት ያለውን ባለሙያ ለማስመደብ ወይም ለመቅጠር በቅድሚያ ለሥራ መደቦች
የሚያስፈልገውን የትምህርት ዝግጅትና የሥራ ልምድ እንዲወጣለት በማድረግ ማሟላት፣ ከዚህም በተጨማሪ አዲስ
ሠራተኞች ሥራ ከመጀመራቸው በፊት ስለአሰራሩ በቂ ስልጠና የሚያገኙበት ሁኔታ ማመቻቸትና በሥራ ላይ እያሉ
የማጠናከሪያ ሥልጠና እንዲሰጥ ማድረግ በጥናቱ የተጠቆመ የመፍትሄ ሀሳቦች ናቸው፡፡
የ ተለያዩ የሥራ ክፍሎችን የሚመሩ የሥራ ኃላፊዎች ሥራውን የሚመሩት በግልፅ መመሪያ ሳይሆን በልምድ፣ በቃል ትዕዛዝ እና በማስታወሻ መሆኑ፣ ይህ ዓይነቱ አሰራር ደግሞ ግለሰቦች እንደፈለጉት ሥራውን የሚመሩበት በመሆኑ በተፈለገው ጊዜ የሚሰራበት በማይመች ጊዜ እንዲቆም የሚታዘዝበት አሰራር ዘይቤ እንዲከተልና ለግለሰብ አመለካከት የተጋለጠ መሆኑም በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡
የይለፍ ማረጋገጫ አሰጣጥ አሰራር ሂደት በባህሪው በየቀኑ በርካታ ተገልጋዮችና መንገደኞች የሚስተናገዱበት የሥራ ክፍል ቢሆንም በአሰራር ሥርዓቱ ላይ የመንገደኛው የሀሳብ መስጫ አስተያየት ማቅረቢያ ቅፅም ሆነ ሳጥን አለመኖር፣ የቅሬታ ማስተናገጃ ክፍልም ሆነ ኦፊሰር አለመደራጀት፣ ተገልጋዩ በአቅራቢው ችግሩን የሚፈታበት ሥርዓት ያልተዘረጋ ስለሆነ ችግር ሲያጋጥመው ከቦሌ ወደ ዋናው መ/ቤት እንዲመጣ ማድረግና ማጉላላት ስላለ ለሙስናና ብልሹ አሰራር በቀላሉ የተጋለጠ ሆኗል
ከአሰራር ጋር በተያያዙ የተጠቀሱት ሌሎች ችግሮች ከአገልግሎት የሚሰበሰብ ገንዘብ በየእለቱ ወደ ባንክ ገቢ
አለማድረግ፣ ከመጠን በላይ በካዝና ገንዘብ ማሳደር፣ የዕለት ገንዘብ ሰብሳቢዎች በየዕለቱ የሚሰበስቡትን ገንዘብ
አግባብ ያለው ወቅታዊ ቁጥጥርና ክትትል እየተደረገበት ለባንክ ገቢ አለመሆን፣ የሂሳብ ምዝገባ በየቀኑ
ስለማይመዘገብ አግባብ ያለውን ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ አለመቻልና የገቢ ሒሳብ ምዝገባ ሳይከናወን ለረጅም ወራት
ማከማቸት፣ የገቢ ሒሳብ እንቅስቃሴ መዝገብ በኮምፒውተር በየጊዜው ስለማይመዘገብ ሒሳቡን በወቅቱ አለመዝጋት፣
የገንዘብ መቀበያ ደረሰኞች አያያዝና አጠቃቀም ብክነት ያለበት መሆን እንዲሁም የሚሰበሰበው
ገንዘብና ወደ ባንክ ገቢ የሚሆነው ገንዘብ ከደረሰኞች ጋር በወቅቱና በዕለቱ ማመዛዘኛ /balance/
አለመሰራት የሚሉት ይገኙበታል፡፡
ከመረጃ አያያዝ ጋር በተገናኘ ከተጠቀሱት ችግሮች መካከል ደግሞ ውዝፍ ሥራዎች በመብዛታቸው ምክንያት
ሥራዎችን በዘመቻ በመስራት የሥራ ጫና መኖር፣ ፋይሎች በዓመታትና በየወሩ ተለይተው በቀላሉ የሚገኙና የተደራጁ አለመሆኑ ምክንያት ለክትትልና ለቁጥጥር አለመመቸት፣ ከክልል ኬላዎች ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ጋር የተቀናጀ ግንኙነት ባለመኖሩ የሰበሰቡትን ገንዘብ በወቅቱ በባንክ በኩል ፈሰስ አድርገው ማስረጃውን እንዲልኩ አለማድረግና የገቢ ደረሰኝ በወቅቱ አለመስራት፣ ፋይሊንግ ሲስተሙ በዘመናዊ መልክ የተደራጀ አለመሆን፣ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ማዕከላዊ ሒሳብ መምሪያ ጋር ተናቦ ሪፖርቶችን በወቅቱ አለማዘጋጀት፣ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር፣ ብሔራዊ ባንክና በመሥሪያ ቤቱ መካከል ልዩነት መኖር ፣ የሚሉት ተካተዋል።
ብሔራዊ የመረጃ ደህንነት አገልግሎት የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ዋና መምሪያ ፓስፖርት ለማውጣትም ሆነ
ለማሳደስ ዜጎች እስከ አራት ወራት የሚደርስ ቀጠሮና መጉላላት የሚደርስባቸው ሲሆን ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት
በነፍስወከፍ እስከ አምስት ሺ ብር ጉቦ በመጠየቅ ላይ መሆናቸውን በቅርቡ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
መ/ቤቱ በቂ የትምህርት ዝግጅት በሌላቸው በቀድሞ የህወሀት / ኢህአዴግ ታጋዮች ከላይ እስከታች የተሞላ መሆኑም ይታወቃል፡፡

ህዝቡ በወያኔ ላይ ያለውን ምሬትና ጥላቻ መግለጽ ጀምሯል!



የኢትዮጵያ ህዝብ እውነተኛ ምርጫና የቀልድ ምርጫ ምን ማለት እንደ ሆነ ጠንቅቆ የሚያውቅ መሆኑን በ1997 አም ባደረገው አለምን ባስደመመ ሂደት አስመስክርዋል::
ወያኔና ጀሌዎቹ ግን ዛሬም ሊማሩ አይችሉምና ደግመው ደጋግመው ህዝባችን ሊያሞኙት ይሻሉ በ2002 አ.ም ምርጫ ቦርድ ከሚባለው ሎሊያችው ጋር ሆነው ድምጹን ሰርቀውና አሰርቀው አሽንፍዋል አሽነፍን ብለው አይናቸውን በጨው አጠበው ጨፍር ብለው አደባባይ አስወጡት፤ በጥቃቅን ስም ባደራጁቸው እበላ ባዮች ታጅበውም በአደባባይ አላገጡ በህዝብ ቁስልም ላይ ጨው ነሰነሱ ህዝብም ታዝቦ ዝም አለ ዘንድሮስ?
ዘንድሮ የተለየው ነገር ተቃዋሚዎች ተባብረው 33 የሚሆኑት በአንድ ላይ ቆሙ ከምርጫው በፊት ጥያቄዎችን አንስተው እንደራደርም ብለው ጠየቁ ትእቢተኛው ወያኔም እንደልማዱ አሻፈርኝ የት ልትደርሱ አላቸው ትኩረታቸውን በሙሉ በየቤቱ እየዞሩ ካርድ እንዲወስድ ያስፈራሩት ጀመር የፈራ ወሰደ ያልፈራም ሳይወስድ ቀረ ይህንንም ህዝብ በትዝብት ተመለከተ ፤ካድሬዎቹም ሆነ አለቆቻቸው ወያኔዎች እሁንም ህዝቡን ንቀውታል ምን ያመጣል በሚል ትእቢት ከ99.6 % ወደ 100፥ በመለወጥ ለማሸነፍና ለመጨፈርና ለማስጨፈር ዝግጅታቸውን ማጠናቅቅ ላይ ብቻ አደረጉ።
ተቃዋሚዎችም በአንድ ድምጽ በመሆን የወያኔ የምርጫ አሻንጉሊት ሆነን ለእሱ ፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያ አንሆንም ብለው በውሳኔያቸው በመጽናታቸው ወያኔን በእጅጉ አበሳጭቶታል፤ ይሁን እንጅ አጨብጫቢ የሆኑ ፓርቲዎችን መፈለጉ ግን አልቀረም ለምርጫ ጨዋታው አዳማቂነት። የምርጫ ዴሞክራሲያዊነት ከሚለካበት አንዱና ዋናው ፤ ህዝብ የሚፈልጋቸውን መሪዎቹ ያለማንም አስገዳጅነት መርጦ እንደሚሾሙና እንደሚሽር ማመን ሲጀምር መሆኑ ዛሬም ሊዋጥላቸው አልቻለም። ይሁን እንጅ ህዝብ ዛሬ ሳይሆን ከ97 ምርጫ ጀምሮ ወያኔን በህዝብ ድምጽ ተሸንፎ እንደማይወርድ የተገነዘበው አሁን ላይ ሆኖ ሳይሆን ትላንት መሆኑን ወያኔዎች አልተረዱትም ቢረዱትም ለህዝብ ድምጽ ደንታ አልሰጣቸውም።

ስለዚህም የህዝብ የበላይነት ማረጋገጫ የሆነውን ምርጫ ሂደት ወደ ልጆች መጫዎቻነትና ማላገጫ በመቀየር መሬት ላይ የሌለውን ምርጫ በቲቢ ምርጫ እንዳለ ለማስመሰል በኢቲቪ ተወዳድሮ የማሸነፍ ምኞታቸውን መራጭ በሌለበት ምርጫ ለማሳየት ሞክረዋል። ይህም የማስመሰል እና የማጭበርበር አመላቸው ሱስ ሆንባቸው የውድቀታቸውን፣ የሽንፈታቸውን ጽዋ እየተጋቱ እልል ሲሉ ያሳዩናል “በቀሎ እያረረ ይስቃል እንዲሉ”።
የሀገሪቱን ዜጎች በደልና ጥቃት የፍትህ ስርአት የነጻነት ጥያቄ በማፈን የአማራውን መፈናቀል ያልዘገበ ሚዲያና ጋዜጠኞቹ፤ እውን ምርጫ ስላልሆነ ተውኔት የአለቆቻቸውንና የስልጣን ጥመኞችን ውሸት እውነት አድርጎ በማቅረብ አለቆቻቸውን ሲደስቷቸው ሌሎችን ደግሞ አሳዝኗል።
ሚዲያ በታፈነባት ሀገረ-ኢትዮጵያ እንደ ኢቲቪ ያሉ ያዩትን ሳይሆን በወያኔ የተነገሩትን፣ የተዘጋጀላቸውን ሀተታዊ ድራማ በሚዘግቡ፤ እውነታን በማይናገሩ ቡችሎች ስለምርጫ ሲዘምሩ ይታያሉ። ካድሬዎቻቸው እንኳ ወጥተው ባልተሳተፉበት መራጭ የሌለውን፤ ውጤቱ የዜሮዎች ድምር ዜሮ የሆነውን የምርጫ ድራማ ተውኔትና ውርደታቸውን ሲያሳዩ በአንጻሩ ህዝብ እየተፈናቀለ እያዩ እንዳላዩ በመሆን ለማስመሰያ ጭዋታ የሀገሪቱን ንብረትና ሀብት ያባክናሉ።
ይህን ሁሉ ፈተና አልፎና ተገድዶ የሄደው ህዝብም ቢሆን ያገኘውን እድል በመጠቀም ወያኔዎችን ውረዱ፣ በቃችሁ፣ወንጀለኞች ናችሁ፣ የፖለቲካና የሃይማኖት እስረኞችን ፍቱ እና ሌሎችንም የወያኔ ባዶነትን ለመግለጽ ባዶ ወረቀቶችን በመስጠት ጥላቻቸውን በድጋሜ አረጋግጠውላቸዋል። ግንቦት 7 ህዝቡ ያሳየውን እምባይነት እያደነቀ ነገር ግን የወያኔዎችን ጭቆና ተቋቁሞ ትግሉን ከዚህም በላይ በመውሰድ በየአካባቢው በማፋፋም መቀጠልና ነጻ አውጪዎችን ሳይጠብቅ በራሱ ጎበዝ አለቃዎች በመደራጀት አልገዛም ባይነቱን እንዲቀጥል ጥሪውን በዚህ አጋጣሚ ማስተላለፍ ይወዳል።
ንቅናቂያችን ዛሬም ትክክለኛና ህዝብ በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ተሳትፎ የሚመርጠው አካል፣ እንዲሁም ለህዝብ ተጠያቂ የሆነና ህዝብን የሚፈራ መንግስት፣ በህዝብ የሚሾም፣ የሚሻር አካል ለመፍጠር በቅድሚያ ወያኔን በማስወገድ ብቻ ነው ብሎ ያምናል።
ነጻነትን ለማግኘት ዝም ብለን ስለተመኘነው የሚመጣ አይደለም፣ ዝም ብሎም በራሱ ታምር ሆኖ አይከሰትም፤ ሁሉም ዜጎች ከወያኔ የምርጫ ማጭበርበሪያ ካርድ ወጥተው ተደራጅተውና አደራጅተው በተናጥልም ሆነ በቡድን ወያኔን አስወግዶ በሀገራችን ሁሉም ዜጎች በእኩልነት ተከብረው የሁሉም መሰረታዊ መብቶች ባለቤት ሲሆኑ ነው።
ይህ የሚሆነው ደግሞ ወያኔ እንደ ምጽዋት እስጣችኋለሁ በሚለው መንገድ ሳይሆን ፣ ብቸኛው ምርጫ በሆነው ነጻነታችንን ለማስከበርና የሀገራችንን ህልውና ለመታደግ ማናቸውንም አይነት የትግል ስልቶችን ተጠቅመን ደማችንን አፍሰን አጥንታችንንም ከስክሰን በሚከፈል ዋጋ መሆኑን አምነን ትግሉን በማፋፋም በመሆኑ በተለይም ወጣቶች ትግሉን እንድትቀላቀሉን ጥሪያችን ይድረሳቹሁ እንላለን።
በዚህም አጋጣሚ ግንቦት 7 ለወያኔ አባላት የሚያስተላልፈው መልእክት በፍላጎታችሁ እና በምርጫችሁ የመስራትና የመኖር ሰብአዊ ነጻነታችሁ በወያኔ የፖለቲካ ፓርቲ አሽከር አደግዳጊና ጉዳይ ፈጻሚ በመሆን ብቻ የምታገኙት እርጥባን ሳይሆን በዜግነታችሁና በሰውነታችሁ የተሰጣችሁ መብት በመሆኑ ከፍርሃት ወጥታችሁ ንጹህ ህሊናን ተጥቅማችሁ ወያኔን በማስወገድ በሚደረገው ህዝባዊ ትግል ውስጥ ጊዜው ሳይይረፍድ ከታጋይ ሀይሎች ጋር በመቀላቀል የበኩላችሁን አስተዋጽኦ በማድረግ ኢትዮጵያዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ESAT DC Daily News 25 April 2013


የህዳሴ ግድብ ኃይል ጣቢያ በ1 ቢሊየን ዶላር የቻይና ብድር ሊሠራ ነው


ከታላቁ የኢትዮጵ ህዳሴ ግድብ የሚመነጨውን ኃይል የሚያስተላልፍና የሚያከፋፍል ጣቢያ ለመገንባት የሚያስችል የኮንትራት ስምምንት ተፈረመ። የማስተላለፊያና የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይጠይቃል።
የኮንትራት ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ምህረት ደበበና የቻይናው ኤሌክትሪክ ፓወር ኢኩዊፕመንት ና ቴክኖሎጂ ኩባንያ ተወካይ ሚስተር ዥያ ዥኪያንግ ፈርመዋል።
አቶ ምህረት በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ ከሚውለው ገንዘብ 85 በመቶ ከቻይና መንግሥት በብድር የሚገኝ ሲሆን፣ ቀሪው በኢትጵያ መንግሥት ይሸፈናል።
የጣቢያው ግንባታ በቀጣዮቹ 30 ቀናት ውስጥ ይጀመራል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ሥራው በ24 ወራት ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።
የፕሮጀክቱ ጥናትና ዲዛይን ሥራ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች መካሄዱን ገልጸው፣ በግንባታው ላይ የሁለቱም አገሮች ባለሙያዎች በጋራ እንደሚሳተፉ አስረድተዋል።
የኃይል ማስተላለፊያ መሥመሩ ባለ 500 እና 400 ኪሎ ቮልት የመሸከም አቅም ያለው ሲሆን፣ አጠቃላይ ርዝመቱ 700 ኪሎ ሜትር ይሸፍናል።
አቶ ምህረት እንዳሉት መሥመሩ ወደፊት በዓለም አቀፍ ደረጃ በኃይል ማስተላለፍ መስክ ለሚደረገው ግንኙነት ከፍተኛ ጠቀሜታም ይኖረዋል። ከግድቡ የሚመነጨውን ኃይል ከዋናው ብሄራዊ ሃይል ማዕከልር ለማገናኘት ከደዴሳ -ሆለታ፣ሰበታ ሁለት እንዲሁም ከሆለታ ወደ ሰበታ ከዚያም አቃቂ ወዳለው የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ እንዲገባ ይደረጋል።
ሚስተር ዥኪያንግ እንዳሉት ኩባንያቸው ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ውስጥ አጠናቅቆ እንደሚያስረክብ ገልጸዋል።
በፊርማው ሥነ ሥርዓት ላይ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል፣የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር አቶ ዓለማየሁ ተገኑና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
***************
Source: Ethiopian News Agency – April 26, 2013. Originally titled “የህዳሴ ግድብ የሚመነጨውን ኃይል የማስተላለፊያና የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ለማከናወን ስምምነት ተፈረመ”.

Wednesday 24 April 2013

በወልድያ ከተማ በርካታ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ታሰሩ

ሚያዚያ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በመላው አገሪቱ ከሚካሄደው የሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በወልድያ ከተማ 10 ሙስሊም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከአለፈው አርብ ጀምሮ መታሰራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
በዛሬው እለትም እንዲሁ አንድ የሁለተኛ ደረጃ እንግሊዝኛ መምህር የሆኑት አቶ አብደላ እና የመደርሳ ትምህርት ቤት የእቃ ግምጃ ቤት ሀላፊ የሆኑ ግለሰቦች ተይዘው ታስረዋል።
መንግስት የሙስሊሙን እንቅስቃሴ ለማፈን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተቃውሞው አስተባባሪዎች ናቸው የሚላቸውን ሰዎች እየያዘ በማሰር ላይ ይገኛል። የተያዙት ተማሪዎች በአሁኑ ጊዜ በወልድያ እስር ቤት ውስጥ ይገኛሉ።
በጉዳዩ ዙሪያ የዞኑን የፖሊስ አዛዥ ለማነጋገር ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።
የአካባቢው ሰዎች እንደሚሉት ፖሊሶቹ አሁንም ተጨማሪ ወጣቶችን ለማሰር እየተንቀሳቀሱ ነው

የፌደራል ፖሊስ አባላት ከግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል ጋር ግንኙነት አላቸው ብለው የጠረጠሩዋቸውን ወጣቶች ይዘው አሰሩ

ሚያዚያ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንዳመለከተው ከአዲስ አበባ የተንቀሳቀሱ የፌደራል ፖሊስ አባላት ከባህርዳር በ35 ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘዋ መርአዊ ከተማ በመሄድ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አፍነው ወስደዋል።
ፖሊሶቹ ትናንት ምሽት ወደ ከተማዋ በመግባት እና የአካባቢውን ሰዎች በማስፈራራት ልጆቹን አፍነው የወሰዱዋቸው ሲሆን፣ አንድ ወጣት ክፉኛ መደብደቡን ለማረጋጥ ተችሎአል። የታሰሩት ወጣቶች ወደ አዲስ አበባ መወሰዳቸውም ታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በኢህዴን ኢህአዴግ እንዲሁም በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የደህንነት ሹም በመሆን ለረጅም ጊዜ ሲያገለግል የነበረው ሻለቃ መሳፍንት ጥጋቡ የግንቦት7 ህዝባዊ ሀይልን መቀላቀሉ ታውቋል።
ሻለቃ መሳፍንት በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ስላለው የዘር ችግር፣ በብአዴን ውስጥ ስለሚነሱ ቅሬታዎች እና መሰል ጉዳዮች ዛሬ ከኢሳት ጋር ሰፊ ቃለምልልስ አድርጓል። ሙሉ ቃለምልልሱ በቅርቡ ይቀርባል።

Tuesday 23 April 2013

የማረሚያ ቤቱ ድራማ በርዕዮት እምቢተኝነት ከሸፈ


ባሳለፍነው እሁድና ሰኞ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት የምትገኘውን ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን ለመጠየቅ በዛ ያሉ የሞያ አጋሮቿና አድናቂዎቿ በስፍራው ተገኝተው ነበር፡፡የጠያቂዎቹ በዛ ብሎ የመገኘት ዋነኛ ምክንያት ደግሞ ርዕዮት በቅርቡ የዩኔስኮን የ2013 አለም አቀፍ ሽልማት በማግኘቷ እንኳን ደስ አለሽ በማለት የደስታዋ ተካፋይ መሆናቸውን ለመግለጽ ነበር፡፡ የባልንጀሮቿን የደስታ ምኞት እየተቀበለች ለሁሉም ሽልማቱ የእርሷ ብቻ እንዳልሆነም ትገልጽ ነበር፡፡
ርዕዮት ጠያቂዎቿን በመቀበል እያነጋገረች በነበረችበት ሰዓት(ሰኞ ዕለት) የቪዲዩ ካሜራ በመደገን ለመቅረጽ ይሞክር የነበረ አንድ ሰው በጋዜጠኞች እይታ ስር ይወድቃል፡፡ርዕዮት ላይ ያነጣጠረው ካሜራ የፈለገውን እንዳያገኝም በስፍራው የነበሩ ሰዎች ጋዜጠኛዋን በመክበብ ምስሏን እንዳይቀርጽ አድርገዋል፡፡በጠያቂዎቿ እንደተከበበች ርዕዮትን መቅረጽ ያልሆነለት ስውሩ ጋዜጠኛ በመጨረሻ ርዕዮትን ነጥሎ ለማናገር ይሞክራል፡፡በዚህ ወቅት ግን የጠያቂዎች ሰዓት በማለቁ የርዕዮት ጠያቂዎች ማረሚያ ቤቱን ለቅቀው እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡
CourageEagle7የፍኖተ ነጻነት ምንጮች እንዳረጋገጡት ጋዜጠኛው ርዕዮትን በማግኘት ‹‹አንቺ ጋዜጠኛ አይደለሽ፣በራስሽ የምትተማመኚ ከሆነስ ለምን ለመቀረጽ እምቢ ትያለሽ›› ይላታል፡፡ርዕዮትም  ‹‹ከአንተ ጋር ከመነጋገሬ በፊት የማረሚያ ቤቱን ሃላፊዎች  ማነጋገር እፈልጋለሁ›› በማለቷ ሃላፊዎቹ ይመጣሉ፡፡ርዕዮት ቀጠለች‹‹ይህ ጋዜጠኛ የሚፈልገውን ቃለ ምልልስ የመስጠት ችግር የለብኝም፣ ነገር ግን የተናገርኩትን ቆራርጦና ጨማምሮ ሊያቀርበው የሚችል በመሆኑ የነጻ ሚዲያ አባላት በቃለ ምልልሱ ወቅት እንዲገኙ ይደረግ ፣ ከዚህ ውጪ ግን ለጥያቄው ምንም አይነት ትብብር እንደማላደርግ ይታወቅልኝ››በማለት አቋሟን ግልጽ አድርጋለች፡፡
እንደሚታወቀው መንግስት በሽብርተኝነት ከስሶ በእስራት እንድትቀጣ እያደረጋት የምትገኘው ጋዜጠኛ የጤንነቷ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መገለጹን ተከትሎ በአገር ውስጥና በውጪ መንግስት ላይ ከፍተኛ ጫና እየተደረገ ይገኛል፡፡የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቹ ሲፒጄን ጨምሮ የአውሮፓ ፓርላማ አባል የሆኑት ሚስ አና ጎሜዝ፤የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትና ሌሎች አለም አቀፍ ተቋማት ጋዜጠኛዋ ተገቢውን የህክምና ክትትል እንድታገኝ መጠየቃቸው አይዘነጋም፡፡
ከዚህ ቀደም ፖለቲከኛና ዳኛ የነበሩት ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ በታሰሩበት ወህኒ ቤት ለህመም ተጋልጠዋል የሚሉ መረጃዎች በመውጣታቸው ጫና የተፈጠረበት መንግስት ብርቱካን በጤንነት ላይ ይገኛሉ ለማለት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አማካኝነት አንድ ዘገባ መስራቱ አይዘነጋም፡፡ርዕዮት ማረሚያ ቤቱ ያስገባው ስውሩ ጋዜጠኛ ከእውቅናዋ ውጪ  ሊሰራው የነበረውን ድራማ ቀድማ በመንቃቷ ሊሳካ አልቻለም፡፡
ባሳለፍነው እሁድና ሰኞ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት የምትገኘውን ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን ለመጠየቅ በዛ ያሉ የሞያ አጋሮቿና አድናቂዎቿ በስፍራው ተገኝተው ነበር፡፡የጠያቂዎቹ በዛ ብሎ የመገኘት ዋነኛ ምክንያት ደግሞ ርዕዮት በቅርቡ የዩኔስኮን የ2013 አለም አቀፍ ሽልማት በማግኘቷ እንኳን ደስ አለሽ በማለት የደስታዋ ተካፋይ መሆናቸውን ለመግለጽ ነበር፡፡ የባልንጀሮቿን የደስታ ምኞት እየተቀበለች ለሁሉም ሽልማቱ የእርሷ ብቻ እንዳልሆነም ትገልጽ ነበር፡፡
ርዕዮት ጠያቂዎቿን በመቀበል እያነጋገረች በነበረችበት ሰዓት(ሰኞ ዕለት) የቪዲዩ ካሜራ በመደገን ለመቅረጽ ይሞክር የነበረ አንድ ሰው በጋዜጠኞች እይታ ስር ይወድቃል፡፡ርዕዮት ላይ ያነጣጠረው ካሜራ የፈለገውን እንዳያገኝም በስፍራው የነበሩ ሰዎች ጋዜጠኛዋን በመክበብ ምስሏን እንዳይቀርጽ አድርገዋል፡፡በጠያቂዎቿ እንደተከበበች ርዕዮትን መቅረጽ ያልሆነለት ስውሩ ጋዜጠኛ በመጨረሻ ርዕዮትን ነጥሎ ለማናገር ይሞክራል፡፡በዚህ ወቅት ግን የጠያቂዎች ሰዓት በማለቁ የርዕዮት ጠያቂዎች ማረሚያ ቤቱን ለቅቀው እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡
የፍኖተ ነጻነት ምንጮች እንዳረጋገጡት ጋዜጠኛው ርዕዮትን በማግኘት ‹‹አንቺ ጋዜጠኛ አይደለሽ፣በራስሽ የምትተማመኚ ከሆነስ ለምን ለመቀረጽ እምቢ ትያለሽ›› ይላታል፡፡ርዕዮትም  ‹‹ከአንተ ጋር ከመነጋገሬ በፊት የማረሚያ ቤቱን ሃላፊዎች  ማነጋገር እፈልጋለሁ›› በማለቷ ሃላፊዎቹ ይመጣሉ፡፡ርዕዮት ቀጠለች‹‹ይህ ጋዜጠኛ የሚፈልገውን ቃለ ምልልስ የመስጠት ችግር የለብኝም፣ ነገር ግን የተናገርኩትን ቆራርጦና ጨማምሮ ሊያቀርበው የሚችል በመሆኑ የነጻ ሚዲያ አባላት በቃለ ምልልሱ ወቅት እንዲገኙ ይደረግ ፣ ከዚህ ውጪ ግን ለጥያቄው ምንም አይነት ትብብር እንደማላደርግ ይታወቅልኝ››በማለት አቋሟን ግልጽ አድርጋለች፡፡
እንደሚታወቀው መንግስት በሽብርተኝነት ከስሶ በእስራት እንድትቀጣ እያደረጋት የምትገኘው ጋዜጠኛ የጤንነቷ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መገለጹን ተከትሎ በአገር ውስጥና በውጪ መንግስት ላይ ከፍተኛ ጫና እየተደረገ ይገኛል፡፡የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቹ ሲፒጄን ጨምሮ የአውሮፓ ፓርላማ አባል የሆኑት ሚስ አና ጎሜዝ፤የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትና ሌሎች አለም አቀፍ ተቋማት ጋዜጠኛዋ ተገቢውን የህክምና ክትትል እንድታገኝ መጠየቃቸው አይዘነጋም፡፡
ከዚህ ቀደም ፖለቲከኛና ዳኛ የነበሩት ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ በታሰሩበት ወህኒ ቤት ለህመም ተጋልጠዋል የሚሉ መረጃዎች በመውጣታቸው ጫና የተፈጠረበት መንግስት ብርቱካን በጤንነት ላይ ይገኛሉ ለማለት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አማካኝነት አንድ ዘገባ መስራቱ አይዘነጋም፡፡ርዕዮት ማረሚያ ቤቱ ያስገባው ስውሩ ጋዜጠኛ ከእውቅናዋ ውጪ  ሊሰራው የነበረውን ድራማ ቀድማ በመንቃቷ ሊሳካ አልቻለም፡፡

የመሠረታዊ ነፃነት ቀበኞች!


የነፃነት ቀበኞች (ፀሮች) የተደራጁትም ያልተደራጁትም ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ አንዳንዶቹ ጡንቻቸውን አፈርጥመው፣ ክራንቻቸውን ስለው፣ ጥፍሮቻቸውን ወድረው ሊዘነጣጥሉ የሚችሉበት አቅምና ጉልበት አላቸው፤ አንዳንዶቹ ደግሞ ያ ጉልበት ስለሌላቸው፣ ቀበኛ ባሕሪያቸውን በጩኸትና በስም ማጥፋት ተግባር ላይ ተሰማርተው ያከናውኑታል፡፡ በልዩ ልዩ መልክና ቅርጽ የተደራጁት “የመሠረታዊ ነፃነት ጠሮች (ቀበኞች)” ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ገሚሶቹ በገዢነት (በፓርቲነት)፣ አንዳንዶቹ በሃይማኖታዊ ማኅበራት ሽፋን፣ ሌሎቹ ደግሞ በአነስተኛና ጥቃቅን ቡድንነት የተደራጁ አዳሚዎችና አሳዳሚዎች ናቸው፤ ቀሪዎቹ ደግሞ በአንድ-ለአምስት ሕዋስ ሥር (as a gangster) የተደራጁ “የጎበዝ አለቆች” ናቸው፡፡ በነዚህ አካላት ጭፍን አካኼድ የተነሳ፣ የዜጎች መሠረታዊ ነፃነትና መብት ይደፈጠጣል፡፡ የሥልጣናቸውና የመጉዳት አቅማቸው መጠን የተለያየ ይሁን እንጂ፣ ሁሉም የመሠረታዊ ነፃነት ቀበኞች (ፀሮች) ናቸው፡፡ ለምን እንደሆኑና እንዴትስ ከዚህ ደረጃ እንደደረሱ ለማሳየት ጥረት አደርጋለሁ፡፡Freedom: the quality or state of being free
የሥነ-መንግሥት ተመራማሪዎች፣ ልዩ ልዩ ዓይነት ነፃነት አለ-ይላሉ፡፡ ሁሉንም ለመዘርዘር አልቃጣም፡፡ ለምሳሌ ያህል፣ የሐሳብ መስጠት ነፃነት፣ አንድ ሰው አምላኩን ሃይማኖቱ በሚፈቅደው መንገድ የማምለክ ነፃነት፣ ተሰብስቦ የመወያየት ነፃነት፣ የመናገርና የመፃፍ ነፃነት፣ እና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትና ነፃነት፣ የመሳሰሉት እያሉ ይዘረዝራሉ፡፡ ሁሉም ታዲያ “ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ነው የሚከወኑት” ይላሉ፡፡ አልተተገበረም አንጂ፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ-መንግሥት በአንቀጽ 27 መሠረት፤ የሃይማኖት፣ የእምነትና የአመለካከት ነፃነት የዜጎች መብት እንደሆነ ይደነግጋል፡፡ በተጨማሪም፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 30 መሠረት፣ የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የመድረግ ነፃነትና አቤቱታንም የማቅረብ መብትን በተመለከተ ነጩ ወረቀት ላይ ሰፍሯል፡፡ ግን አልተተገበረም፡፡ የከፋ በደል ነው፡፡ የበደልም በደል! (“የሰው ልጅ በሠለጠኑትም ሆነ ባልሰለጠኑት አገሮች መሠረታዊ ነፃነት እንጂ ፍፁም ነፃነት ሊያገኝ እንደማይችል የሚታወቅ ነው፤” ሲሉ ተመራማሪዎቹ ያክላሉ፡፡)
ስለ“መሠረታዊ ነፃነት” ምንን ከመጻፌ በፊት፣ ስለዚህ የነጻነት ዓይነት ለመፃፍ ያሳሰቡኝን ምክንያቶች ላነሣ እፈልጋለሁ፡፡ የመጀመሪያው የሩዶልፎ ግራዚያኒ ደጋፊዎች በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 30 መሠረት፤ “የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የመድረግ ነፃነትና አቤቱታንም የማቅረብ መብትን” እንዴት በካልቾ እንደመቱት በመመልከቴ ሲሆን፤ ሁለተኛው ምክንያቴ ደግሞ፣ አንዳንድ ሰዎች (በግልም በቡድንም ሆነው) እንዴት የሌሎችን መሠረታዊ ነፃነት እንደሚጣረሩ ለማሳየት ነው፡፡ ከሁሉ አስቀድሜ ግን፣ “ነፃነት ማለት ምንድነው?” የሚለውን ጥያቄ ለመመለስም እሞክራለሁ፡፡ በአቦ ሰጡኝ የመጣልኝ መልስ፣ “ነፃነት የሰው ልጅ ከአላህ ወይም ከእግዚአብሔር (አዳላህ እንዳትሉኝና ከእግዚአብሔር ወይም ከአላህ) በተፈጥሮ የተሰጠውን ክብር መጠበቂያው ሚዛን ነው፡፡” የሚል ሆነ፡፡ መሠረታዊ ነፃነት የሌለው ሰው፣ በሰው ፊት ሰው የበለጠው፣ ከሰው በታች የሆነም ነው፡፡ ነፃነት የሌለው ሰው፤ በሰው ፊት የተዋረደ፣ የተናቀ፣ ሕቁር (Inferior) ፍጥረት ነው፡፡ ነፃነት የሌው ሰው በአፀደ ሕይወት ቢኖር እንኳን፣ መኖሩ እንደሰው ሳይሆን እንደዕቃ፤ እንደ“እንትና” ሳይሆን እንደ“እንትን” የሚታይና የሚቆጠር ፍጡር ነው፡፡ “እንትን” የሚል ቅጽል የሚሰጠው፣ መሠረታዊ ነፃነት ለሌለው ሰው ነው፡፡ እንትንነት ክብራቸውን በፍርፋሪ ለሸጡና መሠረታዊ ነፃነታቸውን ለተገፈፉ የሚሠጥ ቅጽል ነው፡፡ ለሕቁር ፍጥረታት የሚሠጥ ቅጽል ነው፡፡ እንደዔሳው የብኩርና ክብራቸውን በምስር ንፍሮ ለሸጡና ለለወጡ ፍጥረታት የሚሠጥ ስያሜ ነው፡፡ እነዚህ አምላክ/ፈጣሪ በተፈጥሮ የሰጣቸውን ክብር የቸበቸቡ ፍጥረታት ደግሞ፣ ሰላማዊ ሰልፎችን የሚከለክሉ፣ የመናገርንና የመጻፍን መብት ለመገደብ የሚንጠራወዙ፤ ፖሊስ ወይም የፀጥታና ደኅንነት ኃይል ተቀጣሪዎች ሲሆኑም ሌሎችን በዱላ የሚደበድቡ፣ የሚሳደቡና በተራ ስም አጥፊነት ተግባር የሚጠመዱ ናቸው፡፡ ኅቁር ፍጥረታት ክብር ስለሌላቸው፣ ማንንም አያከብሩም፡፡
ኅቁር ፍጥረታት ሰላማዊ ሰልፍ ሲሏቸው፣ እፊታቸው ድቅን የሚልባው የአመጽ ሰልፍ ነው፡፡ ለኅቁር የፀጥታና የዘመኑ ሹሞች የሚታያቸው፣ በሕግ ፊት ሰዎች እኩል መሆናቸው ሳይሆን፣ ተደብዳቢነታቸው ነው፡፡ ኅቁራን ሹሞችና አሽቃባጮቻቸው፣ ሰብዓዊ መብትን መጣስና መሠረታዊ ነፃነትን ማሳጣት የእንጀራ ገመዳቸው እንዳይበጠስ ማረጋገጫ ነው፡፡ ኅቁራን ባለሥልጣኖች፣ የጉልበት ሥልጣን እንጂ የመንፈስ ሥልጣን የላቸውም፡፡ ለኅቁር ፍጥረታት፣ ካላግባብ በአሸባሪን ስለታሰሩ ወገኖቻችን ሲነገራቸው፣ እንደሰረሰር ሰርሳሪ የቄራ ለማጅ፣ ዋናውንና ሙዳውን ስጋ ትተው አገጭና ሌንጬጭ ይፈልጣሉ፡፡ ኅቁራን ፍጥረቶች፣ “ለአህያ ማር አይጥማትም” እንደሚባለው፣ ትልቁ ዓላማ አይጥማቸውም፡፡ ለኅቁር ፍጥረታት፣ መሳደብና ስም ማጥፋት ቋሚ ተግባራቸው ነው፡፡ ለኅቁራን፣ መቼም ቢሆን የቃላት ስንጠቃና “ከቁንጫ መላላጫ” ማውጣት የተለመደ ተግባር ነው፡፡
እንደአለመታደል ሆኖ ብዙዎቹ የኢትዮጵያ ገዢዎች የዔሳው የመንፈስ ልጆች ናቸው፡፡ የእነሱ አጫፋሪዎችና ሎሌዎቻቸው ደግሞ የባሰባቸው “ኅቁሮች” ናቸው፡፡ ኅቁርነት፣ “ከመምህሩ ደቀ-መዝሙሩ” እንደሚባለው እየከፋና እየሰፋ የሚሄድ ነቀርሳ (Cancer) ነው፡፡ በቅርቡ ፕሮፌሰር መስፍን እንዳሉት፣ ኅቁራን “በቆብ ላይ ሚዶ” የሚሽጡም ናቸው፡ በዚህ አላዋቂነትና ጠብደል መታወር ውስጥ እየኖሩ እንደምን የሌሎችን መሠረታዊ ነፃነት ሊያከብሩ ይችላሉ? ፈጽሞ ፈጣሪ ለሰው ልጆች ስለሠጠው መሠረታዊ ነፃነት ስለማያውቁ፣ ወይም በያውቁም ሆን ብለው ስለሚክዱት፣ የሌሎችን ነፃነትና ክብር የገፋሉ፡፡ (ኋላ እመለስበታለሁ፡፡) አባቶቻችን አገራችን በተወረረች ጊዜ ነፃነትን አጥቶ ሆድን በፓስታና በሹታ ጎስሮ፣ ገላን በአቡጀዲና በጨርቅ ሸፍኖ ከመንቀዋለል ይልቅ፣ መሠረታዊ ነፃነትን ማጣት ምን እንደሚደርስባቸው ስላወቁ፤ “ነፃነት ወይም ሞት!” ብለው በጀግንነት ተጋድለው አለፉ፡፡ በፍርሃትና በጥቅመኝነት ታውረው፣ “ከመሞት መሰንበት” ያሉትም ቢሆኑ፣ ያለመሠረታዊ ነፃነት መኖር ምን ምን እንደሚል አሳምረው ቀምሰውታል፡፡ በዱር በገደል የተጋደሉትና በእስር አዚናራ የተጋዙት ምንኛ እድለኞች ነበሩ?
በነሐሴ 1960 ዓ.ም በወጣው የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ላይ ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ፣ ስለመሠረታዊ ነፃነት ሲያወሱ፣ “የባሕል ነፃነት ነው” በማለት ሊገልፁት ሞክረዋል (ገጽ 5 ላይ ይመልከቱ)፡፡ “በሀገራችንና በሕዝባችን ዘንድ የባሕል ነፃነት ወይም የመሠረታዊ ነፃነት ከነትርጉሙም አይታወቅም፡፡ ነገሩ ግን የሀገርን ነፃነት የማጣትን ያህል ደም የሚያፋስስ ነው፤” (የዛሬይቱ ኢትዮጵያ፣ ነሐሴ 9/1960)፡፡ ይሄው የመሠረታዊ ነፃነትን የማጣትና የማሳጣት ተንኮል፣ ከጥንት ጀምሮ በምዕራባውያን (በቄሳራውያን ሃይሎች) ዘንድ የተለመደ ተግባር ነው፡፡ መሠረታዊ ነፃነት ገፈፋው ዘዴ በጣም ረቂቅና ስልታዊም ነው፡፡ ከባሕልና ከመሠረታዊ ነፃነት ገፈፋ ስልቶች መካከል አንዳንዶቹን ለመጥቀስ እፈልጋለሁ፡፡ የመጀመሪያው ዘዴ፣ የገዢዎችን መብት ለአንዳንድ ተገዢዎች መስጠት ነው፡፡ ሁለተኛ፣ ተገዢዎች ማንነታቸውን ክደው፣ የሀገርና የብሔራዊ ስሜታቸውን ማስካድ ነው፡፡ ሦስተኛውና ዋናው ችግር ደግሞ፣ ተገዢው ባሕሉንና ወጉን እንዲንቅና በራሱ እንዳይተማመን የማድረግ የሥነ-ልቦና ክሽፈት ነው፡፡
ከመጀመሪያው ነጥብ ጀምሮ መተንተን ያለበት ነው፡፡ ገዢዎቹ ለአንዳንድ ተገዢዎች፤ “በብሔር፣ በዘር ወይም በሃይማኖት ተዋጽዖ ስም” የይስሙላ የገዢነት መብት ይሠጧቸዋል፡፡ የአገሩን ሰርዶም በአገሩ በሬ ማለት እንደዚህ ነው እያሉ ይደልሏቸዋል፡፡ ጣሊያን አንዴ ልጅ አያሱን ልጅ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ የአፄ ዮሐንስን ወይም የንጉሥ ተክለ ሃይማኖትን ልጆች ከተገዢነት አውጥታ ገዢ ልታደርጋቸው ያልፈነቀለችው ድንጋይ አልነበረም፡፡ ገዢዎች የሚከተሉት ስልትና ብልሃት ተመሳሳይ ነው፡፡ መሠረታዊ ነፃነቱን የተገፈፈው ሰው፣ የነፃነት ገፋፊውን ቋንቋና አነጋገር በቅጡ እንዲኮርጅ ከተደረገ በኋላ፣ የነፃነት ገፋፊውን አገር ዜጎች ያላቸውን ክብርና የይስሙላ ማዕረግ ይሰጡትና፣ የትውልድ አገሩንና የወገኖቹን መሠረታዊ ነፃነት የሚንድ “ምልምል አሽከር” ይሆናል፡፡ እንደዚያ ለመሆን የሚጠበቁበት ነገሮች ቀላል ናቸው፡፡ የመጀመሪያው ቋንቋውን ማጥናት፣ ሁለተኛ፣ የወራሪውን ሀገር ዜጎች አክባሪ መሆኑን ለማሳየት መስገድ/እጅ መንሳት፣ ሦስተኛ፣ የወራሪውን አገር ከትውልድ አገሩ በላይ እንደሚያፈቅርና እንደሚወድ ማሳየት ነው፡፡ በተቻለ መጠን የሀገሩ ሕዝብና የሀገሩን ፍቅር ክዶ የብሔራዊ ስሜቱን አንጠፍጥፎ ደፍቶ ሞራለ-ቢስ መሆን በቂው ነው፡፡ ያን ጊዜ፣ ከተገዢነት ወጥቶ፣ የፈረስ ስም ተሰጥቶት፣ (ማጆር፣ ወይ ሰር፣ አልያም ደግሞ አፈ-ቄሳር፣ ማንትሴ እየተባለ) የይስሙላ ገዢ/ሹም ይሆናል፡፡ እንዴት ዓይነት አዘቅት ነው ጃል!
ሌላው ከተገዢነት ደረጃ ወጥቶ ወደ ይስሙላ ገዢነት መብት የሚደርስ ሰው፣ ከአፋፉ ጫፍ ላይ ለመድረስ ክህደትን የሙጥኝ ማለት አለበት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ የይሁዳ ሰው ሆኖ ሳለ፣ የገዢዎቹን ሮማዊነት መብት ያገኘውና ከእስር ቤት የተለቀቀው በዚሁ መንገድ ነው፡፡ እንደጳውሎስ ያለውን መብት ያገኘ ሰው፣ ከእስር ቤት ወጥቶ ስለፎለለ ነፃነትን ያለገደብ ያገኘ ይመስለዋል፡፡ ለሌሎች ተገዢዎችም ትልቅ ሰው መስሎ ስለሚታያቸውና በየአደባባዩም ስለሚወጣጠርና ስለሚበጣጠስም ጭምር፣ እርሱን መስሎ ለመገኘትና እርሱ የደረሰበት የክህደት አፋፍ ላይም ለመቆም ብዙ ወገኖቹ በማመጽ ፈንታ ጀርባቸውን ለሸክም፣ ኅሊናቸውንም ለሎሌነት ይሰጡታል፡፡ ተገዢዎች መሠረታዊ ነፃነታቸውን ለማግኘት ከመታገል ይልቅ፣ የገዢነትን መብት ለማግኘት ይንጠራወዛሉ፡፡ ብዙዎችም ነፃነት የሚባለውን አኃዝ ከነመኖሩም ይረሱታል፡፡ ትግሉ ሮማዊ፣ እንግሊዛዊ፣ አሜሪካዊ፣ ፈረንሳዊ፣ ጣሊያናዊ፣ ሳዑዲአረባዊ ወይም ሊባኖሳዊና ኳታራዊ ምንትስ ለመሆን መንጠራራት ይሆናል፡፡ ገዢዎች ከሚሠሩት ሃጢያት ሁሉ እንዲዚህኛው ዓይነት በክፋት የተሞላና የረጅም ጊዜ ቀውስ የሚያስከትል መርዝ የለም፡፡
ነፃነት ገፋፊዎች ይሄንን ሳያደርጉ ሁለት ዓላማዎችን ይዘው ነው፡፡ 1ኛ) የገዢዎቹን (የራሳቸውን) ትልቅነትና የሌላውን ትንሽነት አሳምኖ የበላይም ሆኖ ለመኖር የተዘየደ ደባ ነው፡፡ 2ኛ) አገሩና ሕዝቡም የኋላ ኋላ የይስሙላ ነፃነት ሲሰጠው፣ የባሕል ተገዢ ሆኖ እንዲቀርና የመሠረታዊ ነፃነት ጣዕም ሳይቀምስ እንዲቀር ለማድረግ የተሸረበ ታክቲክ ነው፡፡ በመሆኑም ነፃነት ገፋፊዎች በእቅድና በብልሃት ወደ ዓላማቸው ይደርሳሉ፡፡ አንዱ ዘዴ ከላይ የጠቀስነው የገዢነት መብት መስጠት ሲሆን፣ ሁለተኛው ዘዴ ደግሞ የነሱንና የባሕላቸውን ትልቅነት እንዲሁም ከፍተኝነት የተገዢዎቹንና የባህላቸውን ትንሽነትና ዝቅተኝነት ከልጅነታቸው ጀምሮ በማስተማር ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ትምህርት በአንድ ሕዝብ አእምሮ ውስጥ ሲቀረጽ ባሕል ለዘላለሙ ይጠፋል፡፡ አብሮትም መሠረታዊ ነፃነት ድራሹ ይጠፋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በየአውደ ምህረቱ፣ በየመስጂዱ፣ በየማኅበር ቤቱና በየመንዙማ ዝየራው፣ በየጽዋውና በየወዳጃ ቤቱ ሳይቀር የባሕል ወራሪዎቹ ትልቅነት ስለሚሰበክና ስለሚደሰኮ ዜጎች ከማይወጡት የመሠረታዊ ነፃነት እጦት ውስጥ ገብተው እንዲዘፈቁ ይዳርጋሉ፡፡ የፖሊስና የወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ ስለገዢዎች የበላይነትና ስለሠልጣኞቹ የበታችነት በዘዴ እንዲማሩ ይደረጋል፡፡ ከዚያ ፀጥ-ለጥ ብለው ተገዢ ከመሆን ውጭ ምርጫ አይኖራቸውም፡፡ ጃስ ሲሉት የሚናከስ፣ ጭላጭ ሲያቀርቡለት የሚልስ ውሻና ድመት ይሆናል፡፡
የተገዢዎቹን ሥነ-ልቦናም የበለጠ ለማኮስመንም ሲባል፣ ገዢው በተገዢው ዓይን ከታምራት የማያንሱ ነገሮችን ሲሰራ እንደነበረና እየሠራም እንዳለ ተደርጎ በየመድረኩና በየአደባባዩ ይደሰኮራል፡፡ ተገዢው ሕዝብ የፈለገውን ያህል ቢማርና ጥበበኛ ቢሆን እንኳን፣ ገዢዎቹ የሚሠሩትን ምትሃት ከቶም የማይደርስበት “ራዕይ” መሆኑን እንዲገነዘብ ተደርጎ ይሰበካል፡፡ የገዢዎቹ ራዕይና አርቆ-አሳቢነት ከሞቱም በኋላ በመገናኛ ብዙሃን እየተደሰኮረለት፣ ለሙት መንፈስ ሳይቀር ታማኝ ሆኖ እንዲገዛ ይደረጋል፡፡ ዱሮ-ዱሮ “ሰማይ አይታረስ፣ ንጉሥ አይከሰስ” ነበር የሚባለው፡፡ አሁን ደግሞ “ከጓድ አብዮታዊ መሪያችን ጋር ወደፊት!” ወይም “ከባለራዕዩ መሪ ጋር ወደፊት!” በሚል ሽፋን፣ ሕዝቡ መሠረታዊ ነፃነቱን እንዳይጠይቅ፣ አልፎ-ተርፎ ነፃነቱን ሲገፈፍም ዝም ብሎ እንዲያይ፣ “አሜን” ብሎ እንዲገዛም ያመቻቹታል፡፡ (ብቻቸውን አይደለም፣ ጭፍራና ጀሌ አስከትለው ነው፤ ካድሬዎቻቸውን አስደግድገው ነው፡፡)
ፕ/ር ጌታቸው እንደጠቀሱት፣ ገዢዎች የሚፈጽሙት ሦስተኛው መቅሰፍት ከሁሉ የባሰ ነው፡፡ ተገዢዎች ነፃ ቢወጡ እንኳን ራሳቸውን ችለው የሚያድሩም እንዳይመስላቸው አድርገው በባዶ ፕሮፓጋንዳ ያሸብሯቸዋል፡፡ ገዢዎቹ (ከሃሊዎቹ) የሌሉበት ነገር እንደሚዘባረቅ፤ “እነርሱ ያልገዙት አገር እንደሚበታተን፤ ዜጎች እንደ ሩዋንዳና ቡሩንዲ እንደሚተላለቁ፣” ሟርትና ጥላቻን ይደሰኮራሉ፡፡ ባዶ ሟርትና ፕሮፖጋንዳ መሆኑን ለመረዳት ተገዢዎች ለማመን እስኪቸገሩ ድረስ ፕሮፓጋንዳ ይሠራባቸዋል፡፡ ያንንም ለማወቅ፣ “በእርግጥ ባህላችንና እምነታችን የተመቸ ነውን?” ብሎ የሚጠየቅ ሰው ያስፈልጋል፡፡ ያን ጊዜም፣ የገዢዎቹ ሟርትና ማስፈራሪያ በሥልጣን ከመቆየት የዘለለ ቁብ እንደሌለው ይረዳል፡፡ “ጠመንጃ ነካሾች፣ በሥልጣን ኮርቻው ለመፈናጠጥና ለመቆየት ብለው የሚነዙትን ሽብር ፋይዳ-ቢስነት ለመረዳት፣ በመጀመሪያ ባህልን ጠንቅቆ ማወቅ” እንደሚያስፈልግ ኤድዋርድ ሳይድ Orientalism በተባለው መጽሐፉ ይመክራል፡፡
ስለባህል ምንነት ለመረዳት የሚፈልግ ሰው ካለም፣ “ባሕል ማለት ቋንቋ፣ ዜማ፣ ዘፈን፣ የአለባበስ ዓይነትና ዘዴ፣ የጸሎት ወይም የአምልኮ ሥነ-ሥርዓት፣ ከቤተሰብና ከጎረቤት ጋር ያለው ተራክቦ፣ በአረጋውያንና በልጆች ብሎም በወራዙት መካከል ያለውን ግንኙነትና ሥርዓት እንዴት ነው?” ብሎ መጠየቅና መመርመር አለበት (ፕ/ር ጌታቸው፣ 1960)፡፡ እስከምናውቀውና እከተረዳነው ድረስ፣ የኢትዮጵያውያን ባሕል በፈሪሃ እግዚአብሔር ላይ የተመሠረተ ነው በመሆኑ፣ ዕልቂትን አያስከትልም፡፡ እልቂት ቢከሰት እንኳን የእልቂቱና የግድያዎቹ ፈፃሚዎች ራሳቸውንና ሀገራቸውን ክደው፣ የገዢዎቹ ደረጃ ላይ ደርሰናል በሚሉት የነፃነት ገፋፊዎች ጭካኔ የሚፈፀም ነው፡፡ የእውነተኛ ኢትዮጵያውያን መዋግደ ኅሊና የተገራና ፈሪሃ-እግዚአብሔር ያለው በመሆኑ፣ ለጭካኔ ብርታት የለውም፡፡ ትክክለኛ ኢትዮጵያውያን ኅቁር ፍጥረታት አይደሉም፡፡ ከነፃነታቸውና ከሰብዐዊነታቸው ያለፈ፣ የሚያስቀድሙት ሃብትም ሆነ ሥልጣን የላቸውም፡፡ ኅቁር ፍጥረታት ከፈረሱ በፊት ጋሪውን ያስቀድማሉ፡፡ “ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ይቅደም!” ሲሏቸው፣ “መልካም አስተዳደር እናሰፍናለን!” ይላሉ፡፡
ምዕራባዊያኑም ሆኑ አንዳንድ የምስራቅ አገሮች በአገራችን ላይ የባሕልና የመሠረታዊ ነፃነት ገፈፋን ስፖንሰር ያደርጋሉ፡፡ በከተሞቻችን አካባቢ እንደምናየው፣ ኦርቶዶክስሰ ክርስቲያኖቹ እንደሶሪያና ሊባኖስ ካህናት፣ ሙስሊሞቹም እንደ ሳዑዲና የመን ሼኪዎች፣ ካቶሊኮቹም እንደቫቲካን ቀሳውስት፣ ፕሮቴስታንቶቹም እንደጀርመንና አሜሪካን ፓስተሮች ለመሆን ይቸጋገራሉ፡፡ የሃይማኖትና የፖለቲካ መሪዎቹ፣ ራሳቸውን ክደው በሌሎች ባሕል ኮራጅነት ተጠምደው እሽቅድምድም ይዘዋል፡፡ ከራሳችን አለባበስ የእነርሱ አለባበስ፤ ከራሳችን ዜማና ዘፈን የነርሱ ጋጠወጥ ስልት፣ ከራሳችን የቤተሰብ ኑሮ የነርሱ ቤተሰባዊ ኑሮ፣ ከራሳችን ወግና ሥርዓት የነርሱ ወግና ሥርዓት፣ ከራሳችን አገር የነርሱ አገር የሚሻል መሆኑን ሊያሳምኑን ጥረዋል፡፡ የዚህ የዚህ ታዲያ፣ በዓድዋና በማይጨው ለምን የብዙ ኢትዮጵያውያን ንፁህ ደም ፈሰሰ? በሽንብራ ኩሬና በመተማ፣ በዶጋሊና በኦጋዴን ለምን ጀግኖች ተሰው? አገራችን እንዳትገዛና በእነርሱ እንዳትተዳደር አልነበረምን?!” እንጂ፤ “አገሪቱማ ሳትገዛና ሳትተዳደር መቼ አድራ ታውቃለች! ዋናው ምክንያት እነሱ በምንም መልኩ እንዳይገዙን መሰረታዊ ነፃነታችንን እንዳናጣ አልነበረም እንዴ? የራሳችን ባህል እንድንጠብቅና የነሱን ባህል እንዳንይዝ አልነበረምን?” አሁን ታዲያ ምን ነካን? ምን ዓይነትስ ጥንጣን በላን? ምን አነቀዘን? (ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ፣ 1960፡፡)
ከላይ በጠቀስነው መጣጥፋቸው ላይ ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ እንደገለጹት ከሆነ፣ “በማናቸውም ረገድና በየትኛውም ሥርዓት ውስጥ መሠረታዊ ነፃነት እንጂ ነፃ ነፃነት የለም፡፡” ነፃ ነፃነት (Absolute Freedom) የሌለው፣ በነፃ ነፃነት ውስጥ መኖርም ስለማይቻል ነው፡፡ ነፃ ነፃነት አለ ካልን፤ የሕዝቡ የርስ በርስ ግንኙነት ባዶ (ዜሮ) ነው ማለታችን ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ኃላፊነትና ግዴታ እስካለ ድረስ “ነፃ ነፃነት” የለም፡፡ ያለው መሠረታዊ ነፃነት ነው፡፡ አንዱ ከሌላው የሚቀበለውና ለሌላውም የሚሠጠው እስካለው ድረስ ነፃ ባህልም የለም፡፡ አንዱ ከሌላው ይዋሳል፤ ያውሳልም፡፡ ነፃ ባህል የለም፤ ነፃ ነጻነትም የለም፡፡ ያለው መሠረታዊ ባህልና መሰረታዊ ነፃነት ነው፡፡ ግራዚያኒን ለመቃወም ሰልፍ መሰለፍ አትችሉትም የሚሉትና የሚያስሩት ወገኖች፣ የመሠረታዊ ነፃነት አፈና እያካሄዱ ነው፡፡ አንድ ሃሳብ ወይም አጀንዳ ሲነደፍ የሚጮኹና የሚፎክሩትም ወገኖች፤ መሠረታዊ ነፃነትን ለመግፈፍ በአነስተኛና ጥቃቅን ገዢነት ተግባር ላይ የተሰማሩ ናቸው፡፡ ሃሳቡን ሳይሆን አሳቢውን የሚዘልፉና የሚሳደቡም ኅቁራን ካሉም፤ አንድ ለአምስት የተደራጁ የገዢዎቹ አባሪዎችና ተባባሪዎች ናቸው፡፡ ከዚህ ሌላ አይደሉም፡፡
መሠረታዊ ነፃነትን የሚገድበው መንግሥት የሚባለው አካል ብቻ አይደለም፡፡ የመንደር ጎረምሳ፣ የቀዬ ጠብደልና የአጥቢያም ጎበዝ አለቃ ጭምር ናቸው፡፡ በግሌ መሠረታዊ ነጻነትን የሚገፍን አገዛዝ፣ ሥርዓትና መንግሥታዊ መዋቅር ለማጋለጥና አላህ ወይም እግዚአብሔር የሰጠኝንም ነፃነት ለማስከበር እጥራለሁ እንጂ፤ በአንድ ለአምስት ወይም በአነስተኛና ጥቃቅን ከተደራጁ የመሠረታዊ ነፃነት ገፋፊዎች ጋር ቅንጣት ሴኮንድም አላጠፋም፡፡ በአንድ ለአምስት ወይም በአነስተኛና ጥቃቅን የጎበዝ-አድማ ላይ ለተሰማሩት ወገኖቼም ሆነ ለሌሎች ኢትዮጵያውያን የምናገረው ሃይለ-ቃልም የሚከተለተው ነው፡፡ “እርስ በርስ መፎካከታችንን ትተን፤ መሠረታዊ ነፃነታችንን የሚገፉትንና እያወናበዱ እንግዛችሁ የሚሉንን፤ ካድሬ ሆናችሁ፣ ሎሌ ሆናችሁ ቋንቋችንን ተናገሩ፤ የእኛን ባሕል ተከተሉ፣ የእኛን ሃይማኖት እመኑ፣ እናንተ ምንም ስለማታውቁ፣ እኛ ሁሉንም እናውቅላችኋለን፤ በአጠቃላይ “እኛን ምሰሉ” ባዮችን የአገዛዝ ዘመን እናሳጥር፡፡ እርስ በርስ ስንቦቃቀስ፣ የገዢዎቻችን እድሜ አራዝመን የእኛንም ሆነ የሕዝባችን ስቃይ ከማራዘም፣ የመሠረታዊ ነፃነት ገፋፊዎችን ጎራ ከማጠናከር በስተቀር የምናተርፈው ቅንጣት ታክል ፍርፋሪም ሆነ ሰደቃ እንደሌለ ማወቅ አለብን፡፡ አይመስላችሁም ጎበዝ?!
(የሳምንት ሰዎች ይበለን!)

አንድነት ፓርቲን ግለሰቦች በሚያናፍሱት የተዛባ መረጃ ከረጅሙ ጉዞው ሊገታ አይችልም!!



ፓርቲያችን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ከተመሰረተበት ዕለት አንስቶ በሀገራችን መሰረት ያለው ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲፈጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካደረጉ ፓርቲዎች መካከል አንዱ ነው የሚል ከፍተኛ እምነት አለን። ፓርቲያችን በሀገራችን ፖለቲካ ጉልህ አስተዋጽኦ ለማድረግ ቁርጠኛ የሆኑ አባላቱ፣ አመራሩና ደጋፊዎቻችን የሆኑ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እያደረጉ ያሉት አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ ነው። በዚህ ሂደትም አንድነት ከፍተኛ የሆነ መስዋዕትነት ከፍሏል። ወደፊትም ይህንን ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን። ይቀጥላል…

ESAT Daily News - Amsterdam April 23 2013 Ethiopia


ከእሁድ እስከ እሁድ


(የሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች)


sidamaበሲዳማ ህዝብ እያመጸ ነው
ሚያዚያ 6 ቀን 2005 ዓ ም ኢህአዴግ ብቻውን ሊያካሂደው የነበረውን ምርጫ አንቀበልም በማለት ከተለያዩ ወረዳ በትስስር የተቃወሙ የሲዳማ ብሔረሰብ አባላት መታሰራቸውን የጎልጉል ምንጮች አስታውቀዋል። ምንጮቹ እንዳሉት በአካባቢው ከፍተኛ ድጋፍ ያለው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ከምርጫው ራሱን ማግለሉ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት እንዳገኘም አመልክተዋል።
በቀበሌ የመሰብሰቢያ አዳራሾች የታጎሩ በርካታ ቁጥር ያላቸው የብሔረሰቡ አባላት እንዲፈቱ በሚጠይቁና በታጣቂ ሃይሎች መላከል የተካረረ ግጭት ይነሳል የሚል ፍርሃቻ እንደነበር ያመለከቱት ምንጮች የሲዳማ ተወላጆች የታጠቁ ስለሆነ ኢህአዴግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የመከላከያ አንጋቾችን ማሰማራቱን አመልክተዋል።
ለምርጫው አንድ ቀን ሲቀረው እጩዎቼ፣ ታዛቢዎቼና አባላቶቼ በእስር፣ በድብደባና ከሥራ በመባረር እየተንገላቱ ነው በማለት ራሱን ከምርጫው ያገለለው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ፤ ከምርጫው በኋላም እስሩና እንግልቱ መቀጠሉን ማስታወቃቸውን፣ በአንድ ሳምንት 26 አባላቱ እስር እንደተፈረደባቸው፣ በሲዳማ ዞን በየወረዳው ጊዜያዊ ፍርድ ቤቶችና ሸንጎዎች እየተቋቋሙ የፓርቲው እጩዎች፣ ታዛቢዎችና አባላት ከ400 ብር በላይ የገንዘብ ቅጣትና ከ3ወር እስከ አንድ ዓመት ከስድስት ወር የሚደርስ እስራት እየተፈረደባቸውና ፍርደኞቹ ወህኒ መውረዳቸውን የሲዳማ አርነት ንቅናቄ የደርጅቱ ጉዳይ ሃላፊ ዶ/ር አየለ አሊቶ በመጥቀስ ኢሳት ዘግቧል። የኢህአዴግ አመራሮች ከሳሽም ፈራጅም በሆኑበት ሁኔታ ዜጎቻችን እየተንገላቱ ነው፤ ከምርጫው ብንወጣም ትግላችን ይቀጥላል ማለታቸውን የኢሳት ዘገባ ያስረዳል። (ፎቶ: worancha blogpost)
የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ታስረው ተፈቱ
semayawiበቤንሻንጉል ጉሙዝ በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰውን መፈናቀል ለማጣራት ወደ መተከል ዞን አቅንተው የነበሩት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት፣ የፓርቲው ም/ል ሊቀመንበር አቶ ስለሺ ፈይሳና የምስራቅ ጎጃም ዞን አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ በቃሉ አዳነ በቡለን ወረዳ ታስረው ተፈቱ። ኢሳት ሚያዚያ 12 ቀን 2005 ዓም እንደዘገበው አመራሮቹ የታሰሩት ከፌደራል፣ ከክልል መንግስትና ከዞን ባለስልጣናት ወደ ወረዳው ገብተው ሰዎችን ለማነጋገር የሚያስችል የፈቃድ ወረቀት ይዛችሁ አልመጣችሁም በሚል ነው። “ከአንድ ክልል ወደ ሌላ ክልል ያለፈቃድ ሄዶ ከአንዳንድ ሰዎች ጋር ለመነጋገር አይቻልም፣ በዚያ ላይ እናንተ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ናችሁ? የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ኢ/ር ይልቃል፣ እንዲህ አይነት ስራ ለመስራት በቅድሚያ ከክልል፣ ከዞንና ከወረዳ ፈቃድ እንደሚያስፈልግ፣ ይህን አለማድረግ ደግሞ የብሄረሰቦችን የራስን በራስ የማስተዳደር መብት መናቅ ተደርጎ እንደሚታይ እንደተነገራቸው ኢ/ር ይልቃል ከእስር ተለቀው እየተመለሱ እያሉ ለኢሳት መናገራቸውን ዘገባው ያስረዳል።
በስፍራው ተገኝተው አንዳንድ ሰዎችን በማናገር ያዘጋጁት ቪዲዮ በወረዳው ባለስልጣናት ትዕዛዝ እንዲደመሰስ መደረጉን ኢንጂነሩ ተናግረው፣ ይሁን እንጅ በአይናቸው ያዩት፣ በጆሮዋቸው የሰሙት በቂ መረጃ እንደሰጣቸው ኢሳት በዘገባው አመልክቷል።
ታሪካዊ የሪፖርተር አንደበት
“ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የመክፈቻ ንግግራቸውን አድርገው ሲያበቁ፣ በዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል የተዘጋጀ የሟቹ ጠቅላይ azebሚኒስትር መለስ ዜናዊ የሕይወት ዘመን ትውስታ ከሕፃንነት እስከ ግባተ መሬት ድረስ የነበረውን ዘጋቢ ፊልም ሲታይ በታዳሚዎች ላይ የተደበላለቀ ስሜት ሲፈጠር ተስተውሏል፡፡ በተለይ በዘጋቢ ፊልሙ የአቶ መለስ አስከሬን ከቤልጂየም ብራሰልስ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስና ቤተሰቦቻቸው ከአውሮፕላኑ ሲወርዱ፣ አስከሬኑ ከቦሌ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ቤተ መንግሥት ሲጓዝ፣ የቀብራቸው ዕለት በመስቀል አደባባይ አስከሬናቸውን የያዘው ሳጥን ሲቀመጥና ከፍተኛ ዝናብ እየጣለ አስከሬኑ በሰረገላ ሆኖ ወደ ቅድሥት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሲያመራ የሚያሳየውን ፊልም የተመለከቱ በአፍሪካ ኅብረት የታደሙ ሰዎች፣ ከንፈራቸውን ከመምጠጥ እስከ እንባ ማፍሰስ ድረስ በሐዘን ስሜት ውስጥ ገብተው ተስተውሏል፡፡ ሌላው አዳራሹን ለተወሰኑ ደቂቃዎች የሐዘን ድባብ ውስጥ የከተተ ክስተትም ተፈጥሮ ነበር፡፡ ዘጋቢ ፊልሙን ከሚመለከቱ ታዳሚዎች መካከል የነበሩት የአቶ መለስ እህቶች ድምፅ አውጥተው ለቅሶ በመጀመራቸው፣ ከሰባት ወራት በፊት የነበረውን የሐዘን ሁኔታ ያስታወሰና የሁሉንም ታዳሚዎች ቀልብ የሳበ ሆኖ ነበር፡፡”
ምንጭ፤ የሪፖርተር ጋዜጣ ዘጋቢ ታምሩ ጽጌ “ከለቅሶ ቤት” እንደዘገበው (10 April 2013)
አርበኞች ግንባር ማርኬ ገደልኩ አለ
የኢትዮጵያ አርበኞች ግንባር ልዩ ስሙ ሰቋር እና አምቦ ጠበል በተባለ ስፍራ  በሁለት ተከታታይ ቀናት ከአገዛዙ  የፈጥኖ ደራሽ ሃይል ጋር ባካሄደው  የፊት ለፊት ውጊያ ወታደራዊ የበላይነትን ስለመቀዳጀቱ ለጎልጉል በላከው መግለጫ አስታወቀ።
eppfግንባሩ ሚያዚያ 8 ቀን 2005 ዓ ም በወሰደው የማጥቃት እርምጃ ሃያ አንድ የአገዛዙ ወታደሮችን ግዳይ ማድረጉን፣ ሃያ አምስት ማቁሰሉን፣ በቀጣይ ቀን በዋልድባ አምቦ ጠበል በተባለው ቦታ በተከፈተ ውጊያ  ሃያ አምስት የአገዛዙ ወታደሮችን መግደሉንና ሰላሳ ዘጠኝ በማቁሰል ከፍተኛ ድል እንዳገኘ በመግለጫው አመልክቷል።
ግንባሩ ካደረሰው ሰብአዊ ጥቃት በተጨማሪ  የተለያዩ የቡድንና የነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያዎችንም ከመሰል ጥይቶቻቸው ጋር መማረኩን አስታውቋል። የኢትዮጵያ አርበኞች ግንባር አገኘሁ ስላለው ድልና ተቀዳጀሁት በሚል በይፋ የገለጸውን ዜና አስመልክቶ ከመንግስት በኩል እስካሁን በይፋ የተሰጠ መልስ የለም። ግንባሩም ቢሆን ሪፖርቱን በምስል አላስደገፈም።
የአውሮፓ ህብረት አቋም አልጠራም
የሰብአዊ መብት ማስከበር የህልውናችን ጉዳይ ነው
ከሰብአዊ መብት፣ ከፕሬስ ነጻነት፣ ዜጎች አመለካከታቸውን በነጻ የማራመድና የተፈጥሮ መብታቸው መገፈፉንና አጠቃላይ በአገሪቱ ውስጥ የሰፈነው አምባገነንነት አስጊ ደረጃ መድረሱን አስመልክቶ የአውሮፓ ህብረት የጠራ አቋም አለመያዙ ታውቋል። አቶ መለስ ከሞቱ በኋላ በአውሮፓ የቀድሞውን ወዳጅነት አጥብቀው እንደሚቀጥሉበት ለማረጋገጥ አውሮፓን  የዞሩትን  የጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ  ጉብኝትን አስመልክቶ የጀርመን ሬዲዮ እንደዘገበው የአውሮፓ ህብረት ኢህአዴግን ከማድነቅ አልፎ የ30 ሚሊዮን ዶላር ርዳታeu መስጠቱን አመልክቷል። በሶማሊያ ስለተፈጠረው መረጋጋት፣ በደቡብ ሱዳን ጉዳይና በምስራቅ አፍሪቃ አጠቃላይ ጉዳይ ላይ መምከራቸውን ያወሳው ሬዲዮው፣ የህብረቱ ሊቀመንበር ማሳሰቢያ ቢጤ ማስተላለፋቸውን አመልክቷል።
በኢትዮጵያ ያለውን የኢኮኖሚ እድገት ያደነቁት የህብረቱ ሊቀመንበር፣ “ይህ ዕድገት ቀጣይነቱ ሊረጋገጥ የሚችለው ፣ የአገሪቱ ሕዝብ መሠረታዊ መብቶች፣ የመናገርና ሐሳብን የመግለጽ ነፃነቶች ሲከበሩ ብቻ ነው” ብለዋል። በጋራ በተዘጋጀው መግለጫ አቶ ሃይለማርያም “የሰብአዊ መብቶች መከበር ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው”  አያይዘውም “የመሬት ወረራ ብሎ ነገር የለም፣ ሊኖርም አይችልም፤ አንድም ጋዜጠኛ ሃሳቡን በመግለጹ አልታሰረም “ሲሉ የተለመደውን የመለስን ዓይነት መልስ በመመለስ ሸምጥጠዋል።

“ማፈናቀሉ የሚካሄደው በመንግሥት ትዕዛዝ ነው፤ ወደ ክስ እናመራለን”


“በቤኒሻንጉል የህወሃት ታጋዮች ሰፋፊ እርሻ አላቸው”


በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ከ2000 ሺህ በላይ ትግሬዎች ባለይዞታ መሆናቸውንና ማንም ሳይነካቸው በሰላም እንደሚኖሩ፣ በቶጎ ወረዳ ከስልሳ በላይ ነባር የህወሃት ታጋዮች ሰፋፊ የእርሻ መሬት ወስደው በባለሃብት ደረጃ እንደሚገኙ የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አስታወቁ። ከሌሎች ብሔረሰቦች ተለይቶ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመበት ያለውን የአማራ ብሔረሰብ በድጋሚ ለማስወጣት መታቀዱንም በመረጃ ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።
በቦታው በመገኘት አስፈላጊውን መረጃ እንደሰበሰቡ ለአሜሪካ ሬዲዮ የገለጹት የመኢአድ ስራ አስፈጻሚ በክልሉ ከሚኖሩት የተለያዩ ብሔረሰቦች ተለይቶ የአማራ ብሔረሰብ እንዲፈናቀልና እንዲሰቃይ የሚደረገው በማዕከላዊ መንግስት ትዕዛዝ እንደሆነም አመልክተዋል።
Justice Gavelመኢአድ ያሰራጨውን መግለጫ ተከትሎ በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ ማብራሪያ የሰጡት አቶ ሃይሉ ሻወል፣ ድርጊቱ በበታች የቀበሌና ወረዳ አመራር አካላት ተፈጽሟል መባሉን ተቃውመዋል።”ሰዎቹ እንዲወጡ ሲታዘዝ ያ ሁሉ ወታደር ከየት መጣ?” በማለት የጠየቁት አቶ ሃይሉ ሻወል፣ በርካታ የወያኔ ሰዎች በቦታው እያሉ አማራው ተለይቶ እንዲፈናቀል የበታች ባለስልጣናት በራሳቸው ውሳኔ ይህን ሊያደርጉ እንደማይችሉ ተናግረዋል። በማያያዝም በርካታ ተጨባጭ ማስረጃ ስለተሰባሰበ ጉዳዩን ወደ ዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ለመውሰድ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
ባላቸው የተለያየ መስመር ፍርድ ቤቱ የሚቀበላቸውን ማስረጃዎች በማጣራት አስፈላጊ መረጃዎችን እንዳሰባሰቡ የገለጹት ኢንጂነር ሃይሉ ሻወል፣ “የሰውና የቪዲዮ መረጃ አለን። የመንግስት ወታደሮች ህዝብ ሲደበድቡ፣ መኪና ተገልብጦ ሰዎች ሜዳ ላይ ሲሰቃዩ፣ በግድ ሲፈናቀሉ … የሚያሳይ ተጨባጭ ማስረጃ አሰባስበናል። ወደ ክስ እናመራለን” በማለት መናገራቸውን የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ (ቪኦኤ) አመልክቷል።
የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ አባል በበኩላቸው የመንግስት ባለስልጣኖችና ካድሬዎች በኩምሩክ ሕዝብ በመሰብሰብ ማነጋገራቸውን ይጠቅሳሉ። እሳቸው እንዳሉት ህዝቡ “ለምን በዘራችን ሳቢያ ይህ ሁሉ ስቃይ ይደርስንባል?” በማለት ጠይቆ ነበር። የሰበሰቧቸው ባለስልጣናት “ክልሉ የናንተ አይደለም ውጡ” ሲሉ  እንደመለሱላቸው የጠቀሱት የስራ አስፈጻሚ አባል፣ በሌላ በኩል የተፈጸመው ህገ ወጥ የዘር ማጥፋት ተግባር የመንግስት እጅ ያለበት እንዳይመስል ለክልሉ ነዋሪዎች “አማራን አታስጠጉ፣ ከአማራ ጋር አትብሉ፣ ከአማራ ጋር አትጠጡ፣ ቤት አታከራዩ፣ ይህን ማድረግ ወንጀል ነው” በማለት መንገራቸውንና በዚሁ መነሻ ህዝቡ በክልሉ ያሉ አማሮች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ጥያቄ እንዲያቀርቡ መመሪያ መሰጠቱን አመልክተዋል። ይህ የሚሆነውም ጥያቄው ከህዝብ የመጣ እንደሆነ ለማሳየት እንደሆነም አስታውቀዋል።
ahmed
የቤኒሻንጉል ፕሬዚዳንት አህመድ ናስር
በዘር፣ በሐይማኖትና በአመለካከት አንድን ማህበረሰብ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት መሞከር፣ ማሸማቀቅ፣ ሴቶችን መድፈር በዘር ማጥፋት እንደሚያስጠይቅ ያመለከቱት የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ አባል፣ “ይህ ሁሉ ተፈጽሟል” በማለት ድርጅታቸው በዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ ለመመስረት ከድምዳሜ መድረሱን ገልጸዋል።
የቤኒሻንጉል ክልል ፕሬዚዳንት ለሪፖርተር በሰጡት መግለጫ ስህተት መሰራቱን ማመናቸውና ድርጊቱን የፈጸሙት ኪራይ ሰብሳቢ የወረዳና የበታች አመራሮች እንደሆኑ ማስታወቃቸው አይዘነጋም። በተመሳሳይ ለስራ ፈረንሳይ አገር በነበሩበት ወቅት ለጀርመን ሬዲዮ ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ፕሬዚዳንቱ ተፈጸመ ስላሉት ስህተት “የማውቀው ነገር የለም። አልሰማሁም። እኔ የማውቀው ደን ጨፍጭፈው በሃይል መሬት የያዙ መፈናቀላቸውን ነው” ብለዋል። ዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማርያም ቀደም ባሉት ሳምንታት ከቤኒሻንጉል የተፈናቀሉትን ዜጎች አስመልክተው በሰጡት አስተያየት ወንጀሉ የዘር ማጥፋት ስለሆነ ክስ መመስረት እንደሚቻል አመልክተው ነበር።
መኢአድ በበደኖ፣ በአርባ ጉጉ፣ አረካ ቀደም ሲል የተፈጸሙትን የዘር ማጥፋት ወንጀሎች አያይዞ ለክስ እንደሚጠቀምበት አመልክቷል። በጥያቄና መልሱ ወቅት ከነበሩት ጋዜጠኞች መካከል “የተፈናቀሉት ተመልሰዋል። ለምን አትተውትም” በማለት ጥያቄ ያቀረቡ ጋዜጠኞች እንደነበሩ የቪኦኤው የአዲስ አበባ ዘጋቢ ጠቆም አድርጎ አልፏል።

Wednesday 17 April 2013

በሰሞኑ ምርጫ ከፍተኛ ዘለፋዎችን ያስተናገዱት ወ/ሮ አዜብና ባለራእዩ ባለቤታቸው ናቸው


በሰሞኑ ምርጫ ከፍተኛ ዘለፋዎችን ያስተናገዱት ወ/ሮ አዜብና ባለራእዩ ባለቤታቸው ናቸው

ሚያዚያ ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ ከተማ በተለይም በጨርቆስ ክፍለከተማ በተካሄደው ምርጫ ከፍተኛውን ዘለፋና ትችት ያስተናገዱት ወ/ሮ አዜብ መስፍን እና ባለራእዩ ባለቤታቸው እንደነበሩ በቆጠራው የተሳተፉ የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል።
ኢሳት በ8 የአዲስ አበባ የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ የተሳተፉ ታዛቢዎችን በመጠየቅ ባሰባሰበው መረጃ ከ30 በመቶ ያላነሰ መራጭ ድምጹን የሰጠ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል 10 በመቶ የሚሆኑት ባዶ ወረቀት ሲያስገቡ፣ አብዛኞቹ ደግሞ ከዘለፋ ጀምሮ የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችን ጽፈው አስገብተዋል። እንደ ታዛቢዎች መረጃ አብዛኞቹ ስድቦች በወ/ሮ አዜብ መስፍንና በባለቤታቸው ላይ ያነጣጠሩ ሲሆን፣ ስድቦቹም በአብዛኛው ወ/ሮ አዜብን በሙስና የሚከሱ ናቸው።
የአዲስ አበባ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ እንደቀበራቸው እና ከፍተኛ የህዝብ ፍቅር እንዳላቸው በመንግስት መገናኛ ብዙሀን የተነገርላቸው አቶ መለስ ዜናዊም ትችቱ አልቀረላቸውም። በእሳቸው ላይ የተሰነዘረው ዘለፋና ትችት ባለራእይነታቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ እንደነበር የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
መራጮች በጻፉዋቸው መልክቶች የተደናገጡት የምርጫ ቦርድ እና የቀበሌ ባለስልጣናት በ ወረቀቶቹ ላይ ስለሚወስዱት እርምጃ ግራ ተጋብተዋል።
በ ምርጫው መላው ኢትዮጵያ ህዝብ በአንድ ቃል ኢህአዴግን እንደማይደገፍ ግልጽ ማድረጉን ታዛቢዎች ይገልጻሉ።
ኢሳት ከወራት በፊት ለምርጫው የተመዘገቡ ሰዎች ቁጥር ከተጠበቀው በታች መሆኑን መዘገቡ ይታወሳል።

የህወሓት መንግስት የአመስት መቶ ብር ኖት ላይ የመለስ ዜናዊ ምስል ሊያትም ነው


የህወሓት መንግስት የአመስት መቶ ብር ኖት ላይ የመለስ ዜናዊ ምስል ሊያትም ነው

አንዳንዴ ወሬ በባዶ ሜዳ ይናፈሳል። ብዙ ጊዜ ትንሽ ጫፍ ይዞ ይናፈሳል። የህወሓት መንግስትን በተመለከተ አያደርጉም የምለው ነገር ስለሌለ ለመጠራጠሬ ገደብ አብጂቸ ነው የምጠራጠረው። ብዙ ጊዜ ግን ስለነሱ የሚወራውን አልጠራጠርም። ያደርጉታል።
ሰሞኑንን (ምናልባት ሌሎቻችሁ ከሰማችሁ ቆይታችሁ ይሆናል!) የህወሓት መንግስት የአመስት መቶ ብር ኖት የማዘጋጀት ሃሳብ እንዳለው እና በገንዘቡ ላይ የ “ባለ ራዕዮ መሪ” ምስል እንደሚያርፍበት ሰማሁ። የታላላቅ መሪዎችን ምስል በምንዛሬ ላይ ማስቀመጥ አዲስ ነገር አይደለም። ጥያቄው ግን ታላቅ ማነው? ታላቅነቱ እንዴት ነው? በየትኛውም ማህበረሰብ የበቀሉ የፖለቲካ መሪዎች የራሳቸው የሆኑ ተቃዋሚዎች እንደሚኖራቸው እሙን ነው። ነገር ግን ከሚከተሉት ፖሊሲ በመነሳት ዜግነታቸው ጭምር ጥያቄ ውስጥ የገባ እና በእኛ ሃገር ዘይቤ በባንዳነት ሂሳብ የተያዙ የሌሎች ሃገር መሪዎች ያሉ አይመስለኝም። ያውም ምስላቸው ምንዛሬ ላይ የሚወጣ?! ፈጽሞ አይመስለኝም። የቻይናው ማኦ የጠባብ ብሔርተኛ የፖለቲካ መሪ አልነበረም። የዘር ትምክህት አባዜ አልነበረውም። የኢንዶኔዢያው ሱካርኖ እንደዚያው። የፓኪስታኑ መሃመድ አሊ ጂና እንደዚያው። ብዙ የ”ሶስተኛውን ዓለም” ሃገሮች መሪዎች ለአብነት ማንሳት ይቻላል።
የመለስ ዜናዊ ታሪክ ሌላ ነው( ለማን ይተረካል እንጂ!)። የመራውን የፖለቲካ ቡድን ለይስሙላም ቢሆን ሃገራዊ መልክ ሳይሰጠው የህወሓት ሊቀመንበር እንደሆነ ነው የሞተው። ከዚያ በላይ ግን የመለስ ዜናዊን የጎሰኛነት ጠባይ ትግራይም አዲሳባም ላይ ሆኖ የተናገራቸው የተለያዮ ንግግሮች የሚመሰክሩት አንድ ነገር ነው፡- የመለስ ዜናዊን ከልክ ያለፈ ጎጠኛነት። ምንም ጥያቄ የለውም ህወሃት ውስጥ አብረውት ብዙ ዓመት የፖለቲካ ስራ ለሰሩ፣ታገልን ለሚሉ ጓደኞቹ መለስ ዜናዊ ሌላ ሰው ነበር-ምንም እንኳን አንዳንዶች ጉደኞቹ ከጊዜ በኋላ ቢቀየሙትም (ወይንም የተቀየሙት ቢመስሉም)። እነዚህ የሚወዱት ጓደኞቹ ከፈለጉ የወርቅ ሃውልትም ሊያቆሙለት ይችላሉ ( ለባለ “ራዕዮ” መሪያቸው ያልሆነ ግዳይ ምን ይፈይዳል ታዲያ!)
ነገር ግን ማወቅ ያለባቸው ጉዳይ እንደው በህወሃትኛ ቋንቋ እንኳን መለስ ዜናዊ ለጉራጌው ምኑ ነው?? በአማራው ምኑ ነው? ለኦሮሞው ምኑ ነው? ለወላይታው ምኑ ነው? እያለ እያለ ይቀጥል እና አጥብቆ ጠያቂ ከመጣ ደሞ “እንኳን ለሌላው ለተምቤኑ ምኑ ነው?” ጥያቂ ሊነሳም ይችላል።
መለስ ዜናዊ ትልቁን ከሃዲ እና ጎጠኛ ነበር የሚለውን ነጥብ ትተን በትንሹ አወዛጋቢ የሚባል የፖለቲካ ሰው ነበር። ህወሓት ይሄን አላውቅም ካለ ፓለቲካ አያውቅም ሊያስብለው ይችላል። እውነቱ ይሄ ሆኖ እያለ ህወሓት የመንግስት ስልጣን ስለያዘ ብቻ እንደፈለኩ ገንዘብ ላይ የመለስ ዜናዊ ምስል አትማለሁ ቢል የህወሓትን የአክራሪነት ስሜት ከሚጠቁም በስተቀር ትርፍ ያለው ነገር አይመስለኝም። ከህወሓት ጋር አብሮ የሚሞት የገንዘብ ኖት ነው የሚያዘጋጀው ማለት ነው። ምናለበት ህወሓት ለጎጠኝነቱ ለከት ቢያበጂለት?! ህወሓት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ምንድን ነው የሚፈልገው?? ሌልቹስ “እህት” ነን የሚሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዴት ይሄን ጉዳይ በቸልታ ይመለከታሉ?!
የመለስ ዜናዊ ምስል በምንዛሬ ላይ የመውጣቱ ነገር በትክክል ሊደረግ ታስቦ ከሆነ ክህወሓት በላይ ተጠያቂ የሚሆኑት ክህወሓት ጋር እየሰሩ ያሉ ድርጂቶች ናቸው!
source: Borkena.com

አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በኑሮ ውድነቱ መማረሩን ቀጥሎአል


አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በኑሮ ውድነቱ መማረሩን ቀጥሎአል

ሚያዚያ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የኑሮ ውድነቱ ቅናሽ ያሳይ ይሆን በማለት ኢትዮጵያውያን ከአመት አመት ተስፋ ቢያደርጉም ተስፋቸው ግን ከተስፋነት እንዳልዘለለ በተለያዩ አካባቢዎች የተሰባሰቡ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በአምስት ክልሎች የሚኖሩ ዘጋቢዎቻችን አጠናቅረው የላኩት ዘገባ እንደሚያመለክተው በሁሉም ክልሎች የኑሮ ውድነቱ መካከለኛ እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች በመላ እየጠበሰ ነው።
በምስራቅ የአገሪቱ ክፍል  የኑሮ ውድነቱ ተባብሶ በመቀጠሉ ህዝቡ ኑሮውን በአግባቡ መምራት እየተሳነው ነው። በድሬዳዋ፣ ሀርር እና ሌሎችም አካባቢዎች አንድ ኩንታል ጤፍ እሰከ 2 ሺ ብር በመሸጥ ላይ መሆኑን ነዋሪዎች ይገልጻሉ።
በኦሮሚያ ክልልም እንዲሁ የኑሮ ውደነቱ መባባሱ ህዝቡን ተስፋ እያስቆረጠ መምጣቱን ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው ሰዎች ይገልጻሉ።
በደቡብ ክልል በሚገኙ አብዛኛቹ ክልሎች የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች እና በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች የኑሮ ውድነቱ በሞት እና በህይወት መካከል የጣላቸው መሆኑን ለኢሳት የደቡብ ክልል ዘጋቢ ገልጸዋል። ስኳር እና ዘይት ከገበያ መጥፋታቸውን ፣ በተለይም የእንዱስትሪ ምርቶች ዋጋቸው እየናረ መምጣቱን ነዋሪዎቹ ይገልጻሉ። ከማዳበሪያ ጋር በተያያዘም አርሶ አደሩ በእዳ እየተሰቃየ መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል።
በአማራ ክልልም እንዲሁ አብዛኞቹ የመንግስት ሰራተኞች የሚያገኙት ወርሀዊ ገቢ ቤተሰቦቻቸውን ለማስተዳደር እንዳላስቻለቸው ገልጸዋል።
የማእከላዊ ስታትስቲክስ መስሪያ ቤት ባወጣው የመጋቢት ወር ሪፖርት የ2005 ዓም የ12 ወራት ተንከባላይ አማካኝ አገራዊ የዋጋ ግሽበት ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር በ18 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። በመጋቢት ወር 2005 ዓም አገራዊ የ12 ወራት ተንከባላይ አማካኝ የምግብ ዋጋ ግሽበት በ20 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። የ12 ወራት ምግብ ነክ ያልሆኑ እቃዎች የዋጋ ግሽበትም በ17 በመቶ ጨምሯል።
በመጋቢት ወር የታየው አጣቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው የካቲት ወር 2005 ዓም ጋር ሲነጻጸር ከአንድ በመቶ ያላነሰ ጭማሪ አሳይቷል።
መንግስት በየጊዜው የሚንረውን የኑሮ ውድነት ለመቆጣጠር እንደተሳነው አስተያየት ሰጪዎች ይገልጻሉ። መንግስት የኑሮ ውድነቱ በከፊል የሚጨምረው  የህዝቡ ኑሮ እየተሻሻለ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ የህዝቡ ፍጆታ በመጨመሩ ነው ይላል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሙያዎችን በማነጋገር ተጨማሪ ዘገባ የምናቀርብ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

! ….. ህወሓት ማስጠንቀቅያ ተሰጠው …….!


! ….. ህወሓት ማስጠንቀቅያ ተሰጠው …….!

መንግሥትና ዘመናዊ የሌብነት ስልቶቻቸው
ባለፈው እሁድ በተካሄደው ያከባቢና ከተሞች ‘ምርጫ’ (ይቅርታ አማራጭ የሌለው ምርጫ ምርጫ ኣይባልም ግን ሌላ ስም ለግዜው አላገኘሁም) የትግራይ ህዝብ ባልጠበኩት ሁኔታ (ህወሓት የትግራይ ህዝብ ድጋፍ እንደሌለው ባውቅም) ለህወሓቶች ኣስደንጋጭ ማስጠንቀቅያ መስጠቱ መረጃ ደሶኛል። በብዙ አከባቢዎች ህዝቡ ለመምረጥ ፍቃደኛ ኣልነበረም። አንዳንድ ካድሬዎች ህዝብን እያስገደዱ ወደ ምርጫ ጣብያ እንዲሄድ ቢያድርጉም ዉጤቱ እንደጠብቁት ኣልነበረም።
በትግራይ ተወዳዳሪ ተቃዋሚ ፓርቲ ኣልነበረም (በኣላማጣ ኣንድ ነበር ኣሉ)። በምርጫው ዋዜማ ሁሉም የመንግስት አካላት ህዝብ በምርጫው እንዲሳተፍ ቅስቀሳ ያደርጉ ነበር (‘ይሄው በህዝብ ተመርጠናል’ ለማለት ያህል)። ነገር ግን በኣክሱም፣ ሸረ፣ ሸራሮ፣ ዓዲግራት፣ ዉቅሮ፣ ሓውዜን፣ አላማጣ፣ ዓብዪዓዲ፣ መቐለ ብዙ ችግሮች ነበሩ። ለምሳሌ ያህል በመቐለ ከተማ ባንዳንድ ምርጫ ጣብያዎች ያጋጠመ ነገር ላካፍላቹ።
መቐለ 05 ቀበሌ በሚገኝ አንድ ምርጫ ጣቢያ 1140 መራጮች ተመዝግበው ነበር። ከነዚህ ተመዝጋቢዎች በምርጫው የተሳተፉ 619 ብቻ ነበሩ። ከተሳተፉት 370 ደግሞ የምርጫ ምልክት ሳያስቀምጡ በስድብ የታጀቡ ኣስተያየቶች ብቻ የፃፉ ናቸው (ምርጫ ጣብያ ተገደው ቢሄዱም ኣልመረጡም)።
ማይ ሊሓም በሚገኝ አንድ ምርጫ ጣብያ ደግሞ 1201 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን 910 መርጠዋል (ከነዚህ መራጮች ግን 521 የስድብ ኣስተያየት የሰጡ ናቸው)።
አቶ ኣባይ ወልዱ (የህወሓት ሊቀመንበር) የተሳተፉበት በዓዲ ሹምድሑን አከባቢ በሚገኝ አንድ የምርጫ ጣቢያ 1446 የተመዘገቡ መራጮች የነበሩ ሲሆን 945 ሰዎች በምርጫው ተሳትፈዋል። ከነዚህ ተሳታፊዎች 415 ስድብ ብቻ ፅፈው ያስገቡ ሲሆን 202 ደግሞ ነፃ ወረቀት ብቻውን (ምንም ምልክት ወይ ፅሑፍ ሳያስቀምቱ) ወደ ኮረጆው ከተው ተመልሰዋል። 330 ብቻ ድምፃቸው በኣግባቡ ሰጥተዋል።
ባጠቃላይ በመቐሌ (እንዲሁም በትግራይ ክልል ማለት ይቻላል) ተመሳሳይ ነው። በተለይ በመቐለ (በዓይደር፣ 06፣ ዓዲሓ፣ ሓዲ ሓቂ) ጭራሽ ሰው አልመረጠም ማለት ይቻላል። የሚገርመው ነገር የህወሓት አባላት ራሳቸው አለመምረጣቸው ነው። ብዙዎቹ የህወሓት አባላት (ከቀበሌ ሰራተኞች በቀር) በምርጫው ለመሳተፍ ዝግጁ አልነበሩም። ሙሁራንና ነጋዴዎች ወደ ምርጫ ጣብያ ላለመሄድ ተደብቀው የዋሉ ሲሆን አንዳንድ ካድሬዎች የምርጫ ካርዳቸው እየሰበሰቡ ራሳቸው ይመርጡላቸው እንደነበር ተሰምተዋል። በትክክል የመረጡ ጥቂት ሴቶች (የህወሓት አባላት) ብቻ ናቸው።
በምርጫው ቀን ብዙ ህዝብ ባለመሳተፉ የተናደዱ አንዳንድ ባለስልጣናት ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ (እስከ አስር ተኩል) ቤትለቤት እየዞሩ ሰዎች ለምርጫ እንዲወጡ ያስገድዱ ነበር። በኋላ ግን በምርጫ ወረቀቱ (ድምፁ ሲቆጠር) የተፃፉ ስድቦችና አስተያየቶች ካድሬዎቹን እጅግ አስደንግጧል። በኣንድ ምርጫ ጣብያ ኣስመራጮቹ (ታዛቢዎችና ፖሊሶች) ደንግጠው ለኣለቆቻቸው ደውለው ሁኔታው ኣስረድተዋል። እንደዉጤቱም ሦስት ከፍተኛ ባለስልጣናት (የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት) ከምሽቱ አራት ሰዓት በምርጫ ጣብያው የተገኙ ሲሆን በሁኔታው ደንግጠው በሁሉም የምርጫ ጣብያዎች ያለ የድምፅ ቆጠራ ሂደት እንዲቆም አዘዋል። ግን ኣልተሳካም፤ ምክንያቱም ኣብዛኞቹ ቆጥረው ጨርሰው ነበር።
ባለስልጣናቱ ካስደነገጡ የህዝብ ኣስተያየቶች መካከል “ ህወሓት ሌላ፣ ምርጫ አታጭበርብሩ፣ ፍትሕ አጣን፣ ከሌሎች ህዝቦች አታጣሉን፣ በሃይማኖት ጣልቃ ኣትግቡ፣ ድምፃችን ዓፍናቹ ድምፅ እንድንሰጣቹ ትፈልጋላቹ?፣ ሙስና ይቁም፣ በእኩል ዓይን እዩን …” ወዘተ።
ከዚህ በተያያዘ የዉቅሮ ህዝብ ከሌላ አከባቢ ተሽሞ የመጣው የወረዳው ኣስተዳድሪ እንዲቀየር ከፍተኛ ተቃውሞ እያሰማ ይገኛል። የወረዳው ህዝብ የዉቅሮ ተወላጅ ኣስተዳዳሪ ይፈልጋል። ህወሓቶች ግን (በኣብዛኞቹ ሌሎች የትግራይ ወረዳዎች እንደሚያደርጉት ሁሉ) የህዝቡን የተቃውሞ ድምፅ ማዳመጥ ኣልፈለጉም። በኣፅቢ ወንበርታ ወረዳም ተመሳሳይ ችግር ኣለ።
በርግጠኝነት መናገር የምችለው ተቃዋሚዎች በምርጫ ቢሳተፉ ኑሮ በትግራይና አዲስ አበባ ያለ ጥርጥር ያሸንፉ ነበር። ግን ያሸነፉበት ድምፅ በገዢው ፓርቲ ይሰረቅ ነበር።
አዎ! ‘ድምፃችን ዓፍናቹ ድምፅ እንድንሰጣቹ አትጠብቁ’።