Tuesday 24 March 2015

የፌደራል ፖሊሶች በግምገማ ተወጥረዋል

መጋቢት ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት በአዲስ አበባ በተወሰኑ ክፍሎች የሚገኙ የፌደራል ፖሊሶች ተቃዋሚዎችን ይደግፋሉ በሚል መነሻ ጠንካራ ግምገማ እየተካሄደባቸው ነው።
የፌደራል ፖሊሶች ፌስ ቡክ እና ሌሎች የመገናኛ ዘዴዎችን እየተጠቀሙ በተለይ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር ይገናኛሉ በሚል የእጅ ስልካቸውን ተነጥቀው ፍተሻ ተደርጎባቸዋል። ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው እስካሁን በተካሄደው ፍተሻ
ቁጥራቸው እስከ 5 የሚደርስ የፌደራል ፖሊስ አባላት ከግንቦት7 እና ኦነግ ጋር በተያያዘ መታሰራቸው ታውቋል። በሁለት የፌደራል ፖሊሶች የሞባይል ስልኮች ላይ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ፎቶ ተገኝቶባቸዋል በሚል መታሰራቸውን ምንጮች አክለው ገልጸዋል።
ምንጮች እንደሚሉት የአሁኑ ግምገማ 12 የፌደራል ፖሊሶች በተለያዩ ጊዜያት  መሳሪያዎቻቸውን ይዘው መጥፋታቸውን ተከትሎ የተካሄደ ነው።
የፌደራል ፖሊስ አባላት ያለባቸው የስራ ጫናና የሚከፈላቸው ገንዘብ አለመመጣጠን፣  ምንም የትምህርት ደረጃ የሌላቸው ነባር የህወሃት ታጋዮች በተራው የፌደራል ፖሊስ አባል ላይ የሚያደርሱት ጫናና በየጊዜው የሚደረገው አስቸጋሪ ግምገማ ስርአቱን እየተው
እንዲሄዱ እንደሚያስገድዳቸው ምንጮች ይገልጻሉ። አብዛኞቹ የፌደራል ፖሊስ አባላት አዛዦች ነባር የህወሃት ታጋዮች ሲሆኑ፣ የሌሎች ብሄር የፖሊስ አባላትን እንደሚንቁና እንደሚያገሉዋቸው የፖሊስ ምንጮች ይገልጻሉ።

ኢትዮጵያ የአባይ ግድብ ግንባታን በየደረጃው የሚቆጣጠረውን ስምምነት ፈረመች

መጋቢት ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ በጋራ የፈረሙት አዲሱ ስምምነት ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ በሙሉ ነጻነት የምትሰራውን ስራ እንደሚገድብ ከአረብኛ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመው  ሰነድ አመልክቷል።
ሰነዱ ኢትዮጵያ ግድቡን ለመገንባት በምታደርገው ማንኛውም እንቅስቃሴና በየትኛውም የግንባታ ደረጃ ላይ አለማቀፉ አጥኝ ቡድን ለሚሰጠው አስተያየት ተገዢ በመሆን እንድትተገብር ይገልጻል። አጥኝ ኮሚቴው የግድቡ ግንባታ የግብጽንና ሱዳንን የውሃ ድርሻ መጠን
ይቀንሳል ወይም በግብጽና ሱዳን አካባቢያዊ ሁኔታ ላይ ተጽአኖ ያመጣል የሚል ድምደማ ላይ ከደረሰ ካሳ እስከመክፈል የሚያደርስ ግዴታም መጣሉ ተመልክቷል።
አጥኚ ቡድኑ የመጨረሻውን የጥናት ውጤት ይፋ ካደረገ በሁዋላ ሶስቱም አገራት እንደሚቀበሉት የተስማሙ ሲሆን፣ ምናልባት አጥኝ ቡድኑ ግድቡ በግብጽና ሱዳን ላይ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግር ያስከትላል ብሎ ቢወስን ኢትዮጵያ የግድቡን ቅርጽ እስከመቀየር ልትደርስ ትችላለች።
ኢትዮጵያ የምትገነባው ግድብ፣ ከግብጽና ሱዳን የውሃ ማጠራቀሚያዎችን የሚጎዳ ከሆነም ኢትዮጵያ አገራቱን ፈጥና የማሳወቅና ለውጥ ማድረግ እንደሚኖርባትም ስምምነቱ ይገልጻል።
የስምምነቱ አብዛኛው ክፍል ኢትዮጵያ ስለምትፈጽማቸው ግዴታዎች ትኩረት ያደረገ ነው። ግብጽና ሱዳን ለአባይ ወንዝ የሚያበረክቱት የውሃ ድርሻ ካለመኖሩ አንጻር ስምምነቱ በዋነኝነት ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን መብት የሚገድብ ብቻ ሳይሆን፣ የአባይ ግድብ
ግንባታ እጣ ፋንታን ከኢትዮጵያ እጅ አውጥቶ በአለማቀፍ አጥኚዎች እጅ እንዲሆን የሚያደርገው ነው በሚል ትችት እየቀረበበት ነው።
ይሁን እንጅ ሶስቱም አገራት ስምምነቱን በማወደስ ለተግባራዊነቱ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

አርበኞች ግንቦት7 – ህዳሴም ሆነ ዉዳሴ ክህዝብ የሚደበቅ ምንም ነገር የለም!

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyከሰሞኑ አገራችን ኢትዮጵያን በተለይም ብሄራዊ ጥቅሟንና ደህንነቷን በተመለከተ ሁለት አቢይ ዜናዎች የአገራቸን የኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ጉዳዮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸዉን አገሮች የአየር ሞገደች ተቆጣጥረዉት ነበር። ከእነዚህ ዜናዎች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ኢትዮጵያ፤ ሱዳንና ግብፅ የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ ስምምነት ላይ ደረሱ የሚል ዜና ሲሆን ሁለተኛዉ ደግሞ አለም አቀፍ ጋዜጠኞች የህዳሴዉ ግድብ የሚሰራበት ቦታ ድረስ ሄደዉ ባካሄዱት ጥናት መሠረት የህዳሴዉ ግድብ ፕሮጀክት ባጋጠመዉ ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት የተነሳ እንዲዘገይ መወሰኑን የሚያወሳ ዜና ነዉ። አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለሚሰሩ ምንም አይነት ስራዎችና በኢትዮጵያ ህዝብ ስም ከየትኛዉም አገር መንግስትና መንግስታዊ ካልሆነ ተቋም ጋር ለሚደረጉ ስምምነቶችና ዉሎች ሁሉ ባለቤቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ነዉ ብሎ ያምናል፤ ስለሆነም አርበኞች ግንቦት ሰባት የኢትዮጵያን ህዝብ ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት ከሚመለከቱና በሚስጢር መጠበቅ አለባቸዉ ተብሎ ከሚታመኑ አንዳንድ ጉዳዮች ዉጭ ሌላ ምንም ስራ ወይም አለም አቀፍ ስምምነትና ዉል የኢትዮጵያ ህዝብ ሳያዉቀዉና ሳይሰማዉ በድብቅ መደረግ የለበትም የሚል የጸና እምነት አለዉ። ሆኖም ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ አገዛዝ ኢትዮጵያን ከቅኝ ገዢዎች በከፋ መልኩ የሚገዛ የጥቁር ፋሺስቶች አገዛዝ በመሆኑ የሚሰራቸዉ ስራዎችና በአለም አቀፍ ደረጃ የሚፈርማቸዉ ዉሎችና ስምምነቶች የኢትዮጵያን ህዝብ ብሄራዊ ጥቅም የሚጻረሩና የሚጋፉ ድብቅ ስምምነቶች ናቸዉ።
ይህ የወያኔ መሪዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ ጀርባ ላይ ተሸሽገዉ የሚሸርቡት የድብብቆሽ ሴራ ዛሬ የተጀመረ አዲስ ክስተት አይደለም። ባለራዕዩ መሪ የሚል አላስፈላጊ የቅጽል ስም የተሰጠዉ መለስ ዜናዊ በ2004 ዓም ሐምሌ ላይ ከዚህ አለም በሞት ሲለይ ዜናዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተነገረዉ በነኀሴ ወር ማለቂያ ላይ ነበር እሱም ቢሆን ሞትን ያክል ነገር ደብቆ ማቆየት ስለማይቻል ነዉ እንጂ አይነግሩንም ነበር። ከዚህ በተጨማሪ በሰሜናዊዉ የአገራችን ከፍል ወያኔ ከጎረቤት አገር ጋር የተዋዋለዉ መሬት ቆርሶ የመስጠት ዉል የኢትዮጵያ ህዝብ ሳያዉቀዉና ሳይሰማዉ የተደረገ ዉል ወይም ስምምነት ነዉ።
አርበኞች ግንቦት ሰባት አገራችን ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ብቻ ሳይሆን ከግዛቷ ተነስተዉ ወደ ጎረቤት አገሮች በሚፈሱ አለም አቀፍ ወንዞቿና በሌሎችም የአገር ዉስጥ ወንዞቿ ላይ ግደብ የመስራት ማንም ሊጋፋዉ የማይገባ የተፈጥሮ መብት አላት ብሎ ያምናል። በሌላ በኩል ደግሞ አባይን በመሳሰሉ ድንበር ዘለል ወንዞች ላይ የሚሰሩ ምንም አይነት የልማት ፕሮጀክቶች በዛቻና በማንአለብኝነት ሳይሆን በመግባባት፤ በመመካከርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን በሚያዳብሩ መልኩ መሰራት አለባቸዉ ብሎም ያምናል። አርበኞች ግንቦት ሰባት ይህንን የሚለዉ ደግሞ መሠረታዊ ኑሯቸዉ በአባይ ወንዝ ላይ አገሮች ሊያደርሱ የሚችሉትን የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ጫና በመፍራት ሳይሆን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች ከመጀመራቸዉ በፊት ፕሮጀክቶቹን አስመልክቶ ሊነሱ የሚችሉ ዋና ዋና ልዩነቶች መወገድ አለባቸዉ፤ ልዩነቶችን ለማስወገድ ደግሞ የተሻለና አዋጭ የሆነዉ አማራጭ ዲፕሎማሲ ነዉ የሚል ጽኑ አምነት ስላለን በቻ ነዉ።
የወያኔ አገዛዝ እንደ ፈረንጆቹ ዘመን አቆጣጠር በ2011 ዓም የህዳሴዉን ግድብ ስራ ሲጀምር ከአራት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ዶላር ወይም 96 ቢሊዮን ብር በላይ የተገመተዉ ግዙፍ ግድብ ስራ ሙሉ በሙሉ ከአገር ዉስጥ የገንዘብ ምንጮች በሚገኝ ገንዘብ እንደሚሰራና አገዛዙ ግድቡንና የግድቡን ስራ አስመልክቶ ምንም አይነት ድርድር ከማንም አገር ጋር እንደማያደርግ ለለህዝብ ቃል ገብቶ ነበር። የግድቡ ስራ በተጀመረ በጥቂት አመታት ዉስጥ የግድቡ ግንባታ የአገሪቱን የካፒታል ጥሪት ሙጢጥ አድርጎ በመብላቱና በሌሎች በተጀመሩና ሊጀመሩ በእቅድ በተያዙ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ በግልጽ የሚታይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማድረግ በመጀመሩ አለም ባንክ፤ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትና አያሌ ኢትዮጵያዉያን ምሁራን የግድቡ ስራና ግድቡ ላይ የሚፈሰዉ የካፒታል ብዛት እንደገና እንዲታሰብበት ምክር ለግሰዉ ነበር፤ ሆኖም ምክሩ የተሰጠዉ የሚሰማ ጆሮ ለሌለዉ ለወያኔ ነበርና ሰሚ ታጣ። ዛሬ ግድቡ ከተጀመረና ወያኔም በህዳሴዉ ግድብ ላይ ከምንም ከማንም አልደራደርም ካለ ከአራት አመታት በኋላ አንደኛ የግድቡ ፕሮጀክት ስራ በገንዘብ እጥረት የተነሳ እንዲዘገይ ተደርጓል፤ ሁለተኛ ወያኔ የህዳሴዉን ገድብ አስመልክቶ ከግብፅና ከሱዳን መንግስታት ጋር ስምምነት ላይ ደርሶ የፊታችን መጋቢት 14 ቀን ስምምነቱን ለመፈረም ጎንበስ ቀና እያለ ነዉ።
ለመሆኑ ይህ ወያኔ ከሱዳንና ከግብፅ ጋር የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ የሚፈራረመዉ የስምምነት ዉሳኔ ይዘት ምንድነዉ? ዉሳኔዉ በሦስቱ አገር መሪዎች ፊርማ ከመፅደቁ በፊት ለምንድነዉ የዉሳኔዉ ባለቤት የሆነዉ የኢትዮጳያ ህዝብ እንዲያዉቀዉ ያልተደረገዉ? ባለፉት አራት አመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ ምንም አይነት ገቢ ከሌላቸዉ ከተማሪዎችና ከአረጋዉያን ጀምሮ እስከ ቀን ሰራተኛዉ ድረስ ለህዳሴዉ ግድብ ግንባታ ገንዘብ አዋጣ ወይም ቦንድ ግዛ እየተባለ በሩ ያልተንኳኳ ኢትዮጵያዊ የለም። ታዲያ ይህ የኢትዮጵያ ህዝብ በራሱ ገንዘብ ለዕድገቴና ለብልፅግናዬ መሠረት ይሆነኛል ብሎ የሚያሰራዉ ግድብ ስራዉ በገንዘብ እጥረት ሲተጓጎልና በዚሁ ግድብ ዙሪያ ከዉጭ መንግስታት ጋር አለም አቀፍ ስምምነቶች ሲደረጉ ምንም የማይነገረዉ ለምንድነዉ?
የወያኔ መሪዎች ከሱዳንና ከግብጽ መሪዎች ጋር የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ የተዋዋሉትን ዉል እንመራዋለን ብለዉ ከሚናገሩት ህዝብ ቢደብቁም ካርቱምና ካይሮ ወስጥ ሾልከዉ የወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ግብፅ የህዳሴዉ ግደብ ፕሮጀክት ላይ የቁጥጥርና የማነጅመንት ድርሻ አንደሚኖራት እየተነገረ ነዉ። እንደዚህ አይነቶቹ ከዚህ ቀደም በፍጹም የማይሞከሩ ወይም የማይታሰቡ ናቸዉ ተብለዉ ሲነገሩ የነበሩ ስምምነቶችና ዉሎች ዛሬ ተደርገዉና የሶስትዮሽ ስምምነት ተደርሶባቸዉ በፊርማ የሚጸድቁት ግድቡን ሰርቶ ለመጨረስ የሚያስፈልግ ገንዘብ ለማግኘት ነዉ ወይስ ሌላ ድብቅ አላማ አለዉ? ደግሞስ ግድቡ የሚሰራዉ ለህዝብ ግድቡን የሚሰራዉም ህዝብ ሆኖ ሳለ ለምንድነዉ ይህ በዉድም በግድም ገንዘብ ካላዋጣህ ወይም ቦንድ ካልገዛህ እየተባለ ቀንና ማታ ሲጠየቅ የኖረ ህዝብ በዚህ ግድብ ዙሪያ የሚደረጉ ዉሎችንና ስምምነቶችን እንዳያዉቅና ጭራሽ እንዳይሰማ የተደረገዉ? ካይሮና ካርቱም ዉስጥ እንደሚነገረዉ ግብፅ በህዳሴዉ ግድብ ግንባታ ዙሪያ የማነጅመንትና የቁጥጥር ሚና ይኖራታል የተባለዉ ዜና እዉነት ከሆነ እኛ እራሳችን አገራችን ዉስጥ በምንሰራዉ ግድብ ግብፅ ሊኖራት የሚችለዉ የማነጅመንትና ቁጥጥር ድርሻ ዬት ድረስ ነዉ የሚሆነዉ …ለምንስ እንዲህ አይነት ሚና እንዲኖራት ተደረገ?
አርበኞች ግንቦት ሰባት የሶስቱ አገሮ መሪዎች ስምምነቱን በፊርማ ከማጽደቃቸዉ በፊት የኢትዮጵያ ህዝብ ለእንደነዚህ አይነት ቁለፍ ጥያቄዎች መልስ ማግኘት አለበት ብሎ ያምናል። የኢትዮጵያ ህዝብ ኢትዮጵያን አስመልከቶ የሚደረጉ ምንም አይነት ዉሎችና ስምምነቶች ብቸኛዉ ባለቤት ነዉና ከዚህ ህዝብ ተደብቆ የሚደርግ ምንም አይነት ስምምነት ሊኖር አይገባም። ስለዚህም የኢትዮጵያ ህዝብ እነዚህ ከዚህ በላይ ያነሳናቸዉ ጥያቄዎች ጥርት ባለ መልኩ እንዲመለሱለት የወያኔን አገዛዝ ማስጨነቅ አለበት፤ አለዚያ ይህ ጉዳይ ዉሎ ካደረ በኋላ የሚደረገዉ ሩጫ ሁሉ “ቁጭ ብለዉ የሰቀሉትን ቆሞ ማዉረድ ያቅታል” እንደሚባለዉ ይሆናል።
ግብፅና ሱዳን የረጂም አመታት ወዳጅነትና አመታት ያስቆጠረ ወተዳራዊ ስምምነት ያላቸዉ ተጎራባች አገሮች ናቸዉ። እነዚህ ሁለት አገሮች በቅርቡ ከወያኔ ጋር የደረሱበትን ስምምነት “የግብፅን ፍላጎት የሚያረካ” ስምምነት ነዉ እያሉ ካርቱምና ካይሮ ዉስጥ አስተያየት በመስጠት ላይ ሲሆኑ ኢትዮጵያ ዉስጥ ግን ሁሉም ነገር ህዝብ እንዳያዉቀዉ በሚስጢር መያዙ እየታወቀ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት “አዲስ ምዕራፍ” ተከፈተ እያለ የፈረደበትን የኢትዮጵያ ህዝብ መሸንገል ጀምሯል። በሌላ በኩል ደግሞ ወያኔ ሱዳንና ግብፅ በቅርቡ ካርቱም ላይ የደረሱበት ስምምነት እዚያዉ ካርቱም ዉስጥ የፊታችን ሰኞ በሦስቱ አገሮች መሪዎች ፊርማ ይጸድቃል ተብሎ በሚጠበቅበት በአሁኑ ወቅት የግብጹ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታ አል ሲሲ የዉጭ ጉዳይና የዉኃ ኃብት ልማት ሚኒስተራቸዉን አስጠርተዉ ሦስቱ አገሮች የደረሱበትን ሰነድ መርምረዉ ሪፖርት እንዲያቀርቡላቸዉ ማዘዛቸዉ ከወደ ካይሮ ተደምጧል። እንግዲህ ይታያችሁ እኛ ኢትዮጵያዉያን የሦስቱ አገሮች ስምምነት ምን እንደሆነ እንኳን ሳናዉቅ ግብፅ እሷ እራሷ የደረሰችበት ስምምነት አልጥም ብሏት ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጣት ጠይቃለች። ይህ የሚያሳየን አገሮች ለብሄራዊ ጥቅማቸዉና ደህንነታቸዉ ምን ያህል እንደሚጨነቁና አርቀዉ የሚመለከቱ አስተዋይ መሪዎች ደግሞ የሚጨንቃቸዉና የሚያሳስባቸዉ ይህ አሁን የሚመሩት ህዝብ ብቻ ሳይሆን ወደፊት በተከታታይ የሚመጣዉ ትዉልድ ጭምር መሆኑን ነዉ።እኛ ኢትዮጵያዉያን ግን ለእንደዚህ አይነት መሪዎች አልታደልንም። የኛ መሪዎች እንኳን ለሚመጣዉ ትዉልድ ሊጨነቁ ለዛሬዉም ትዉልድ “እኛ ከሞትን ሠርዶ አይበቀል” የሚሉ ስግብግቦች ናቸዉ።
ወያኔ ከራሱ ዉጭ ማንንም የማይሰማ፤ልዩነትን የማያስተናግድና የሌሎችን ሃሳብ ከሱ ሀሳብ የተሻለ መሆኑን እያወቀም ቢሆን የማይቀበል ችኮ መሆኑን በተደጋጋሚ አሳይቶናል። ዛሬ ላይ ቆመን ወደ ኋላ ዞር ብለን የትናንቱን ስንመለከት ወያኔ በህዳሴዉ ግድብ ዙሪያም ገና ከጥንስሱ ጀምሮ ያሳየን ይህንኑ ችኮነቱንና “እኔን ብቻ ስሙ” ባይነት ዕብሪቱን ነዉ። በተለይ የህዳሴዉን ግደብ በተመለከተ አባይ ወንዝ ላይ የሚገነባዉ ግድብ ከዚህ ቀደም በማንም ኢትዮጵያዊ ያልታሰበና የልተወጠነ ፍጹም አዲስ የሆነ ወያኔ ለኢትዮጵያ ያበረከተዉ ገጸ በረከት መሆኑን ለማሳየት ብዙ ጥሯል፤ አንዳንድ የዋሆችን ደግሞ አሳምኗል።ወያኔ ሁሌም ቢሆን ጥረቱና ፍላጎቱ እራሱን ከብጤዉ ከደርግ ጋር እያወዳደረ የተሻለ ሆኖ ለመታየት መሞከር ነዉ እንጂ የተሻለ ስራ መስራት ስላልሆነ በህዳሴዉ ግድብ ላይም አብዛኛዉን ግዜ ያጠፋዉ “አባይን የደፈረ” ተብሎ ለመጠራት ስለሆነ ዛሬ ግድቡ ግንባታዉ አልቆ አገልግሎት መስጠት በሚጀምርበት ወቅት የግድቡ ስራ ከመጀመሩ በፊት ተሰርተዉ ማለቅ የነበረባቸዉን ስራዎች እየሰራ ነዉ።
በቅርቡ አንድ አለም አቀፍ የጋዜጠኞች ቡድን ግድቡ የሚሰረባት ቦታ ድረስ በመሄድ የፕሮጀክቱን እንቅስቃሴ በተመለከተ ጥናት አትንቶ የግድቡ ስራ በከፍተኛ የገንዘብ እጥረት የተነሳ ይዘገያል ብሎ ሪፖርት ማቅረቡ የሚታወስ ነዉ። ጉዳዩን በቅርብ ለምናዉቀዉ ለኛ ለኢትዮጵያዉያን ግን እዉነቱ ከዚህ በላይ ነዉ። የህዳሴዉ ግደብ የሚዘገየዉ በገንዘብ እጥረት ብቻ አይደለም። የዚህ ትልቅ ፕሮጀክት ድህረ ጥናት ሁኔታዎችን የላጤነና ቅደም ተከተሎችን ያላገናዘበ ጎደሎ ጥናት ነበር፤ ከዚህ በተጨማሪ ሩጫዉና ግርግሩ የተጀመረዉ የህዳሴዉን ግደብ የመሰለ ግዙፍ የ96 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት በይድረስ ይድረስ ሰርቶ ለመጨረስ ነበር።
የብዙ አለም አቀፍና የአገር ዉስጥ ኤክስፐርቶች ግምት በግልጽ እንደሚጠቀመዉ የህዳሴዉን ገድብ ግንባታ ጨርሶ አግልግሎት የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ለማድረስ ፕሮጀክቱ በዕቅድ ከተያዘለት በጀት ከሃምሳ በመቶ በላይ ሊያስፈልገዉ ይችላል። ይህ ደግሞ ዛሬ ወያኔን ስለምንቃወም የምናወራዉ ተራ የፕሮፓጋናዳ ጨዋታ ሳይሆን የዛሬ አራት አመት ወያኔ ከበቂ ጥናትና ዝግጅት ዉጭ አባይን እገድባለሁ ብሎ ሲፎክር የዛሬዋ ቀን እንደምትመጣ አዉቀን በተከታታይ ያስጠነቀቅነዉ ማስጠንቀቂያ ስለሆነ ነዉ። ይህ ሁሉ የሚያሳየን ወያኔ አስቀያሚ መልኩን ለማሳመር ሲል ብቻ በኢትዮጵያ ህዝብ ገንዝብና ጉልበት የህፃን ጨዋታ መጫወቱን ነዉ። ሆኖም ዛሬ የሚያስፈራን ይህ ወያኔ የተጫወተበት መጠነ ብዙ የህዝብ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ግድቡን ሰርቶ ለመጨረስ ተጨማሪ ገንዘብ ለማግኘት የሚያደርገዉ አጉል መቅበዝበዝ ነዉ። በእኛ እምነት የህዳሴዉ ግደብ ተሰርቶ ሲያልቅ ኢትዮጵያን ከጥገኝነት ነፃ ማዉጣት ነዉ ያለበት እንጂ ሌላ አላስፈላጊ የሆነ የፖለቲካ ጥገኝነት ዉስጥ ይዞን መግባት የለበትም። ለዚህም ነዉ አርበኞች ግንቦት ሰባት ወያኔ፤ ግብፅና ሱዳን በአባይ ወንዛችን ላይ የሚሰራዉን ግድብ አስመልክቶ ደረስን የሚሉትን ስምምነት ምኑም ሳይደበቅ ለኢትዮጵያ ህዝብ በግልጽ መነገር አለበት እያለ ህዝብንም ወያኔንም የሚያስጠነቅቀዉ። የግብፅና የሱዳን መንግሰታት አገራቸዉ ዉስጥ ህዝብ የሚወዳቸዉ ወይም የሚጠላቸዉ መንግስታት ሊሆኑ ይችላሉ፤ ሆኖም ከዉጭ መንግሰታት ጋር በሚያደርጉት ምንም አይነት ድርድርና ዉይይት ሽንጣቸዉን ገትረዉ የሚቆሙት ለአገራቸዉ ጥቅም ብቻ ነዉ እንጂ ሌላ ከህዝብና ከአገር የተለየ አጀንዳ የላቸዉም። ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ አገዛዝ በተለይ ባለፉት ሃያ አራት አመታት ብቻዉን ስልጣን ተቆጣጥሮ የኖረዉ ህወሓት ግን ከኢትዮጵያ ህዝብ ዘለቄታዊ ጥቅም የተለየ የራሱ የሆነ አጀንዳ አለዉ። አርበኞች ግንባት 7 ህወሓትንና ይህንን ከህዝብና ከአገር የተለየ አጀንዳዉን የማቆሚያዉ ግዜ ዛሬ ነዉና ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፤ ገንዘብ ያለህ በገንዘብህ፤ እዉቀት ያለህ ደገሞ በእዉቀትህ ነገ ሳይሆን ዛሬ ህዝባዊዉን ትግል ተቀላቀል እያለ አገራዊ ጥሪ ያስተላልፋል።

Thursday 12 March 2015

አርበኞች ግንቦት7 – በህወሓት ላይ የሚቀርቡ ተቃውሞዎች ሁሉ ወደ እምቢተኝነት ይደጉ!

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy
የኢትዮጵያ ሕዝብ በአለፉት 23 ዓመታት በህወሓት ዘረኛ አገዛዝ የደረሰበት ስቃይ እንዲቀንስ፤ ገዢዎቹ ከጫንቃው እንዲወዱ፤ ህወሓትን አውርዶ የሚፈልጋቸው መሪዎችን በነፃነት እንዲመርጥ ሲጠይቅና አቤቱታ ሲያሰማ ቆይቷል። በ1997 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሕዝብ ምኞት የሚሳካ መስሎ የታየ የነበረ ቢሆንም በአገዛዙ አረመኔዓዊ እርምጃ ተሰናክሏል። ከጥቂት ዓመታት ወዲህ “ድምፃችን ይሰማ” የሚሉ አቤታዎች ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች መምጣት ጀምሯል – “ድምፃችን ይሰማ ሙስሊሞች”፣ “ድምፃችን ይሰማ ኦርቶዶክሶች”፣ “ድምፃችን ይሰማ መምህራን”፣ “ድምፃችን ይሰማ ተማሪዎች”፣ … ወዘተ። በተለይ ሙስሊም ወገኖቻችን በተደራጀ መንገድ “ድምፃችን ይሰማ” እያሉ ሲወተውቱ ሦስት ተከታታይ ዓመታት አልፈዋል። ወገኖቻችን “ድምፃችን ይሰማ” በማለታቸው ተደብድበዋል፣ ታስረዋል፣ ተገድለዋል።
አቤቱታ የሚሰማ ጆሮ የሌለው አገዛዝ ሲገጥም ምን ይደረጋል? ለአቤቱታ አቅራቢው ያለው ምርጫ ከሁለት አንድ ነው። ወይ አቤቱታን እርግፍ አድርጎ ጥሎ በደልን ተቀብሎ “እህህ !” እያሉ መኖር፤ አሊያም “በቃኝ፣ እንቢ አልገዛም” ማለት፤ ሦስተኛ ምርጫ የለም።
አቤቱታ ሰሚ ሲያጣ እና ሕዝብ መሮት “እንቢኝ፣ አልገዛም” ሲል ነው ሕዝባዊ እምቢተኝነት ተቀሰቀሰ የሚባለው። ሕዝባዊ እምቢተኝነት ብዙ መልኮችና ቅርጾች ቢኖሩትም ዋነኛዎቹ መገለጫዎች ሁለት ናቸው። አገዛዙ ሕዝብ እንዲያደርግ የሚፈልገውን አለማድረግ እና/ወይም አገዛዙ ሕዝብ እንዲያደርግ የማይፈልገውን ማድረግ።
ለምሳሌ፣ አገዛዙ ሹማምንቱ እንዲከበሩ፣ ሕዝብ እንዲታዘዝላቸው ይፈልጋል፤ እንቢ ያለ ሕዝብ ግን የአገዛዙን ሹማምንት ይንቃል፣ በየደረሱት ያዋርዳቸዋል፣ “አልታዘዛችሁም” ይላቸዋል። ማንኛውም መንግስት የዳኝነት ሥርዓቱ እንዲከበርለት ይፈልጋል፤ በደል የመረረው ሕዝብ ግን የአምባገነኖች ችሎት ውሳኔ አይቀበልም፤ ዳኞችንም ዳኝነትንም አያከብርም። ሕዝብ የመንግሥትን ግብር በወቅቱ እንዲከፍል የማንኛውም መንግሥት ፍላጎት ነው። በመንግሥት ያመረረ ሕዝብ ግን ግብር አይከፍልም፤ መክፈል ግድ ከሆነበትም አዘግይቶ፣ አስለፍቶ ነው። የመረረው ሕዝብ ምሬቱን መፃፍ በሌለበት ቦታ ይጽፋል። በደል የበዛበት ሕዝብ “ዝም በል” ሲሉት ይናገራል፤ “ተናገር” ሲሉት ዝም ይላል።
አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ የሕዝባዊ እምቢተኝተኝነት እርምጃዎች ጅምሮች እየታዩ ነው። በአማራ ክልል፣ ሕዝብ በሹማምንት ላይ የራሱን እርምጃ መውሰድ ጀምሯል። ሕዝብ ራሱ የፓሊስንም የፍርድ ቤትንም ሥራ ተክቶ እየሠራ ነው። ይህ መበረታታት ያለበት ትልቅ እርምጃ ነው። እንደዚሁም ሁሉ በተለይ ወጣቶች ብሶቶቻቸውን በብር ኖቶች ላይ ጽፈው ገበያው እንዲያዘዋውራቸው እያደረጉ ነው። ይህም “የወረቀት ገንዘብን ለተሠራበት ዓላማ ብቻ ተጠቀሙ” የሚለውን ህግ በመጣስ ለቅስቀሳ ሥራ መጠቀም በመሆኑ የሕዝባዊ እምቢተኝነት አካል ነው። በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ በርካታ የወረቀት ገንዘቦች በምሬት መግለጫነት ይውላሉ ተብሎ ይገመታል።
በተጓዳኝ በርካታ አማራጭ ስልቶች ሥራ ላይ መዋል ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ ተቀማጭ ገንዘብን ከህወሓት ባንኮች ማውጣት በቀላሉ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል ስልት ነው። በውጋጋን ባንክ ተጀምሮ ወደ አንበሳ ኢንተርናሽናል ከዚያም ወደ ንግድ ባንክ ማሸጋገር ይቻላል።
በወገኖቻችን ላይ የግፍ ፍርድ የሚያስፈርዱ አቃቢያነ ህግ እና የግፍ ብይኖችን የሚሰጡ ዳኞች በቸልታ ሊታለፉ አይገባም። በእስር ቤቶችም በወገኖቻችን ላይ ሰቆቃ እየፈፀሙ ያሉ ጨካኞች ከሰላማዊ ሕዝብ ጋር ተደባልቀው ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ ሊፈቀድላቸው አይገባም። እነዚህ ሁሉ ሊወገዙ፣ ሊገለሉ፣ በየደረሱበት ሊዋረዱ ይገባል።
በአገዛዙ መንግሥታዊ መዋቅር ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችን በሥራቸው ላይ መለገም ተቀባይነት ያለው በጎ ተግባር እንደሆነ ሰፊ ግንዛቤ ሊያገኝ ይገባል። ከአምባገነን ሥርዓት ጋር መተባበር እኩይ ተግባር ሲሆን አምባገነን ሥርዓትን ከውስጥ መቦርቦር ደግሞ የሚበረታታ ሰናይ ሥራ ነው።
ለወያኔ አገዛዝ ግብር መክፈል የምናቆምበት ሰዓትም ተቃርቧል። በራሳችን ገንዘብ ገዳዮቻችን እንዲሰለጥኑብን መፍቀድ የለብንም። ስለሆነም “ግብር አንከፍልም”፤ “መዋጮዎቻችሁ አይመለከቱንም” የምንልበት ቀን ቀርቧል።
በፋይዳ የለሽ ምርጫ የሀገር ሀብት ሲመዘበር ማየት አንሻም። በአግባቡ ለማይቆጠር ድምፃችን አንድም ደቂቃ የምናባክንበት ምክንያት የለምና ሁላችንም የምርጫ ካርዶቻችንን ቀዳደን ቁርጭራጮቹን በየመንገዱ ልንበትናቸው ይገባል።
እነዚህን እነዚህን የመሳሰሉ ናቸው የሕዝባዊ እምቢተኝነት የመጀመሪያ ደረጃዎች። እነዚህን እያደረግን በምስጢር መደራጀታችንን እንቀጥል። ከጥቂት በኋላ አምባገነኑን ሥርዓት የሚያንበረክክ ኃይል እንፈጥራለን። ጥቃት ቢደርስ የሚመክት ኃይል የተደራጀ በመሆኑም ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አመጽ ተቀናጅተው እንዲሄዱ ይደረጋል።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሕዝባዊ እምቢተኝነትንና ሕዝባዊ አመጽን አቀናጅቶ ለመምራት የተዘጋጀ፤ ለዚህ የሚያበቃው ድርጅታዊ አቅም እየገነባ ያለ ድርጅት ነው። አርበኞች ግንቦት 7 “እንሰባሰብ በወያኔ ላይ የምናቀርባቸው ተቃውሞዎች በሙሉ ወደ እምቢተኝነት ከፍ እናድርጋቸው” ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የዲሞክራሲዊለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ድጋፍ አሰባሳቢ ጊዜያዊ ግብረ ኃይል የተሰጠ የአቋም መግለጫ !!

የባዕዳን ወራሪዎች ለሃገራቸው ቀናኢ በሆኑ ጀግኖች አባቶቻችን አይቀጡ ቅጣት ተቀጥተው ነጻነታችንን የተቀዳጀንበት እንዲሁም ለጥቁር ህዝብ አርአያ የሆንበት 119 የአድዋ በዓል በሚከበርበት በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ ህዝብ ማንነቱ ተዋርዶና ተንቆ በጥቂት ዘረኛ ፋሽስቶች  እየደረሰበት ያለው ግፍና መከራ ውሎ እያደረ እየመረረና እየከረፋ መምጣቱ ከማንም ኢትዮጵያዊ የተሰወረ አደለም፡፡
DCESON
አንባገነኑ ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ ከመቼውም ጊዜ በባሰ ሁኔታ በሃገርና በህዝብ ላይ እያደረሰ ያለው ሰቆቃ ለመታገል ኢትዮጵያንና ህዝቧን አስተማማኝ መሰረት ያለው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ባለቤት ለማድረግና ከዚህ በዘር ከተደራጀ የሃገርና የህዝብ ጠላት ነጻ ለማውጣት በውጪም ሆነ በውስጥም ውድ ህይወታቸውን ለመስዋእትነት ያቀረቡና ለማቅረብ የተዘጋጁ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች መኖራቸው ይታወቃል፡፡ ይሁንና ይህው ዘረኛዉ የወያኔ ሥርዓት ከወትሮው በረቀቀ መልኩ በሃገር ውስጥ የሚደረገውን የነጻነት ትግል ለማዳፈን ከማሰርና ከማሰቃየት በዘለለ ባስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ደፋ ቀና የሚሉ አውራና በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን የህዝብ ፓርቲዎች ሌት ተቀን የሚዘምርለት የይስሙላ ምርጫ ከመድረሱ በፊት የሥርዓቱ ክንፍ በሆነው የወያኔ ምርጫ ቦርድ ተብዬው አማካኝነት በነጻነት የመደራጀት መብታቸውን በመግፈፍ እንደበታተናቸውና ምርጫው ከመካሄዱ ከወራት በፊት ለተጨማሪ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ራሱን ለመጫን ብቻውን እሮጦ ብቻውን የሚያሸንፍበትን ጥርጊያ መንገድ እያመቻቸ መሆኑ በገሃድ እየታየ ነው፡፡
በሕዝብ ና በሃገር ላይ እየደረሰ ያለውን መረን የለቀቀ የዘረኛውን ቡድን  እኩይ ተግባር  እምቢኝ በማለት በውስጥም ሆነ በውጪም የሚደረገው እልህ አስጨራሽ ትግልና በኢትዮጵያችን እውን እንዲሆን የምንፈልገውን ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ስብዓዊ መብቱ ተከብሮ በነጻነት የሚኖርባት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባትና ዘረኛውን የወያኔ ሥርዓት ለማስወገድ ያላሰለሰ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡

ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ከዚህ ከፋፋይ የዘረኛ ሥርዓት ለማላቀቅ የሚደረገው ትግል ለጥቂት የህብረተሰብ ክፍል የሚተው ሳይሆን ኢትዮጵያ እንደ ሃገር እነድትቀጥል የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ማድረግ የሚችለውን በማድረግ ሃገራዊ ግዴታውን የሚወጣበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የተደረሰበት ወቅት ነው፡፡

ስለሆነም በኖርዌይ የምንኖር ኢትዮጵያዊያን የነጻነት ትግሉ የሚጠይቀውን ሃገራዊ ጥሪ እንደ ከዚህ ቀደሙ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠትየዲሞክራሲዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ  በአፕሪል 18፣2015 በዓይነቱ ልዩ የሆነ ታላቅ ሕዝባዊ ሥብሰባና የነጻነት ትግሉን የሚያግዝ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አዘጋጅቷል፡፡

በመሆኑም በሃገራችንና በሕዝቧ ላይ ቀን ከሌት የሚደርሰው ሰቆቃ የሚያሳስበው፣ በወገኖቻችን ላይ በተለይ እምቢኝ ለሃገሬ እምቢኝ ለሕዝቤ ባሉ ንጹሃን የህሊና እስረኞች ላይ የሚደርሰው ዘግናኝ ሰቆቃ እንደወገን የሚቆጨው፣ ከአያት ቅድመ አያት ሲወርድ ሲዋረድ የመጡት የዕምነት ተቋማት እንዲሁም ማህበራዊ እሴቶቻችን  በዚሁ ዘረኛ ቡድን መደፈርና መዋረድ ያስቆጣው፣  ምስኪኑ የሃገራችን ገበሬ ከቤት ንብረቱ መፈናቀል ለህሊናው የከበደው ፣. . . . . . . . ይህንንና ይህንን የመሳሰለ በሃገርና በሕዝባችን ላይ የሚደርሱ ተነግረው የማያልቁ ሰቅጣጭ በደሎችን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከነ ሥርዓቱ ለማስወገድ ከላይ በተጠቀሰው ቀን በሚደረገው ሃገራዊ ጥሪ ላይ በመገኘት የበኩልን ያድርጉ!! ለሚደረገው የነጻነት ትግል አጋርነትዎን በተግባር ያስመስክሩ!!!!
ቀኑ፣ አፕሪል 18፣ 2015
ሰአት፣ 15፣00 እስከ 22፣00
ቦታ ከተጨማሪ ማብራሪያ ጋር በቅርብ ቀን ይገለጻል

የፌስቡክ ኤቨንት ገጻችንን ይጎብኙ እንዲሁም በዝግጅቱ ላይ እንደሚመጡ ያረጋግጡ በተጨማሪም ጓደኛዎትን በዚህ ሃገራዊ ጥሪ ላይ ይጋብዙ፣
https://www.facebook.com/events/445434435611079/

ነፃነት፣ ፍትህ፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!
ኢትዮጵያ በልጆቿ ደምና አጥንት መስዋዕትነት ለዘላለም ተከብራ ትኖራለች !!!
የዲሞክራሲዊለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ !!
675

Monday 9 March 2015

የኢትዮጵያ ጠላት ወያኔ – ወያኔ ብቻ ነዉ!

pg7-logoባለፈዉ ሳምንት አይጋፎረም የሚባለዉና የወያኔን ቱልቱላ በዉጭ አገሮች የሚያናፍሰዉ ድረገጽ ከነብስ አባቱ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ በአደራ የተሰጠዉን አንድ የመላምት ድርሰት የፊት ለፊት ገጹ ላይ ለጥፎት የህዝብን ስሜት የኮረኮረ እየመሰለዉ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ ከሁለት ሺ አመታት በኋላ ይሁዳዊ ክህደት ሲክድ እጅ ከፍንጅ ተይዟል። የሚገርመዉ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዝሙር ሆኖ ሳለ ያንን የመሰለ የክህደት መንፈስ ልቡ ዉስጥ ያስቀመጠለት ሰይጣን እንደሆነ ሁሉ አዲስ ዘመንና አይጋ ላይ የወጣዉን ጽሁፍ የጻፈዉ ግለሰብም የወያኔ ጌቶቹን ምክር ተቀብሎ አሜን አለ እንጂ የዚህ የዉሸት ድርሰት ጠንሳሾች በሰይጣን የሚመሰሉት የወያኔ መሪዎች ናቸዉ። የጽሁፉ ደራሲ ነኝ ግለሰብ የወያኔን ትዕዛዝ ከመቀበል ዉጭ ያደረገዉ ነገር ቢኖር ስሙ ከፅሁፉ አርዕስት ስር እንዲቀመጥ መፍቀዱ ብቻ ነዉ – ለዚያዉም የብዕር ስም!
አገሮች፤ ድርጅቶች ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች የፕሮፓጋንዳ ጦርነት ዉስጥ ሲገቡ በዉሸት ዉስጥ እዉነት ወይም በእዉነት ዉስጥ ዉሸት እየሸነቆሩ ነዉ የፕሮፓጋንዳቸዉ ኢላማ የሆነዉን የህብረተሰብ ክፍል ቀልብ ለመግዛት የሚፍጨረጨሩት እንጂ ዉሸትን በዉሸት ለዉሰዉ ቢያቀርቡማ ህዝብ እንኳን ሊያምናቸዉ ደግሞ ሊሰማቸዉም ፈቃደኛ አይሆንም። ይህ ከሰሞኑ አይጋፎርምና አዲስ ዘመን ላይ የወጣዉ ጽሁፍ ግን ምንም አይነት የፕሮፓጋንዳ ህግ አይከተልም፤ ምክንያቱም ጽሁፉ የተጻፈዉ ህግ የሚባል ነገር በሌለባትና ወያኔና ግብረ አበሮቹ እራሳቸዉ ህግ በሆኑበት አገር ዉስጥ ነዉ። ጽሁፉ ሲጀምር በዉሽት ይጀምርና መሀል ላይ ዉሸቱን በዉሸት አጠናክሮ በዉሸት ይደመደማል። እንደዚህ አይነት የዉሽት ክምር የሚመጣዉ ደግሞ ከሌላ ከየትም ሳይሆን በዉሸት ተወልደዉ፤ በዉሸት አድገዉ በዉሸት ከሸበቱት የወያኔ መሪዎች ብቻ ነዉ። ዉድ አድማጮቻችን የዚህ ጽሁፍ አላማ ለሻዕቢያ ጥብቅና መቆም አይደለም፤ ሻዕቢያ ከኛ በላይ ለራሱ ጥብቅና መቆም ይችላል። የዚህ ጽሁፍ ብቸኛ አላማ የኢትዮጵያ ህዝብ ገንበዙን፤ ሀብቱንና ጉልበቱን አስተባብሮ መዋጋት የሚገባዉ ቀንደኛ ጠላቱ ወያኔ መሆኑን መናገር ነዉ። ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ትናንት ሲከናዉን የምናዉቀዉንና አይናችን ፊት ተፈጽሞ ከ “ሀ” ወደ “ፐ” የተጻፈዉን ታሪክ ዛሬ ወያኔና ቡችሎቹ ከ “ፐ” ወደ “ሀ” ሲያነብቡትና የኢትዮጵያን ህዝብ ለማሳሳት ሲሞክሩ ዝም ብለን አንመለከትምና ይህንን የዉሸት ክምር ከመሰረቱ መናድ እንፈልጋለን።
ይህንን በዉሸት የተጀቦደ የወያኔ ቡትቶ እንዳለ ማቅረቡ የአድማጭን ጆሮ ማደንቆር ስለሚሆን አንሞክረዉም። ሆኖም ወያኔ በተከበበና አንድ እርምጃ ወደማይቀረዉ ዉድቀቱ በቀረበ ቁጥር የሚመዝዛቸዉን አገር የሚገዘግዙ መጋዞች የኢትዮጳያ ህዝብ ከአሁኑ አዉቆ እንዲጠነቀቅ ስለምንፈልግ የፅሁፉን ጎላ ጎላ ያሉ የዉሸት ምሶሶዎች እንዳሉ ለማቅረብ እንገደዳለን።
የመመሪያዉ አይን ያወጣ ዉሸት “በወቅቱ ኢሕአዴግ ከበረሀ ይዞት የመጣው መደበኛ ያልሆነ ሰራዊት ብቻ በእጁ ነበር። ቀድሞ የነበረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሀይል፣ የምድር ጦሩ፣ ታንከኛው፣ መድፈኛው፣ አየር መከላከያው፣ አየርሀይሉ፣ ባህር ኃይሉ፣ ኮማንዶው ሰራዊት፣ ፖሊስና ሌሎችም ሙሉ በሙሉ ተበትነዋል” ይላል። ይህ ዉሸት ከተለመዱት የወያኔ ተራ ዉሸቶች ጋር ሲተያይ ተጠንቶበት በጥንቃቄ የተዋሸ ዉሸት ይመስላል። የቀድሞዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ወራዊት ሰራዊት አባላት በገዛ ፈቃዳቸዉ የተበተኑ ይመስል የዚህ ጽሁፍ ጸሀፊ የቀድሞዉ የመከላከያ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተበትነዋል እያለ ነዉ የሚነግረን። በእርግጥም ቁጥሩ ከ300 መቶ ሺ በላይ የሚሆን ሰራዊት የኢትዮጵያ ሠራዊት መሆኑ ተረስቶ የደርግ ጦር፤ የትምክህተኞች ኃይል ወይም የነፍጠኞች ምሽግ እየተባለ በወያኔ ዘረኞች ተበትኖ በምትኩ በአንድ ዘር የበላይነት ላይ የተመሰረተ የመከላከያ ኃይል ተገንብቷል። የቀድሞዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የማን ሠራዊት እንደነበር፤ ለምንና በማን እንደተበተናና በምትኩም የተገነባዉ ሠራዊት ለማን ጥቅም እንደቆመ የኢትዮጵያ ህዝብ አንደ ጥቁር ነጭ ለያይቶ የሚያዉቀዉ ሀቅ ነዉና ከዚህ በላይ የምንለዉ ምንም አይኖርም።
ከአንድ ወር በፊት የኢትዮጵያ ሳቴላይት ቴሌቭዥንና ሬድዮ ጋዜጠኞች በኢትዮጵያና በኤርትራ ህዝብ መካከል ሊኖር የሚገባዉን ግኑኝነትና ኤርትራ ዉስጥ እየተካሄደ ነዉ የሚባለዉን የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት ትግል እንቅስቃሴ አስመልክቶ እዉነቱን ለህዝብ ለማሳወቅ ታሪካዊ ጉዞ ወደ አስመራና የኤርትራ በረሀዎች አድርገዉ ነበር። በጉዟቸዉ ወቅት ጋዜጠኞቹ ሰፋ ያሉ ጉዳዮችን የዳሰሰ ቃለ መጠይቅ ከኤርትራዉ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር አድርገዉ ነበር። ይህ ማን ምን ሰራ የሚለዉን ጥያቄ በታሪክ ወደ ኋላ እየሄደ የሚመልሰዉና በአይነቱ ልዩ የሆነዉ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለመጠይቅ በመገናኛ አዉታሮች መሰራጨት ሲጀምር የኢትዮጵያ ህዝብ ከደደቢት ዉሸትና ተረት ዉጭ ሌላ ሲሰማ የሚያመዉ ወያኔ እንደለመደዉ ሲወራጭና እዉነትን ለመጋረድ ሲፍጨረጨር ታይቷል።
የኢትዮጵያን ህዝብ እንዳሰኛቸዉ የሚረግጡት፤ የሚያስሩት፤ የሚገድሉትና በተለይ በቅርቡ የመስፋፋትና የማፈናቀል ፖሊሲያቸዉን የሚቃወመዉን ሁሉ “ልክ እናስገባዋለን” ብለዉ የዛቱት የወያኔ መሪዎች የእነሱን ጠላትነትና ስር የሰደደ ፀረ ኢትዮጵያ አቋም ሸፍነዉ ኤርትራን የኢትዮጵያ ዋነኛ ጠላት አድርገዉ ማቅረብ ጀምረዋል። የሚገርመዉ ይህ ሁሉ አልበቃ ብሏቸዉ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ በኢሳት ቴሌቪዥን በሚተላለፍበት ወቅት በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይ ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ ቀድሞዉኑም ከብልጭ ድርግም አልፎ የማያዉቀዉን አሌክትሪክ ጭራሽ እንዲጠፋ አድርገዋል።
ሻዕቢያና ህወሓት የትጥቅ ትግል በሚያካሄዱበት ግዜ የተነሱበትን ዋነኛ አላማ ለማሳካት የተለያዩ የፕሮፓጋንዳ ጨዋታዎችን ተጫዉተዋል። ከእነዚህ የፕሮፓጋንዳ ጨዋታዎች ዉስጥ አንዱ ኢትዮጵያ ኤርትራን በቅኝ ግዛትነት ይዛለች የሚለዉ ፕሮፓጋንዳ ነዉ።የሚገርመዉ ይህንን ፕሮፓጋንዳ ከባለቤቱ ከሻዕቢያ ይበልጥ የተሸከመዉና ያርገበገበዉ ህወሓት ህወሓት ዉስጥ ደግሞ መለስ ዜናዊና ስብሀት ነጋ ናቸዉ። ይህ ደግሞ ዛሬ እኛ ፈጥረን የምናወራዉ ወሬ ሳይሆን በቦታዉ የነበሩና ህወሓትን የፈጠሩት እን ገብሩ አስራትና እነ ገ/መድህን አርአያ በግልጽ የሚናገሩት እዉነት ነዉ። የትናንቱን የኢህአፓ የበረሃ ዉስጥ ታሪክ ትዝ ለሚለን ደግሞ ህወሓትንና ኢህአፓን ጦር አማዝዞ ለአያሌ ኢትዮጵያዉያን ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆነዉ ኢህአፓ ይህንኑ የወያኔን ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ናት የሚለዉን መዝሙር አልዘምርም በማለቱ ነበር። እንግዲህ ዛሬ ይህ ሁሉ መረጃና ይህ መረጃ በእጃቸዉ ላይ ያለ ሰዎች በህይወት እያሉ ነዉ የወያኔ አይነ አዉጣዎች “ከመጀመሪያዉም ሻዕቢያ እንደሚለፈልፈዉ ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት አልነበረችም፤ ይህ የእነ ኢሳያስ እብደት ነዉ እያሉ የራሳቸዉን ቀን የቆጠረ ዕብደት የሚነግሩን። በ1967 ዓም እግራቸዉ የደደቢት በረሃን ከረገጠበት ግዜ ጀምሮ በ1983 ዓም አዲስ አበባን እስከተቆጣጠሩበት ግዜ ድረስ በወዶ ገባነት ከገበቡበት ከሻዕቢያ ጉያ ያልተለዩትና አጠገባቸዉ ያለችዉን አክሱም ፅዮንን ትተዉ ሻዕቢያን ሲሳለሙ የከረሙት የወያኔ መሪዎች ዘንድሮ ሳይታሰብ በድንገት ቀኝ ኋላ ዙር ብለዉ ከሻዕቢያ ጋር የነበራቸዉን አለመግባባት መናዘዝ ጀምረዋል። በተለይ “ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ናት” ብለዉ እራሳቸዉ በጻፉት ማኒፌስቶ ዉስጥ ያሰፈሩትን ቃል ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ የረሳ መስሏቸዉ የክህደት ጫጫታ መደርደር ጀምረዋል።
አገራችን ኢትዮጵያ በየዘመኑ በአንድነቷና በሉዓላዊነቷ ላይ የዘመቱ ብዙ ታሪካዊ ጠላቶች ነበሯት፤ ዛሬም አሏት፤ ሆኖም የኢትዮጵያ ህዝብ በረጂም ዘመን ታረኩ ዉስጥ እንደ ወያኔ ህልዉናዉን፤ አንድቱንና የወደፊት ተስፋዉን ያጨለመበት የዉጭም የዉስጥም ጠላት አጋጥሞት አያዉቅም። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች መብታቸዉ፤ ነጻነታቸዉና እኩልነታቸዉ ተከብሮ የኖሩበት ዘመን ባይኖርም ኢትዮጵያ እንደ ወያኔ ዘመን በዘር የተከፋፈለችበትና የመበታተን አደጋ ያጋጠማት ግዜ የለም። ዛሬ የኢትዮጵያን አንድነትና የህዝቦቿን መብትና ነጻነት መከበር አጥብቀዉ የሚሹ ወገኖች ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሊዋጉት የሚገባ ብቸኛ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት ጠላት ወያኑ ወይም ህወሓት ነዉ። የኢትዮጵያህዝብ መከፈል የሚገባዉን መስዋዕትነት ከፍሎ ወያኔን በአጭር ግዜ ዉስጥ ካላስወገደ የአገራችን ህልዉና በቀላሉ የማይጠገን አደጋ ዉስጥ መዉደቁ አይቀርም።
ይህ የአገራችን አንድነት አደጋ ላይ የመዉደቁ ዜና እጅግ በጣም የሚያስፈራና የሚያሳዝን ዜና ነዉ። ደግነቱ የሚያስደስተን፤ ተስፋችንን የሚያለመልምና አንገታችንን ቀና የሚያሰደርግ ዜናም አለ። ወያኔ አገራችን ላይ ይዞት የመጣዉ አደጋ ከወዲሁ የታያቸዉ ኢትዮጵያዉያን የአባቶቻችዉን ፈለግ ተከትለዉ ዱር ቤቴ ብለዉ ወያኔን በሚገባዉ ቋንቋ ለማነጋገር ተዘጋጅተዋል።የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔንና ወያኔ የፈጠረዉን ዘረኛ ስርዐት ደምስሶ ፍትህ፤እኩልነትና ነጻነት የሰፈነባትን ኢትዮጵያ ለመገንባት በሚየደርገዉ ትግል የመጀመሪያዉ ምዕራፍ ዉስጥ እንደ ኤርትራ ህዝባነ መንግስት አጋር ሆኖ የተሸከመዉ ሌላ አገርም መንግስትም የለም።የኤርትራ ህዝብና መንግሰት ወያኔ የሚባል ነቀርሳ ከስሩ እስካልተነቀለ ድረስ የአፍሪካ ቀንድ የሰላም አየር እየተነፈሰ በሠላም መኖር እንደማይችል ከተረዱ ቆይተዋል። ስለዚህም ነዉ የኢትዮጵያን ህዝብ የነጻነት አርበኞች አስጠግተዉ አስፈላጊዉን እርዳታ ሁሉ የሚያደርጉላቸዉ። ዛሬ ኢትዮጵያንና ኤርትራን የሚመሩ መሪዎችና መንግስታት ዘሏአለማዊ አይደሉም፤ የሁለቱ አገሮች ህዝብ ወንድማማችነትና ጉርብትና ግን ዘለአለማዊ ነዉ። በዚህ ዘሏአለማዊ ወዳጅነትና ጉርብትና ዉስጥ የስግብግቦቹ የወያኔ መሪዎች አመለካከት “እኔ ከሞትኩ ሠርዶ አይብቀል” ካለችዉ እንስሳ የሚለይ አይደለም።ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለመጠይቅ በግልጽ እንደሰማነዉ በኤርትራ በኩል ያለዉ አመለካከት ለኢትዖጵያነ ለኤርትራ ህዝብ ታሪካዊ ትስስር፤ ጉርብትናና ወደፊት ወዳጅነት እጅግ በጣም ከፍተኛ ግምት የሚሰጥ አመለካከት ነዉ። አርበኞች ግንቦት ሰባትና የኤርትራ መንግስት በኤርትራና የኢትዮጵያ ህዝብ የተሳሰረ የጋራ ዕድገት፤ ብልጽግናና መልካም ጉርብትና ላይ እንደ ነቀርሳ የተተከለዉ ዘረኛዉ የወያኔ ስርዐት ነዉ ብለዉ ያምናሉ። ይህ ነቀርሳ በተባበረ የህዝብ ትግል መነቀል አለበት ብለዉም ያምናሉ።
“አህያዉን ፈርቶ ዳዉላዉን እንዲሉ” ዛሬ ወያኔ “ኤርትራ” “ኤርትራ” እያለ የአዞ የሚያነባዉ እሱ ባልተገራ አንደበቱ ሊነግረን እንደሚፈልገዉ ኤርትራ በእርግጥም የኢትዮጵያ ጠላት ሆና አይደለም። ጉዳዩ ወዲህ ነዉ። ወያኔ በኤርትራ አሳብቦ ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ነጻነት የቆሙ ኃይሎችን ቆርጦ ተነስቷል፤ ይህንን ለማወቅ ደግሞ ብዙ መረጃ መሰብሰብ አያስፈልግም። እራሳቸዉ የወያኔ መሪዎች በየመድረኩ የተናገሩትንና ቡችሎቻቸዉ ደግሞ በቅርቡ አዲስ ዘመን ላይ የጻፉትን ጽሁፍ ማንበቡ ይበቃል – እንዲህ ሲሉ ነበር የጻፉት “አለም አቀፍ ሕጉን ማክበር በሚል እንጂ ዛሬ ይህንን ደባና ሴራውን በጣጥሦ በመጣል ከነሎሌዎቹ ድባቅ በመምታት ከነበረ ወደአልነበረ በመለወጥ ያለአንዳች እንቅፋት ይሕንን ዘመን የማይሽረው ጸረ ኢትዮጵያ ሀይል ሙሉ በሙሉ በመደምሰስ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና እፎይታ ማስገኘት ይቻላል፡፡ ኢትዮጵያ ቆርጣ ስትነሳ የሚገታት አንድም ሀይል የለም” የኢትዮጵያ ወጣት፤ ሠራተኛ፤ ገበሬ፤ የመከላከያ ሠራዊት አባላትና ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ወያኔ ምን ያህል አንተንና አገርህን አንደሚጠላ ባለፉት ሃያ አራት አመታት በግልጽ አሳይቶሀል። ዘንድሮ ደግሞ በተለይ ባለፉት ሦስት ሳምንታት አንተና ልጆችህ በየቀኑ እያደገ በሚሄደዉ የኑሮ ዉድንት እየነደዳችሁ ወያኔ ግን አገራችንን በዘር ከፋፍሎ ለመግዛት የመሠረት ዲንጋይ ያኖረበትን ቀን ለማክበር ከአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ አባክኗል። ከዚህ በተጨማሪ ነብሰ ገዳይ ፖሊሶቹን አሰማርቶ አባቶችህ አድዋ ላይ ያጎናፀፉህን አንጸባራቂ የጥቁር ህዝብ ድል በሆታና በእልልታ እንዳታከብር አድርጓል።
ባጠቃላይ አርባኛዉ አመት የህወሓት ምስረታና የኢትዮጵያ ህዳሴ የሚል አዲስ የመላምት ታሪክ እንዲጻፍ እያደረገ በአባቶችህና በእናቶችህ ደም የደመቀዉን ትልቁን የአድዋ ድል ታሪክ እንዲደበዝዝ አድርጓል። የኢትዮጵያ ህዝብ ጨዋ ነዉ- በእርግጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ጨዋ ነዉ። ኢትዮጵያዉያን ታጋሾች ናቸዉ? ያለምንም ጥርጥር ኢትዮጵያዉያን አለም የሚያዉቃቸዉ ታጋሾች ናቸዉ። ነገር ግን ትዕግስትም ሆነ ጨዋነት ትርጉም የሚኖራቸዉ ህዝብ መብቱና ነጻነቱ ተከብሮ በማንነቱ ኮርቶ መኖር ሲችል ብቻ ነዉ። እየተረገጠ፤ ልጆቹ ከጉያዉ እየተወሰዱ እየተረሸኑና ታሪኩ ፤ አንድነቱና ብሄራዊ ማንነቱ ሲዋረድ የሚታገስና አንገቱን ደፍቶ የሚኖር ህዝብ የለም። በሳምንቱ መግቢያ ላይ ያከበርነዉ የአድዋ ድል በዐልም የሚያሳስበን ይህንን እዉነት ነዉ። የዚህ ዘመን ኢትዮጵያዊ አባቶቹና እናቶቹ በነጭ ፋሺስቶች ላይ በተጎናፀፈት የአድዋ ድል መኩራት ብቻ ሳይሆን የሱም ልጆች አባቶቼ ብለዉ አንዲኮሩበት የአድዋን ድል በዛሬዎቹ ጥቁር ፋሺስቶች ላይ መድገም አለበት። አድዋ የእኛ የኢትኦጵያዉያን ብቻ ሳይሆን የአለም ጥቁር ህዝብ በነጭ ወራሪዎች ላይ የተጎናፀፈዉ አንፀባራቂ ድል ነዉ። አድዋ ትዕግስትና ጨዋነት ለማይገባቸዉ እብሪተ ችና ትዕቢተኞች ቆራጡና ጀግናዉ የኢትዮጵያ ህዘብ የማይረሳ ትምህርት ያስተማረበት ቦታ ነዉ። ዛሬ ደጃፋቸዉ ላይ የኢትዮጵያ ህዝብ የሰራዉን ገድል የረሱና አድዋ ላይ ታሪክ ሲሰራም ቢሆን ባንዳዎች የነበሩ የባንዳ ልጆች ከቅኝ ገዢዎች ባልተለየ ጭካኔ፤ ዝርፊያና ጥላቻ አገራችን ኢትዮጵያን እንዳልነበረች እያደረጓት ነዉ። የዛሬዉ ትዉልድ ኢትዮጵያዊ ከዚሁ ከአድዋ አፈር በቅለዉ በራፋቸዉ ላይ ህዝብ የሰራዉን ታሪክ እየፋቁ የራሳቸዉን የመላ ታሪክ የሚጽፉ ከዲዎችን አባቶቹ ለፋሺስቶች ያስተማረዉን ትምህርት ለነዚህ ፋሽስቶችም እንደገና ማስተማር አለበት።

Ethiopia: Digital Attacks Intensify


(New York) – The Ethiopian government has renewed efforts to silence independent voices abroad by using apparent foreign spyware, Human Rights Watch said today. The Ethiopian authorities should immediately cease digital attacks on journalists, while foreign surveillance technology sellers should investigate alleged abuses linked to their products.

Independent researchers at the Toronto-based research center Citizen Lab on March 9, 2015, reported new attempts by Ethiopia to hack into computers and accounts of Ethiopian Satellite Television (ESAT) employees based in the United States. The attacks bear similarities to earlier attempts to target Ethiopian journalists outside Ethiopia dating back to December 2013. ESAT is an independent, diaspora-run television and radio station.

“Ethiopia’s government has over the past year intensified its assault on media freedom by systematically trying to silence journalists,” saidCynthia Wong, senior Internet researcher at Human Rights Watch. “These digital attacks threaten journalists’ ability to protect the safety of their sources and to avoid retaliation.”

The government has repressed independent media in Ethiopia ahead of the general elections scheduled for May, Human Rights Watch said. Many privately owned print publications heavily self-censor coverage of politically sensitive issues or have shut down. In the last year, at least 22 journalists, bloggers, and publishers have been criminally charged, at least six publications have closed amid a campaign of harassment, and many journalists have fled the country.

Many Ethiopians turn to ESAT and other foreign stations to obtain news and analysis that is independent of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front. However, intrusive surveillance of these news organizations undermines their ability to protect sources and further restricts the media environment ahead of the elections. Government authorities have repeatedly intimidated, harassed, and arbitrarily detained sources providing information to ESAT and other foreign stations.

Citizen Lab’s analysis suggests the attacks were carried out with spyware called Remote Control System (RCS) sold by the Italian firm Hacking Team, which sells surveillance and hacking technology. This spyware was allegedly used in previous attempts to infect computers of ESAT employees in December 2013. If successfully installed on a target’s computer, the spyware would allow a government controlling the software access to activity on a computer or phone, including email, files, passwords typed into the device, contact lists, and audio and video from the device’s microphone and camera.

Citizen Lab also found that the spyware used in the attacks against ESAT appeared to have been updated as recently as December 2014. On November 19, a security researcher, Claudio Guarnieri, along with several nongovernmental organizations, publicly released a tool called Detekt, which can be used to scan computers for Hacking Team RCS and other spyware. Citizen Lab’s testing determined that Detekt was able to successfully recognize the version of RCS used in a November attack, but not the version used in a December attack. Citizen Lab concluded that this may indicate that the software had been updated sometime between the two attempts.

These new findings, if accurate, raise serious concerns that Hacking Team has not addressed evidence of abuseof its product by the Ethiopian government and may be continuing to facilitate that abuse through updates or other support, Human Rights Watch said.

Hacking Team states that it sells exclusively to governments, particularly law enforcement and intelligence agencies. The firm told Human Rights Watch in 2014 that “we expect our clients to behave responsibly and within the law as it applies to them” and that the firm will suspend support for its technology if it believes the customer has used it “to facilitate gross human rights abuses” or “who refuse to agree to or comply with provisions in [the company’s] contracts that describe intended use of HT [Hacking Team] software.” Hacking Team has also stated that it has suspended support for their product in the past, in which case the “product soon becomes useless.”

Media reports and research by independent human rights organizations in the past year have documented serious human rights violations by the Ethiopian government that at times have been facilitated by misuse of surveillance powers. Although spyware companies market their products as “lawful intercept” solutions used to fight serious crime or counterterrorism, the Ethiopian government has abused its counterterrorism laws to prosecute bloggers and journalists who merely report on public affairs or politically sensitive issues. Ethiopian laws that authorize surveillance do not adequately protect the right to privacy, due process, and other basic rights, and are inconsistent with international human rights requirements.

Hacking Team previously told Human Rights Watch that “to maintain their confidentiality” the firm does not “confirm or deny the existence of any individual customer or their country location.” On February 25, 2015, Human Rights Watch wrote to the firm to ask whether it has investigated possible abuse of its products by the Ethiopian government to target independent media and hack into ESAT computers. In response, on March 6 a representative of the firm emailed Human Rights Watch that the company “take[s] precautions with every client to assure that they do not abuse our systems, and, we investigate when allegations of misuse arise” and that the firm is “attempting to understand the circumstances in this case.” The company also stated that “it can be quite difficult to get to actual facts particularly since we do not operate surveillance systems in the field for our clients.” Hacking Team raised unspecified questions about the evidence presented to identify the spyware used in these attacks.

Human Rights Watch also asked the company whether contractual provisions to which governmental customers agree address governments’ obligations under international human rights law to protect the right to privacy, freedom of expression, and other human rights. In a separate March 7 response from the firm’s representative, Hacking Team told Human Rights Watch that the use of its technology is “governed by the laws of the countries of our clients,” and sales of its technology are regulated by the Italian Economics Ministry under the Wassenaar Arrangement, a multilateral export controls regime for dual-use technologies. The company stated that it relies “on the International community to enforce its standards for human rights protection.”

The firm has not reported on what, if any, investigation was undertaken in response to the March 2014 Human Rights Watch report discussing how spyware that appeared to be Hacking Team’s RCS was used to target ESAT employees in 2013. In its March 7 response, the company told Human Rights Watch that it will “take appropriate action depending on what we can determine,” but they “do not report the results of our investigation to the press or other groups, because we consider this to be an internal business matter.”

Without more disclosure of how Hacking Team has addressed potential abuses linked to its business, the strength of its human rights policy will be in question, Human Rights Watch said. 
Sellers of surveillance systems have a responsibility to respect human rights, which includes preventing, mitigating, and addressing abuses linked to its business operations, regardless of whether government customers adequately protect rights.

“Hacking Team should publicly disclose what steps it has taken to avoid abuses of its product such as those alleged against the Ethiopian government,” Wong said. “The company protects the confidentiality of its customers, yet the Ethiopian government appears to use its spyware to compromise the privacy and security of journalists and their sources.” 
http://www.hrw.org/
http://www.hrw.org/news/2015/03/08/ethiopia-digital-attacks-intensify

Sunday 8 March 2015

ሚኒስቴሩ መልስ ሰጡ! የቴድሮስ አድሃኖም የ20 ሚሊዮን ዶላር ፕሮፓጋንዳ

ኤርትራ ተወልዶ ያደገውና በአሁኑ ወቅት በችሎታው ሳይሆን በዘሩ እና በወያኔነቱ ተመርጦ “የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር” ለመሆን የበቃው ቴድሮስ አድሃኖም ሰሞኑን የተለመደ ወያኔዊ ፕሮፓጋንዳ ሰርቶ ሲያራግብ ከርሟል። ይሁንና የዚህኛው ፕሮፓጋንዳ ታሪክ የሚጀምረው ወያኔዎች ከማይቆጣጠሩት ሩቅ ሃገር (አውስትራሊያ) በመሆኑ የፕሮፓጋንዳው ታሪክ ሃሰት እንደሆነ ለማወቅ ጊዜ አልፈጀም።
Tedros Adhanom's propaganda የታሪኩ ምንጭ የሆነችው ታዳጊ በሪቱ ጃለታ አሕመድ በሃገረ አውስትራሊያ በምትማርበት ትምህርት ቤት በተካሄደ ውድድር በማሸነፏ የተሸለመችውን 20 ሚሊዮን ዶላር ይዛ ኢትዮጵያ ውስጥ ትምህርት ቤቶችን ልትገነባ (ኢንቬስት) ልታደርግ ገስግሳ መጥታለች በማለት ነበር አይተ ቴድሮስ አድሃኖም በፌስቡካቸውና በቴሌቪዥናቸው የፕሮፓጋንዳ ዜናቸውን ያሰራጩት።
ጋዜጠኛ አበበ ገላው፣ ኢሳት እና ነዋሪነታቸው በአውስትራሊያ የሆነ ኢትዮጵያውያን ጉዳዩን ለማጣራት ባደረጉት ሙከራ እንደተረዱት ከሆነ ያን ያህል ገንዘብ ለአንዲት ታዳጊ ወጣት በሽልማት መልክ የሰጠ የአውስትራሊያ ተቋም አልተገኘም። በቴድሮስ አድሃኖም ዜና ስሙ የተጠቀሰው “የአውስትራሊያ ሮታሪ ክለብ” ከነጭራሹ የለም። ጉዳዩን ለማጣራት የሞከረው ጋዜጠኛ አበበ ገላው እንደተረዳው… በአውስትራሊያ በሺዎች የሚቆጠሩ ሮታሪ (የበጎ አድራቶት፟) ድርጅቶች ያሉ ሲሆን አንዳቸው የተባለውን ያህል ገንዘብ በሽልማት ለመስጠት አቅም የላቸውም። የአውስትራሊያ መንግስት በበኩሉ በአንድ ዓመት በአጠቃላይ በአፍሪካ ለበጎ አድራጎት ያወጣው ገንዘብ መጠን ወደ 14 ሚሊዮን ገደማ እንደሆነ አመልክቷል። በቴድሮስ አድሃኖም ከሚነገረው 20 ሚሊዮን ዶላር ግማሽ ያህሉን ማለት ነው።
ቴድሮስ አድሃኖም ውሸታቸው ከተጋለጠ በኋላ እንደሰለጠነ ሰው ማስተባበያ ይሰጣሉ ወይንም ይቅርታ ይጠይቃሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ ከዚህ በታች የሰፈረውን እጅ እግር የሌለው መልዕክት አስተላልፈዋል…
“… እንደምታውቁት በሪቱ የ 14 ዓመት ታዳጊ ናት፡፡ ህፃናትና ታደጊዎች የዋሆች እንደሆኑ ክፋት እንደሌላቸው ከኔ ጋር የምትስማሙ ይመስለኛል፡፡ በዚህ ምክንያትም ህፃናትና ታዳጊዎች የሚነግሩኝን ማመን እመርጣለሁ፡፡ ስህተትም ቢኖራቸው ከየዋህነት ካልሆነ ከክፋት አይመነጭም፡፡ ህፃናትን ማመን ስህተት ከሆነ መሳሳትን እመርጣለሁ፡፡…”
በቴድሮስ አድሃኖም ደረቅ መልስ የተበሳጩ ኢትዮጵያውያን ከብዙ በጥቂቱ እንዲህ ብለዋቸዋል…
“ህፃናት ብፁአን ናቸዉ አሉ ዶፍተሩ የሳቸዉን ጥፋት ወደ ልጂቱ ጠጋ ጠጋ?ዛሬ መዋሸት አይቻልም እድሜ ለኢሳት እንዲህ ራቁታችሁን ያስቆማችኋል ። ይብላኝ እናተን ተከትለዉ ገደል ለገቡት!” Hirut Hailu
“…ይህን የዶ/ር ቴውድሮስን ሃሳብ ስመለከት … መንግስታችን የሚያምናቸው ያሉትን የሚሰማቸው ዜጎች ህፃናት ከሆኑ …ውሃ መብራት ዲሞክራሲና የመሳሰሉት መሰረታዊ ጥያቄወች በህፃናት ልጆቻችን በኩል ብናቀርብ አጥጋቢ ምላሽ ሊሰጠን ይችላል ስል አሰብኩ ! ጥያቄው ልጆቻችን የሚታመኑት ሃያ ሚሊየን ዶላር ይዘው ሲናገሩ ነው ወይስ ባዷቸውን ቢያወሩም ይሰማሉ… የሚለው ነው ፡) ለማንኛውም ዶ/ር ይችን አንድ ፍሬ ልጅ ሃሳብሽ ጥሩ ነው የተቀደሰ ነው ግን ውሸት ‹ለህፃናት› ጥሩ አይደለም ብለው መምከር አባታዊ ግዴታዎት ይመስላኛል!!…” Alex Abraham
“…ተሸዉጃለሁ ማለቱን ስሰማ ሀገሬ አሳዘነችኝ! አንዲት ፍሬ የ14 አመት ህፃን እንዲህ ከሸወደችዉ ምላሳቸዉ ወፍ ከሰማይ የሚያወርደዉ ዲፕሎሞቶችማ ሊሸጡትም ይችላሉ!! ደግሞ ሸጠዉት ቦንድ ግዙ ከሚሉን በጊዜ ከስልጣኑ ቢያባርሩት ነዉ የሚሻለዉ! እሱም አርፎ ፎቶዎቹን ይለጥፍ ነበር!” Gashaw Mersha
“…ይህ ሰውዬ በ90 ሚሊዬን የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ሲቀልድ ተመልከቱት ውሸቱ የተፈጠረው ልጅቷ ትንሽ ስለሆነች በሷ የተፈጠረ ችግር ነው እና ራዕይዋ እንዲሳካ ከጎና እንሁን እያለ በሷ እየአማህኝ ነው ፤ እንግዲህ ይታያችሁ ኢትዮጵያን የምታህል ትልቅ አገር የውጭ ጉዷ ሚንስቴር ነኝ ብሎ ተቀምጦ የበሬው ላሞለደ የውሸት መረጃ እሱና ጓደኞቹ በሞኖቦል በያዙት ኢቢሲ ለህዝብ እያቀረቡ ያሉት ማፊሪያዎች።” Netsanet Beqalu
 http://ecadforum.com/Amharic/archives/14575/

Wednesday 4 March 2015

The 60th Andargachew Tsige’s Birthday Celebration on Feb 14, 2015

The celebration of the 60th birthday of Andargachew Tsige was organized by youth section under Domocracy Change in Ethiopia Supoort Organization in Norway (DCESON) in a very colorful celebration which held on Feb 14, 2015 in Oslo. Many Ethiopians who are living in and out 0f Oslo were invited and satisfied by the celebration of our hero Andy’s birthday.