Sunday 31 March 2013

የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የገዢው ፓርቲ አባላት እንዲሆኑ እየተጠየቁ ነው


የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የገዢው ፓርቲ አባላት እንዲሆኑ እየተጠየቁ ነው

መጋቢት ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን በግድ የፓርቲ አባል እያደረገ ያጠመቀው ኢህአዴግ  አሁን ደግሞ በአካል ጠና ያሉትን ታዳጊ ወጣት የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎችን የአባልነት ፎርም እያስሞላ እንደሚገኝ ምንጮች አስታወቁ፡፡
ታዳጊ ወጣቶች በጠርናፊ መምህራን በኩል እየተመለመሉ መሆኑን የገለጹት ምንጮች በዚህ ሳምንት በመላ አዲስ አበባ በመንግሥት ትምህርት ቤቶች የሚማሩትን ታዳጊ ወጣቶች በግማሽ ቀን ሥልጠና የመግባቢያ ዝግጅት አካሂዶ እና 50 ብር የውሎ አበል ሰጥቶ በመሸንገል ፎርም እንዲሞሉ አድርጓል።
አምስት፣ አምስት የኮሚቴ አባላትም በየትምህርት ቤቱ የተመረጡ ሲሆን የኢህአዴግ ካድሬዎች መመሪያ የሚያወርዱት ለነዚህ ተማሪዎች ይሆናል ተብሎአል።
ዘጋቢያችን ‹‹ለ ተማሪ … እርስዎ የኢህአዴግ አባል መሆንዎ ይታወቃል፤ በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ መጋቢት 21 እና 22 ቀን በሚካሄደው የሙሉ ቀን ሥልጠና ላይ በ … ትምህርት ቤት ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ላይ እንዲገኙ በአክብሮት ተጋብዘዋል›› የሚል ወረቀት መመልከቱን ገልጿል።
ለሥልጠና የተመረጡት የተማሪዎች ሥም እና የመንግሥት ትምህርት ቤቶችም ሥማቸው ፎርሙ ላይ በብዕር የተሞላ ሲሆን በሁለቱ ቀን ሥልጠና በቀን መቶ መቶ ብር እንደሚሰጣቸው ጠርናፊዎቻቸው በቃል እንደነገሯቸው ተማሪዎቹ ለዘጋቢያችን ገልጸዋል፡፡
በባህርዳር በተካሄደው 9ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ላይ አንዳንድ ከፍተኛ ባለስልጣናት ኢህአዴግ ሰዎችን ለመመልመል የሚጠቀምበት ዘዴ ከእውነተኛ ተጋዮች ይልቅ አድርባዮችን እንዲያፈራ አድርጓል በማለት እንደገና እንዲታይ መጠየቃቸው ይታወሳል።
ኢህአዴግ 6 ሚሊዮን አባላት እንዳሉት በተደጋጋሚ ይናገራል። በኢህአዴግ ስሌት መሰረት ከ13 ኢትዮጵያውያን መካከል አንዱ ኢህአዴግ ነው። እድሜያቸው ከ18 አመት በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ግምት ውስጥ ካስገባን ደግሞ፣ ከ5 ሰዎች መካከል አንዱ የኢህአዴግ አባል ነው ።

Ethiopia: EPRDF, no identity and no vision


Ethiopia: EPRDF, no identity and no vision

FOR  IMMEDIATE  RELEASE
March 28 2013
For the past twenty one years, the Tigray People Liberation Front (TPLF) that has no mandate to rule Ethiopia hasGinbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy actually ruled Ethiopia with iron fist dashing on the  Trojan horse,  the  EPRDF ( Ethiopian People Revolutionary Democratic Front).  The EPRDF, a political front; composed of a hodgepodge of ethnically assembled organizations, is a hollow group of ethnic demagogues created by its late leader to materialize his lifelong dream of dividing Ethiopia along ethnic lines. Ironically, the EPRDF that blatantly boasts to have averted the disintegration of Ethiopia, firmly stood up to the dreams of its creator and augmented the fragmentation of Ethiopia, the very country it calls home.
On Saturday March 23, 2013, the EPRDF started its 9th and possibly what could be its last congress with an embarrassing; and to the vast majority of Ethiopians with a pointless theme of – “The Thoughts of Meles”.  In fact, if there is one good cause served by the 9th EPRDF congress, it should be that, the Trojan horse EPRDF proved to the Ethiopian people that it is a party in existence with a borrowed identity that rules over a nation of ninety million people with a dead vision of a deceased man. The EPRDF is a party that lives in the past, failed to cease the moment and has no vision for the future.
The four-day congress that ended on Tuesday came to an end with exactly the same hollowness that it started. To the surprise of its own members and diehard supporters, the four -day congress looked like much of a eulogy of a man (dead for seven months) than an occasion to map a vision for Ethiopia’s future.  Despite all indications of the nation’s chronic problems of ethnic conflict, poverty, human rights abuse, deteriorating living conditions, and alarming outflow of skilled manpower, the EPRDF vowed to extend its grip on power and carry on the same old failed policies of the past. All in all, the handmade toy, the EPRDF, shamelessly told the Ethiopian people that it has no vision of its own and nothing new on its plate.
Ginbot 7, Movement for Justice, Freedom and Democracy not only invalidates the resolution of the 9th congress of the EPRDF, but it also extends its call to the Ethiopian people inside and outside Ethiopia to come together and fight in unison to stop the implementation of a policy that has a hard to reverse the detrimental effect on our nation. Ginbot 7 reiterates its perennial message to the Ethiopian people and to the international community at large that there are much better alternatives to the tested and failed policies of the EPRDF that benefit the interest of the Ethiopian people, the Horn of Africa and all other parties’ involved. The international community, donor nations and most importantly, the EU, United Kingdom and the United States must come to their senses and acknowledge that freedom; justice and democracy are God given human values that the people of Ethiopia thirst for just like the British and the American people.

“እያንጓለለ” የአዜብ ኮሜዲ


“እያንጓለለ” የአዜብ ኮሜዲ

ከቴድሮስ ሐይሌ (TADYHA@GMAIL.COM)
“መለስ ወደዚህ ዓለም ጭንቅላቱን ይዞ ለዝህች አገር ለዚህች ምድር የሚጠቅም ሃሰብ አመነጨ ለግሌ ለቤተሰቦቼ ሳይል አንድ ቀን ለራሱ ሳይሆን መንግስት በሚሰጠው ደመወዝ በፔሮል የሚከፈል መሪ በዓለም ላይ መለስ ብቻ ነው።” አዜብ መስፍን
የዛሬ ሁለት አመት ገደማ ዝናው ገኖ የነበረው የቀድሞው መንግስት ተራ ወታደር የነበረው ታምራት ገለታ የተባለ አባይ ጠንቋይ ሴት ወንዱን መሃይም ምሁሩን ብቻ ከተራውAzeb Mesfin, the wife of Meles Zenawi ዜጋ እስከዘመኑ ባለስልጣናት ሲያሰግድ ለቃልቻ ጣዖቱ ግብር ሲያስገባ የበረታ መንፈሳዊ ሃይል የተቀዳጀ እንደሆነ በአንድ ግዜ በተለያየ ቦታ እንደሚገለጽ ለተማጠነው ሃብት ጤና ትዳር እንደሚሰጥ በመስበክ ብዙ የዋሃንን አሳምኖ እስከ መመለክ ደርሶ የእግሩን እጣቢ እነደ ጠበል ሲያስጠጣ የነሆለሉለትን ሃብታሞች መድሃኒት በማጠጣት ገድሎ ሃብታቸውን የወረሰበትን የዩንቨርስቲ ምሩቃንን ሳየቀር ሳር እያስጎዘጎዘ ቡና እያስወቀጠ ይካደም የነበረበትን ሞራል አልባ የእውነት ድራማ በፍርድ መቋጫ እስካገኘበት ድረስ ያለውን የግለሰቡን የአጭበርባሪ ጥንቆላ ተውኔት ያንድ ወቅት መነጋገሪ ሆኖ የድርጊቱ ሰለባዎችና ራሱ ወንጀል ፈጻሚው ጭምር ለፖሊስ ይሰጡ የነበረውን መረጃ በየፌስቡኩና በዩትዩብ ተለቆ ጉድ ሲባል ነበር። ይህ አባይ ጠንቋይ ታዲያ በማጭበርበር ባካበተው ሃብቱ የገነባቸውን የቢዝነስ ተቋማት የላቡ ውጤት መሆኑንና ህብረተሰቡን በመርዳት ያበረከተው በጎ አስተዋጾ የማይገባ ስም እንደተሰጠው ለመከራከር ያቀረበው እፍረት አልባ ሙግት ተገቢ በሆነ ቅጣት መደምደሙን አስተውለናል።
ይህ አባይ ጠንቋይ ቢታሰርም አምሳያዎቹ የፖለቲካ ሟርትና የሙት ራዕይ አስፈጻሚ ተንበርካኪ የወያኔ ሎሌዎች መለስ የተባለ ጣዖት አቁመው ሲበሉም ሲጠጡም ስሙን ካለነሱት የማይሆንላቸው እንደ ሃይለማርያም ደሳለኝ ያለ ነሆለል ወንጌላዊ ነኝ የሚል ወንጀለኛ ከጠንቋዩ ካዳሚዎች በባሰ አገላለጽ መንገድና እውነት መለስ ነው ሲል የሬሳ አምልኮውን የገለጠበት አጋጣሚ የዘርና መንደር ደዌ አይነልቦናቸውን የጋረዳቸው ካህን ነን ባይ ባለጥምጥሞች ሳይቀር ቃላት ያረከሱበትን ቅጥፈታዊ ሙገሳዎችንና የተጋነኑ በተረት የተሞሉ ከንቱ ውዳሴያቸውን እንደ ቃልቻው ታሪክ በመገረም ስንከታተለው የከረምንው ቴያትር ገና ትዝታው ሳይጠፋ ወይዘሮ አዜብ ሰሞኑን ባህርዳር ላይ የዘላበደችው የሃገሬ ሰው የአቡዬን መገበሪያ የበላ ያስለፈልፈዋል እንዲሉ ሳትጠየቅ ባሏ በድህነት ኖሮ በድህነት ማለፉን ቅንድቧ ሰበር እንኳ ሳይል ተጨፈኑ ላሞኛችሁ መሐይማዊ ትንተናዋ ብዕሬን እንዳነሳና ከነባለቤቷ ሲፈጽሙ የቆዩትን ወንጀል ለማስታወስ እንድገደድ አድርጎኛል ታዲያም እንዲሁ በደረቁ እንዳይሆን ያ ህዝብ አዳም ያሸረግድለት የነበረ ቃልቻ ሴራው ከሽፎ ዘብጥያ ከወረደ በኋላ ኮሜድያኑ አዝናኝና አስተማሪ
የሆነውን እያንጓለለ በሚል የተሰራው ክሊፕ ከቁመቱ በላይና በሌለው ራዕይ በወያኔዎች ዘንድ ተመላኪ ከሆነው መለስ ዜናዊ ጋር በአጭበርባሪነት ይሁን በጣዖትነት ተመሳሳይ ሁኔታ እንዳላቸው ይህ በኩምክና የታጀበች ሙዚቃ እንዲመለከቱት እጋብዛለሁ
ልባዊ ወዳጄ የሆነው የቀድሞው የሕወሃት ታጋይ የዛሬው የዲሞክራሲ አክቲቪስት አቶ መኮንን ዘለለው የዛሬዋን ስም የለሽ ንግስት አንዳንዶች የዘረፋ ሴትወይዘሮ ሲሉ የሚጠሯት የሰው በላውና የዘረኛው መለዝ ዜናዊ ባለቤት አዜብ ጎላ (አዜብ መስፍን) ወልቃይት ከሚገኝ አንድ መሸታ ቤት መልምሎ ለትግል ሲያሰልፋት ያቺ የገጠር ኮረዳ ዛሬ በሚለዮኖች ህልውና የምትቀልድ መከራ የማይመክራን ልበ ድፍን ትሆናለች ብሎ የገመተም ሆነ ያሰበ አልነበረም። ምግብ አጥተው ለሞት ከሚዳረጉ ህጻናት አፍ በበሽታ ከሚማቅቀው ደሃ ወገናችን ላይ በባሏ አመራር ከነጭፍሮቿ ያለ ይልኙታ ሲዘርፉ የኖሩት የህዝብ ሃብት የውጭ ሃገራትን ባንኮች ማጨናነቁን ሪፖርቶች ይፋ በሚያደርጉበት ወቅት ላይ 11 ቢለዮነ ዶላር መዘረፉንና በህገወጥ መንገድ ከሃገር መውጣቱ በአስተማማኝ መረጃ ይፋ በተደረገበት ሁኔታ ላይ ባሌ በችግር ነው የኖረው መንግስት ከሚከፍለው ውጪ ቤሳ ቤስቲን የሌለው ሃቀኞች ነን ስትል ጆሮ አልሰማ አይል ሰማናት
ባለፉት ሃያሁለት አመታት ከስሙኒ ማራገቢያ ሻጭነት ተነስተው ዛሬ ቢጠሯቸው የማይሰሙ ሚሊየነሮች በሆኑበት ታጋይ ከበርቴዎች ልማታዊ ዘራፊዎች ከራሳአቸው አልፈው ተርፈው ለቅምጦቻቸው ሳይቀር የቅንጦት መኪና ስጦታ የሚያበረክቱበት የወታደራዊ አዛዠነት ከቁመታቸው በላይ የታደላቸው የትግሬው ነጻ አውጪ አባሎች የሚሰሩት ቪላ ኢንቨስት የሚያደርጉት ገንዘብ ከደደቢት ይዘው የመጡት ነው ካልተባለ በስተቀር አለም የሚያውቃቸው አዲስ አበባ ሲገቡ ከራሳቸው ተባይ ከገላቸው እድፍና ከእግራቸው ንቃቃት ውጪ የረባ ኩባያ እንኳ ያልነበራቸው ወያኔዎች የዛሬዎቹ ሻኛ ቁርሱ ወርቅ ትራሱ ለመሆን የበቁት ከደሃው ኢትዮጽያዊ አፍ ነጥቀው ለመሆኑ ማስረጃ ለመደርደር መሞከሩ ለቀባሪው ማርዳት ነው።እነዚህ የወያኔ ጉዶች ቁርበት ላይ ተወልደው ቁረበት ላይ እንዳላደጉ ዘርፈው ከሚያካብቱት ሃብት በተጨማሪ በቀል ባጫጨው አይምሮአቸው ለሚቀመጡበት የቢሮ ወንበርና ጠረጤዛ ሳየቀር በውድ ዋጋ በውጭ ምንዛሪ እንዲገዛ በማድረግ የሚያወድሙት ሃብት ስፍር ቁጥር የለውም። በችግር የሚለበለበው መላው ህዝባችን የ21 አመት የወያኔ ጉዞ የት እንዳደረሰው አርቲስቶቹ በሙዚቃ በተቀናበረ ኮሜዲ ያቀረቡት የፈጠራ ስራ ሁኔታውን በሚገባ ይገልጸዋል ብዬ ስለገመትኩ ሌላም የኮሜዲ ሙዚቃ ተጋበዙ።
የአዜብና የባሏ ጭፍራዎች እንዲህ በቅንጦት ካበዱ ዋናዎቹ ምን ሊኖራቸው እንደሚችል ለመገመት ጠንቋይ መሆንን አይጠይቅም። በአጭሩ የሌቦች አውራና የዘራፊዎች አዛዠ በግፍ የሰበሰበውን ሳይበላ የተጠራው መለስ ከምድራዊ ፍርድ ባያመልጥም በጥይት ያስፈጃቸው ብቻ ሳይሆን በረሃብ ከጠወለገች እናታቸው ደረቅ ጡት እየማጉ በሞት የተነጠቁት ጨቅላ ህጻናት ሳይቀር በአረመኔነቱ ለፍርድ ከጌታ ዘንድ እንደሚያቀርቡት እሙን ነው። የትላንቷ ኮማሪት የዛሬዎ ኤፈርት የተባለው የኢትዮጽያውያንን ደም የሚመጥ ሃገር ገዳይ ሞኖፖሊስት የቢዝነስ ተቋም ሃገሪቷ የሌላትን የገንዘብ አቅም ያካበተ ተጠያቂነቱ ማንና ለምን እንደሆነ የማይታወቅ ብድር ወስዶ የማይመልስ ሂሳቡን እንኳ ኦዲት የማያስደርግ በባልና ሚስት አመራር ይዘወር የነበረው ይህ ተቋም የማን ሆነና ነው መለስ የፔሮል ደመወዝ ተከፋይና የገንዘብ ደሃ የሚሆነው አዜብ መስፍን ለማያቅሽ ታጠኝ ዘራፊነታችሁን አለም ያወቀው ፀሃይ የሞቀው ለመሆኑ ትንሿ ማስረጃ ልጃችሁ እንግሊዝ ሃገር የምትማርበት ክፍያ ከዛች ከባሎ ደመወዝ ላይ ተቆርጦ ነው! ወይስ ልጆቻችሁ እንደ ጓድ መንግስቱ ሃይለማርያም ልጆች በሃገር ቤት እንደ ሌላው ዜጋ የመንግስት ትምህርት ቤት ነው የሚማሩት እሜዬቴ በካድሬነቶ ዘመን ትንሽ እንኳ ሂሳብ አልተማሩም እንዴ ቀጣፊ።
ወይዘሮ አዜብ ሌላው በዚህ ቅብጥርጥሯ ካነሳችሁ ውስጥ የመለስ ሃብት ጭንቅላቱ ነው ለዚህች ምድር ታላቅ ሃሳብ ያመጠቀ ፈላስፋ አድርገዋለች ለመሆኑ መለስ ለጥቅስ እንኳ የሚበቃ እውቀት ትቷል ወይ በየትኛው መጽሃፉ ነው ችሎታው የታየው በየትኛውስ ነጻ መድረክ ላይ ተገኝቶ ተከራክሮ ችሎታውነ ያስመሰከረው መቼመ ሴትየዋ ከዛ ከከብት በረት ካልተሻለው ፓርላማ ላይ ያለከልካይ ይቀባጥር የነበረውን ባዶ የቃላት ጋጋት በሚያቀርበው ዲስኩር እጁ እስኪግል እንዲያጨበጭብ መመሪያ የሚሰጠው ካድሬ ሁካታ ካልጠቀሰች በስተቀር ሌላ ብትጠየቅ የምትሰጠው መልስ አይኖርም። መለስ በዘመኑ ከጻፋቸው ውስጥ ህዝብ ዘንደ የደረሰው የሃገር ልዑዓላዊነትን አሳልፎ የሰጠበት የሻብያ መወድስ የተባለለት ኤርትራ
ከየት ወዴት ብሎ የደረሰው ቀሽም የክህደት ዶሴ ቀለሙ ሳይደርቅ ተሰብስቦ መቃጠሉ ይታወቃል ከዛ በተረፈ ይህ ነው የሚባል በሎጂክና በዲያሌቲክስ የዳበረ የራሱ ፈጠራ ውጤት ሳያኖር ያለፈ ቢሆንም ምንአልባት በብልጣብልጥነትና ውሸትን አጣፍጦ በማቅረብ በመልቲነቱ በመሪነት ደረጃ በዓለም ውስጥ የሚወዳደረው የሌለ የክብረ ወሰን ባለቤት ያደርገዋል።
ለሃገሩ ቀን ከሌት ሲደክም የኖረ እንደነበርም ደስኩራለች፤ ለመሆኑ መለስ የትኛውን በጎ ነገር ነው ለሃገር ያበረከተው፤ ዲሞክራሲን መልካም አስተዳደርን ፤እኩልነትን፤ ልማትን መለስ ለሃገራችን አበርክቷልን መልሱ በተቃራኒው ነው እድሜ ለመለሰ አመራር አንድነታችን ተዳክሞ ቁርሾ በህዘቦች ዘንድ እንዲኖር ተደርጓል፤ ህዝባችን በሃገር የመኖር የመስራት የመማርና ሃሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብት ተነፍጎ ሃገር ጥሎ በመሰደድ የዓለም ክብረወሰን ጨብጧል፤ መለስ በዋሾነቱ በጫት ቃሚነቱና በትንባሆ አጫሽነቱ ጭምር ለትውልዱ መልካም አርዓያ በመሆን ፋንታ የጥፋት ተምሳሌት ሆኖ ያለፈ ምግባረ ብልሹ ነበር። ሌላው መለስ በአገዛዘ ዘመኑ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱም ጭምር ኢትዮጽያን በማድማት ትግራይን ለማበልጸግ እቅድ ነድፎ ዘረኝነት ለትውልድ እንዲተላለፍ ጭምር ያደረ እኩይ ግለሰብ ነበር።
ውሃን ድንጋይ ያናግረዋል እንዲሉ ሴትየዋ እንደ አለት ጠጥሮ ከተጣባት ሃሰተኝነት አልላቀቅ ብላ በሞተው ሰውዬ ላይ እርግማን እንድናበዛ አደረገችን እዚህ ላይ ሴትዮይቱም ሆነ ሌላው ወገን ሊያውቀው የሚገባ በደርግ ዘመን ጠቅላይ ሚንስትር የነበረው በመልከ መልካምነቱ የሚወሳው ፍቅረስላሴ ወግደረስ በግዜው አበላል እንደ ደርግ አባል አለባበስ እንደወግደረስ ተብሎ ይነገርለት የነበረው ይህ ከፍተኛ ባለስልጣን ወያኔ አዲስ አበባን ሲቆጣጠር ከዚህ ግለሰብ ካዝና የተገኘው ገንዘብ በጣም ትንሽ በመሆኑ ለራሳአቸው ለወያኔዎቹ አስደንግጦዓቸው እንደነበር በግዜው ከተለያዩ ጽሁፎች አንብቤያለሁ ፤ አዎን በደረጉ ግዜ የነበረ ባለስልጣን ግፋ ቢል ከጮማና ከውስኪ የማያልፍ በዘረፋ ያልተጠመደ በአብዛኛው በደመወዙ የሚተዳደር እንደነበር ከማንም በላይ ያረጋገጡት ራሳቸው ወያኔዎች ቢሆኑም ከላይ እንደተባለው የወያኔው ባለማሎች የሚያነቀሳቅሱተ የገንዘበ መጠን ለቁጥር የሚታክት ቢሆንም እንዲህ ጥቂቶች በቅንጦት በሚቀብጡባት ሃገር የእለት ጉርስ የአመት ልብስ አጥቶ በየበረንዳው ፍግም ብሎ ከሚያድረው አውታታ ጀምሮ ዛሬ ዛሬ ቤተሰብ ልጆቹን መመገብ ተስኖት ህጻናት በየትምህርት ቤታቸው ጠኔ ሲጥላቸው መስማት የተለመደበት ቁራሽ እንጀራ ማግኘት የከበደበት የመከራ ዘመን ለመድረሳችን አንዱና ዋናው ምክንያት መለስና ቡድኑ ያለቅጥ በዘረፋ መጠመዳቸውና ዘረኛና አድሏዊ በሆነው የልማትና የዕድገት ፖሊሲያቸው ከትግራይ ክልል በስተቀር መላዋ ኢትዮጽያ የሰቆቃ ቀጠና እንድትሆን በማደረጋቸው ነው። አዜብ መስፍን የባሏን ፍሬ አልባ ተረት ትቀባጥር በነበረበት የባሕርዳር ከተማ በትንሽ ኪሎሜትር እርቀት ላይ በዘራቸው ምክንያት ውጡልን ተብለው ለዘመናት ከኖሩበት ቅያቸው ሃብት ንብረታቸው ተቀምተው የወገን ያለህ የሚሉበት ሁኔታ መለስ ዘርቶት የሄደው አረም ሃገር ሊያጠፋ ዳርዳር ያለበት ሁኔት ተፋፍሞ በሚገኝበት ሁኔታ ላይ እንኳ አለመንቃቷ የሴትዮይቱን ለከት የለሽ እብሪት ከማሳየት ባሻገር ገና ሃገሪቱ በዚሁ ሙት መንፈስ ብዙ አበሳ እንደሚመጣባት ጠቋሚ ሆኖ ይታየኛል።
ኢትዮጽያን እግዚያብሄር ይባርክ አሜን !
ትንሳዔዋን ያሰየን!!
አሜን!!!
ከቴድሮስ ሐይሌ (TADYHA@GMAIL.COM)
“መለስ ወደዚህ ዓለም ጭንቅላቱን ይዞ ለዝህች አገር ለዚህች ምድር የሚጠቅም ሃሰብ አመነጨ ለግሌ ለቤተሰቦቼ ሳይል አንድ ቀን ለራሱ ሳይሆን መንግስት በሚሰጠው ደመወዝ በፔሮል የሚከፈል መሪ በዓለም ላይ መለስ ብቻ ነው።” አዜብ መስፍን
የዛሬ ሁለት አመት ገደማ ዝናው ገኖ የነበረው የቀድሞው መንግስት ተራ ወታደር የነበረው ታምራት ገለታ የተባለ አባይ ጠንቋይ ሴት ወንዱን መሃይም ምሁሩን ብቻ ከተራውAzeb Mesfin, the wife of Meles Zenawi ዜጋ እስከዘመኑ ባለስልጣናት ሲያሰግድ ለቃልቻ ጣዖቱ ግብር ሲያስገባ የበረታ መንፈሳዊ ሃይል የተቀዳጀ እንደሆነ በአንድ ግዜ በተለያየ ቦታ እንደሚገለጽ ለተማጠነው ሃብት ጤና ትዳር እንደሚሰጥ በመስበክ ብዙ የዋሃንን አሳምኖ እስከ መመለክ ደርሶ የእግሩን እጣቢ እነደ ጠበል ሲያስጠጣ የነሆለሉለትን ሃብታሞች መድሃኒት በማጠጣት ገድሎ ሃብታቸውን የወረሰበትን የዩንቨርስቲ ምሩቃንን ሳየቀር ሳር እያስጎዘጎዘ ቡና እያስወቀጠ ይካደም የነበረበትን ሞራል አልባ የእውነት ድራማ በፍርድ መቋጫ እስካገኘበት ድረስ ያለውን የግለሰቡን የአጭበርባሪ ጥንቆላ ተውኔት ያንድ ወቅት መነጋገሪ ሆኖ የድርጊቱ ሰለባዎችና ራሱ ወንጀል ፈጻሚው ጭምር ለፖሊስ ይሰጡ የነበረውን መረጃ በየፌስቡኩና በዩትዩብ ተለቆ ጉድ ሲባል ነበር። ይህ አባይ ጠንቋይ ታዲያ በማጭበርበር ባካበተው ሃብቱ የገነባቸውን የቢዝነስ ተቋማት የላቡ ውጤት መሆኑንና ህብረተሰቡን በመርዳት ያበረከተው በጎ አስተዋጾ የማይገባ ስም እንደተሰጠው ለመከራከር ያቀረበው እፍረት አልባ ሙግት ተገቢ በሆነ ቅጣት መደምደሙን አስተውለናል።
ይህ አባይ ጠንቋይ ቢታሰርም አምሳያዎቹ የፖለቲካ ሟርትና የሙት ራዕይ አስፈጻሚ ተንበርካኪ የወያኔ ሎሌዎች መለስ የተባለ ጣዖት አቁመው ሲበሉም ሲጠጡም ስሙን ካለነሱት የማይሆንላቸው እንደ ሃይለማርያም ደሳለኝ ያለ ነሆለል ወንጌላዊ ነኝ የሚል ወንጀለኛ ከጠንቋዩ ካዳሚዎች በባሰ አገላለጽ መንገድና እውነት መለስ ነው ሲል የሬሳ አምልኮውን የገለጠበት አጋጣሚ የዘርና መንደር ደዌ አይነልቦናቸውን የጋረዳቸው ካህን ነን ባይ ባለጥምጥሞች ሳይቀር ቃላት ያረከሱበትን ቅጥፈታዊ ሙገሳዎችንና የተጋነኑ በተረት የተሞሉ ከንቱ ውዳሴያቸውን እንደ ቃልቻው ታሪክ በመገረም ስንከታተለው የከረምንው ቴያትር ገና ትዝታው ሳይጠፋ ወይዘሮ አዜብ ሰሞኑን ባህርዳር ላይ የዘላበደችው የሃገሬ ሰው የአቡዬን መገበሪያ የበላ ያስለፈልፈዋል እንዲሉ ሳትጠየቅ ባሏ በድህነት ኖሮ በድህነት ማለፉን ቅንድቧ ሰበር እንኳ ሳይል ተጨፈኑ ላሞኛችሁ መሐይማዊ ትንተናዋ ብዕሬን እንዳነሳና ከነባለቤቷ ሲፈጽሙ የቆዩትን ወንጀል ለማስታወስ እንድገደድ አድርጎኛል ታዲያም እንዲሁ በደረቁ እንዳይሆን ያ ህዝብ አዳም ያሸረግድለት የነበረ ቃልቻ ሴራው ከሽፎ ዘብጥያ ከወረደ በኋላ ኮሜድያኑ አዝናኝና አስተማሪ
የሆነውን እያንጓለለ በሚል የተሰራው ክሊፕ ከቁመቱ በላይና በሌለው ራዕይ በወያኔዎች ዘንድ ተመላኪ ከሆነው መለስ ዜናዊ ጋር በአጭበርባሪነት ይሁን በጣዖትነት ተመሳሳይ ሁኔታ እንዳላቸው ይህ በኩምክና የታጀበች ሙዚቃ እንዲመለከቱት እጋብዛለሁ
ልባዊ ወዳጄ የሆነው የቀድሞው የሕወሃት ታጋይ የዛሬው የዲሞክራሲ አክቲቪስት አቶ መኮንን ዘለለው የዛሬዋን ስም የለሽ ንግስት አንዳንዶች የዘረፋ ሴትወይዘሮ ሲሉ የሚጠሯት የሰው በላውና የዘረኛው መለዝ ዜናዊ ባለቤት አዜብ ጎላ (አዜብ መስፍን) ወልቃይት ከሚገኝ አንድ መሸታ ቤት መልምሎ ለትግል ሲያሰልፋት ያቺ የገጠር ኮረዳ ዛሬ በሚለዮኖች ህልውና የምትቀልድ መከራ የማይመክራን ልበ ድፍን ትሆናለች ብሎ የገመተም ሆነ ያሰበ አልነበረም። ምግብ አጥተው ለሞት ከሚዳረጉ ህጻናት አፍ በበሽታ ከሚማቅቀው ደሃ ወገናችን ላይ በባሏ አመራር ከነጭፍሮቿ ያለ ይልኙታ ሲዘርፉ የኖሩት የህዝብ ሃብት የውጭ ሃገራትን ባንኮች ማጨናነቁን ሪፖርቶች ይፋ በሚያደርጉበት ወቅት ላይ 11 ቢለዮነ ዶላር መዘረፉንና በህገወጥ መንገድ ከሃገር መውጣቱ በአስተማማኝ መረጃ ይፋ በተደረገበት ሁኔታ ላይ ባሌ በችግር ነው የኖረው መንግስት ከሚከፍለው ውጪ ቤሳ ቤስቲን የሌለው ሃቀኞች ነን ስትል ጆሮ አልሰማ አይል ሰማናት
ባለፉት ሃያሁለት አመታት ከስሙኒ ማራገቢያ ሻጭነት ተነስተው ዛሬ ቢጠሯቸው የማይሰሙ ሚሊየነሮች በሆኑበት ታጋይ ከበርቴዎች ልማታዊ ዘራፊዎች ከራሳአቸው አልፈው ተርፈው ለቅምጦቻቸው ሳይቀር የቅንጦት መኪና ስጦታ የሚያበረክቱበት የወታደራዊ አዛዠነት ከቁመታቸው በላይ የታደላቸው የትግሬው ነጻ አውጪ አባሎች የሚሰሩት ቪላ ኢንቨስት የሚያደርጉት ገንዘብ ከደደቢት ይዘው የመጡት ነው ካልተባለ በስተቀር አለም የሚያውቃቸው አዲስ አበባ ሲገቡ ከራሳቸው ተባይ ከገላቸው እድፍና ከእግራቸው ንቃቃት ውጪ የረባ ኩባያ እንኳ ያልነበራቸው ወያኔዎች የዛሬዎቹ ሻኛ ቁርሱ ወርቅ ትራሱ ለመሆን የበቁት ከደሃው ኢትዮጽያዊ አፍ ነጥቀው ለመሆኑ ማስረጃ ለመደርደር መሞከሩ ለቀባሪው ማርዳት ነው።እነዚህ የወያኔ ጉዶች ቁርበት ላይ ተወልደው ቁረበት ላይ እንዳላደጉ ዘርፈው ከሚያካብቱት ሃብት በተጨማሪ በቀል ባጫጨው አይምሮአቸው ለሚቀመጡበት የቢሮ ወንበርና ጠረጤዛ ሳየቀር በውድ ዋጋ በውጭ ምንዛሪ እንዲገዛ በማድረግ የሚያወድሙት ሃብት ስፍር ቁጥር የለውም። በችግር የሚለበለበው መላው ህዝባችን የ21 አመት የወያኔ ጉዞ የት እንዳደረሰው አርቲስቶቹ በሙዚቃ በተቀናበረ ኮሜዲ ያቀረቡት የፈጠራ ስራ ሁኔታውን በሚገባ ይገልጸዋል ብዬ ስለገመትኩ ሌላም የኮሜዲ ሙዚቃ ተጋበዙ።
የአዜብና የባሏ ጭፍራዎች እንዲህ በቅንጦት ካበዱ ዋናዎቹ ምን ሊኖራቸው እንደሚችል ለመገመት ጠንቋይ መሆንን አይጠይቅም። በአጭሩ የሌቦች አውራና የዘራፊዎች አዛዠ በግፍ የሰበሰበውን ሳይበላ የተጠራው መለስ ከምድራዊ ፍርድ ባያመልጥም በጥይት ያስፈጃቸው ብቻ ሳይሆን በረሃብ ከጠወለገች እናታቸው ደረቅ ጡት እየማጉ በሞት የተነጠቁት ጨቅላ ህጻናት ሳይቀር በአረመኔነቱ ለፍርድ ከጌታ ዘንድ እንደሚያቀርቡት እሙን ነው። የትላንቷ ኮማሪት የዛሬዎ ኤፈርት የተባለው የኢትዮጽያውያንን ደም የሚመጥ ሃገር ገዳይ ሞኖፖሊስት የቢዝነስ ተቋም ሃገሪቷ የሌላትን የገንዘብ አቅም ያካበተ ተጠያቂነቱ ማንና ለምን እንደሆነ የማይታወቅ ብድር ወስዶ የማይመልስ ሂሳቡን እንኳ ኦዲት የማያስደርግ በባልና ሚስት አመራር ይዘወር የነበረው ይህ ተቋም የማን ሆነና ነው መለስ የፔሮል ደመወዝ ተከፋይና የገንዘብ ደሃ የሚሆነው አዜብ መስፍን ለማያቅሽ ታጠኝ ዘራፊነታችሁን አለም ያወቀው ፀሃይ የሞቀው ለመሆኑ ትንሿ ማስረጃ ልጃችሁ እንግሊዝ ሃገር የምትማርበት ክፍያ ከዛች ከባሎ ደመወዝ ላይ ተቆርጦ ነው! ወይስ ልጆቻችሁ እንደ ጓድ መንግስቱ ሃይለማርያም ልጆች በሃገር ቤት እንደ ሌላው ዜጋ የመንግስት ትምህርት ቤት ነው የሚማሩት እሜዬቴ በካድሬነቶ ዘመን ትንሽ እንኳ ሂሳብ አልተማሩም እንዴ ቀጣፊ።
ወይዘሮ አዜብ ሌላው በዚህ ቅብጥርጥሯ ካነሳችሁ ውስጥ የመለስ ሃብት ጭንቅላቱ ነው ለዚህች ምድር ታላቅ ሃሳብ ያመጠቀ ፈላስፋ አድርገዋለች ለመሆኑ መለስ ለጥቅስ እንኳ የሚበቃ እውቀት ትቷል ወይ በየትኛው መጽሃፉ ነው ችሎታው የታየው በየትኛውስ ነጻ መድረክ ላይ ተገኝቶ ተከራክሮ ችሎታውነ ያስመሰከረው መቼመ ሴትየዋ ከዛ ከከብት በረት ካልተሻለው ፓርላማ ላይ ያለከልካይ ይቀባጥር የነበረውን ባዶ የቃላት ጋጋት በሚያቀርበው ዲስኩር እጁ እስኪግል እንዲያጨበጭብ መመሪያ የሚሰጠው ካድሬ ሁካታ ካልጠቀሰች በስተቀር ሌላ ብትጠየቅ የምትሰጠው መልስ አይኖርም። መለስ በዘመኑ ከጻፋቸው ውስጥ ህዝብ ዘንደ የደረሰው የሃገር ልዑዓላዊነትን አሳልፎ የሰጠበት የሻብያ መወድስ የተባለለት ኤርትራ
ከየት ወዴት ብሎ የደረሰው ቀሽም የክህደት ዶሴ ቀለሙ ሳይደርቅ ተሰብስቦ መቃጠሉ ይታወቃል ከዛ በተረፈ ይህ ነው የሚባል በሎጂክና በዲያሌቲክስ የዳበረ የራሱ ፈጠራ ውጤት ሳያኖር ያለፈ ቢሆንም ምንአልባት በብልጣብልጥነትና ውሸትን አጣፍጦ በማቅረብ በመልቲነቱ በመሪነት ደረጃ በዓለም ውስጥ የሚወዳደረው የሌለ የክብረ ወሰን ባለቤት ያደርገዋል።
ለሃገሩ ቀን ከሌት ሲደክም የኖረ እንደነበርም ደስኩራለች፤ ለመሆኑ መለስ የትኛውን በጎ ነገር ነው ለሃገር ያበረከተው፤ ዲሞክራሲን መልካም አስተዳደርን ፤እኩልነትን፤ ልማትን መለስ ለሃገራችን አበርክቷልን መልሱ በተቃራኒው ነው እድሜ ለመለሰ አመራር አንድነታችን ተዳክሞ ቁርሾ በህዘቦች ዘንድ እንዲኖር ተደርጓል፤ ህዝባችን በሃገር የመኖር የመስራት የመማርና ሃሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብት ተነፍጎ ሃገር ጥሎ በመሰደድ የዓለም ክብረወሰን ጨብጧል፤ መለስ በዋሾነቱ በጫት ቃሚነቱና በትንባሆ አጫሽነቱ ጭምር ለትውልዱ መልካም አርዓያ በመሆን ፋንታ የጥፋት ተምሳሌት ሆኖ ያለፈ ምግባረ ብልሹ ነበር። ሌላው መለስ በአገዛዘ ዘመኑ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱም ጭምር ኢትዮጽያን በማድማት ትግራይን ለማበልጸግ እቅድ ነድፎ ዘረኝነት ለትውልድ እንዲተላለፍ ጭምር ያደረ እኩይ ግለሰብ ነበር።
ውሃን ድንጋይ ያናግረዋል እንዲሉ ሴትየዋ እንደ አለት ጠጥሮ ከተጣባት ሃሰተኝነት አልላቀቅ ብላ በሞተው ሰውዬ ላይ እርግማን እንድናበዛ አደረገችን እዚህ ላይ ሴትዮይቱም ሆነ ሌላው ወገን ሊያውቀው የሚገባ በደርግ ዘመን ጠቅላይ ሚንስትር የነበረው በመልከ መልካምነቱ የሚወሳው ፍቅረስላሴ ወግደረስ በግዜው አበላል እንደ ደርግ አባል አለባበስ እንደወግደረስ ተብሎ ይነገርለት የነበረው ይህ ከፍተኛ ባለስልጣን ወያኔ አዲስ አበባን ሲቆጣጠር ከዚህ ግለሰብ ካዝና የተገኘው ገንዘብ በጣም ትንሽ በመሆኑ ለራሳአቸው ለወያኔዎቹ አስደንግጦዓቸው እንደነበር በግዜው ከተለያዩ ጽሁፎች አንብቤያለሁ ፤ አዎን በደረጉ ግዜ የነበረ ባለስልጣን ግፋ ቢል ከጮማና ከውስኪ የማያልፍ በዘረፋ ያልተጠመደ በአብዛኛው በደመወዙ የሚተዳደር እንደነበር ከማንም በላይ ያረጋገጡት ራሳቸው ወያኔዎች ቢሆኑም ከላይ እንደተባለው የወያኔው ባለማሎች የሚያነቀሳቅሱተ የገንዘበ መጠን ለቁጥር የሚታክት ቢሆንም እንዲህ ጥቂቶች በቅንጦት በሚቀብጡባት ሃገር የእለት ጉርስ የአመት ልብስ አጥቶ በየበረንዳው ፍግም ብሎ ከሚያድረው አውታታ ጀምሮ ዛሬ ዛሬ ቤተሰብ ልጆቹን መመገብ ተስኖት ህጻናት በየትምህርት ቤታቸው ጠኔ ሲጥላቸው መስማት የተለመደበት ቁራሽ እንጀራ ማግኘት የከበደበት የመከራ ዘመን ለመድረሳችን አንዱና ዋናው ምክንያት መለስና ቡድኑ ያለቅጥ በዘረፋ መጠመዳቸውና ዘረኛና አድሏዊ በሆነው የልማትና የዕድገት ፖሊሲያቸው ከትግራይ ክልል በስተቀር መላዋ ኢትዮጽያ የሰቆቃ ቀጠና እንድትሆን በማደረጋቸው ነው። አዜብ መስፍን የባሏን ፍሬ አልባ ተረት ትቀባጥር በነበረበት የባሕርዳር ከተማ በትንሽ ኪሎሜትር እርቀት ላይ በዘራቸው ምክንያት ውጡልን ተብለው ለዘመናት ከኖሩበት ቅያቸው ሃብት ንብረታቸው ተቀምተው የወገን ያለህ የሚሉበት ሁኔታ መለስ ዘርቶት የሄደው አረም ሃገር ሊያጠፋ ዳርዳር ያለበት ሁኔት ተፋፍሞ በሚገኝበት ሁኔታ ላይ እንኳ አለመንቃቷ የሴትዮይቱን ለከት የለሽ እብሪት ከማሳየት ባሻገር ገና ሃገሪቱ በዚሁ ሙት መንፈስ ብዙ አበሳ እንደሚመጣባት ጠቋሚ ሆኖ ይታየኛል።
ኢትዮጽያን እግዚያብሄር ይባርክ አሜን !
ትንሳዔዋን ያሰየን!!
አሜን!!!

አዲስ ቤተመንግስት ሊገነባ ነው ተባለ


አዲስ ቤተመንግስት ሊገነባ ነው ተባለ

መጋቢት ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ኢህአዴግ ስድስት ኪሎ በሚገኘው  የስብሰባ  ማእከል ግቢ  ውስጥ አዲስ ቤተመንግሥት ሊገነባ መሆኑን  ምንጮችን በመጥቀስ የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ገልጿል።
የስብሰባ ማዕከል ያለበት ቦታ ለቤተመንግሥቱ ግንባታ የተመረጠው፣  ቦታው ከመሐል ከተማ ወጣ በማለቱ፣ ዙሪያ ገባው ለደህንነት ምቹ ስለሆነ፣ መንግሥት ከምኒሊክ ቤተመንግሥት ወጥቶ የራሱን አዲስ ታሪክ ለመስራት በመፈለጉ ነው ተብሎአል።
በስብሰባ ማዕከል ዙሪያ የሚገኙ የድሃ መኖሪያ ቤቶችና ተቋማት በቅርቡ በልማት ሥም እንደሚነሱ እንዲሁም ህንፃ ለመስራት በዝግጅት ላይ የነበሩ ሰዎችም ህንጻ እንዳይሰሩ መከልከላቸው ታውቋል፡፡
ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በህይወት በነበሩበት ጊዜ ወ/ሮ አዜብ መስፍን በምኒሊክ ቤተመንግሥት ውስጥ ልዩ የመኖሪያ ቤት በከፍተኛ ገንዘብ በማስገንባት ላይ እንደነበሩ ይታወቃል።

ሳዑዲና ዓባይ ምን አገናኛቸው?


ሳዑዲና ዓባይ ምን አገናኛቸው?

Source:-  Fitih le Ethiopia
በዘሪሁን አበበ ይግዛው
ሳዑዲ ዓረቢያንና አፍሪካን (ዓባይን) የከፈለውን ቀይ ባህርን ስናስብ እንዴት ሳዑዲ ዓረቢያ ከዓባይ ጋር ልትያያዝ የምትችለው ብለን ላናስብ እንችላለን፡፡ ምንም ዓይነት መቀራረብም ሆነ ጉርብትና የላቸውም፡፡ የሰውየውን መልዕክት አዘል ንግግር ስናስብ ደግሞ ሳዑዲ ዓረቢያ ለግብፅና ለሱዳን ጠበቃ ለመቆም የተናገረችው ሊመስለን ይችላል፡፡ ይህንንም ከተለያዩ መላምቶችና ምክንያቶች ብለን ከምናስባቸው ጉዳዮች እየተነሳን ልናትት እንችላለን፡፡Abay fallsሆኖም ግን የዓባይ ውኃ ፖለቲካን ጠለቅ ብለን ስንመረምር የምናገኘው እውነት ሳዑዲ ዓረቢያ በአንድም በሌላም መልኩ በዓባይ ውኃ ፖለቲካ ውስጥ እጇን ለማስገባት መፈለጓን እንረዳለን፡፡ ይህንም ከኢትዮጵያው ባሮ (ጋምቤላ) በተከዜ አትባራ (ፖርት ሱዳን) እስከ ቶሽካ ፕሮጀክቶች እንደሚከተለው እንቃኛለን፡፡
ሳዑዲ ስታር የማንና ለማን ነው?
ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጥግ ብቻውን አገር ሆኖ የሚታየው ትልቁ የሚሊኒየም አዳራሽ በአንድ ወቅት በውጭ በኩል ባለው ግድግዳው እጅግ ትልቅ የሆነ ማስታወቂያ ሰቅሎ ነበር፡፡ ስለ “ሳዑዲ ስታር አግሪካልቸራል ዴቭሎፕመንት” ኩባንያ የሚለፍፈው ያ ማስታወቂያ እጅግ አረንጓዴ የሆነ የሩዝ ማሳ ያሳያል፡፡ ባለቤቱ ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሳዑዲው ዜጋ ሼክ መሐመድ አል አሙዲ ናቸው፡፡ በምዕራብ ጋምቤላ ወደ 10,000 ሔክታር መሬት እጅግ ርካሽ በሆነ የሊዝ ኪራይ (158 ብር በዓመት ለአንድ ሔክታር) የተረከበው ይህ ድርጅት እስከ 2020 ድረስ ወደ 2.5 ቢሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ያፈስበታል የተባለው ይህ ፕሮጀክት ዋና ምርቱ ሩዝ ሲሆን፣ በዋናነትም ለውጭ ገበያ የሚቀርብ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በምግብ ራሷን ያልቻለችው ኢትዮጵያ ለም መሬቶችን ለግዙፍ ኩባንያዎች እየሰጠች ሲሆን፣ በዋናነትም የውጭ ምንዛሪን ለማግኘት፣ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማምጣት እንደሆነ ይታመናል፡፡ ከዚህ አንፃር እሳቤው ባይከፋም ትኩረት የሚያሻው ጉዳይ እንደሆነ ግን ሳንገልጽ አናልፍም፡፡
እንግዲህ ሳዑዲ ስታር የተባለው የሼክ አል አሙዲ ድርጅትም ምርቱን በዋናነት ለሳዑዲ ዓረቢያ ሊያቀርብ የታሰበ እንደሆነ የታመነና የተነገረ ነገር ነው፡፡ ባለሀብቱም ከሳዑዲ ንጉሣዊ ቤተሰቦች ጋር ባላቸው መቀራረብ ጋር ተነጋግረው የተጀመረ ግዙፍ ፕሮጀክት እንደሆነ በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሲናገሩ መስማቴን አስታውሳለሁ፡፡ ይህ የሚያሳየን ሳዑዲ ዓረቢያ በአንድም በሌላም መልኩ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው የዓባይ ውኃ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የራሷ የሆነ የጥቅም ፍላጎት አላት ማለት ነው፡፡ ጋምቤላ ውስጥ ያሉ ወንዞች የዓባይ ገባር መሆናቸውን ልብ ይሏል፡፡
ዋናው ጥያቄ የሚሆነው ይህ ጥቅም እያለ እንዴት የሳዑዲው ምክትል መከላከያ ሚኒስትር በእንደዚያ ዓይነት አካሄድ “ኢትዮጵያ የዓረቡን ዓላም ከመጉዳት ቦዝና አታውቅም” ሊሉ ቻሉ? እዚህ ላይ ሊሰመርበት የሚገባ ጉዳይ አገሮች የተሻለ ነው የሚሉትን ጥቅማቸውን እንደሚያሳድዱ ግልጽ ሊሆንልን ይገባል፡፡ ይህ ጥቅማቸውም ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ ባሕላዊ፣ ሃይማኖታዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚህም በመነሳት ሚዛን ወደሚደፋው ጥቅማቸው ያጋድላሉ ማለት ነው፡፡ ሳዑዲ ዓረቢያም ያን እንዳደረገች የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ያምናል፡፡ ይህንም ለመረዳት በሳዑዲ ዓረቢያና በታችኞቹ የዓባይ ተፋሰስ አገሮች (ግብፅና ሱዳን) መካከል ያለውን ከዓባይ ውኃ ጋር የተያያዘ ግንኙነት ማጤን ይገባል፡፡
የግብፁ ቶሽካ ፕሮጀክትና ሳዑዲ ዓረቢያ
አሁን በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው የግብፅ መሪ ሆስኒ ሙባረክ እ.ኤ.አ በ1997 “New Nile Valley Project” “የአዲሱ የናይል ሸለቆ ፕሮጀክት” በሚል ግዙፍ የሆነውን የሰሐራ በረሃን የማልማት ዕቅድ ነድፈው ያም ዕቅድ ተግባራዊ እየሆነ ይገኛል፡፡ በተያዘለት ዕቅድ ከተከናወነ ይህ ፕሮጀክት እ.ኤ.አ በ2017 ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ እየተጠበቀ ቢሆንም፣ በሌላ በኩል የማጠናቀቂያ ጊዜው እስከ 2020 ድረስ መሆኑን በቅርብ ጊዜ ከወደ ግብፅ የወጡ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ይህ ፕሮጀክት በዋናነት ሁለት ምዕራፎች ሲኖሩት አንደኛው በሰሜን ምሥራቅ ግብፅ የሚገኘው የአል-ሰላም ቦይ (canal) ፕሮጀክት ነው፡፡ እሱም ውኃ ከዓባይ ግርጌ በመጥለፍ ወደ ሲና በረሃ ማሻገር ነው፡፡
ይህን በማድረግ ብዙ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬት በማልማት 750 ሺሕ ግብፃውያንን ለማስፈር ያለመ ነው፡፡ ዋናውና ትልቁ ፕሮጀክት ግን የቶሽካ ፕሮጀክት ሲሆን፣ ይህም የደቡብ ምዕራብ ግብፅ በረሃን ለማልማት ያቀደ ፕሮጀከት ነው፡፡ በግብፃውያኑ ዘንድ ይህ ፕሮጀክት አሁን ባለው ሁኔታ እ.ኤ.አ 2020 ያልቃል ተብሎ ይታሰባል፡፡ ፕሮጀክቱ በዋናነት አዲስ ግብፅን በበረሃው ለመፍጠር ያቀደ ሲሆን፣ የተለያዩ በርካታ የውኃ ቦዮችንና የውኃ መምጠጫ ፓምፖዎችን በመገንባት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ይህን በማደረግ በረሃውን በማልማት ወደ ሦስት ሚሊዮን ግብፃውያንን የማስፈር ዕቅድ አላቸው፡፡ እንደ ግብፃውያኑ ከሆነ ይህ ፕሮጀክት ውኃውን የሚያገኘው በናይል ላይ ከተሠራው የአስዋን ግድብ ጀርባ ከሚገኘው የናስር ሐይቅ ነው፡፡ ግብፃውያኑ ይህን ሥራ የትኞቹንም የላይኛውን የተፋሰስ አገሮች ሳያናግሩ ሲሠሩት ውኃውን ከየት እንደሚያመጡት ያሰቡ አልመሰሉም፡፡ እነሱ እ.ኤ.አ በ1959 ከሱዳን ጋር የተፈራረሙት በሌሎቹ አገሮች ውድቅ የተደረገው “ስምምነት” ለራሳቸው በሰጡትና በመደቡት 55.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ራሽን/ኮታ መሠረት “ያላቸውን” ውኃ ለመጠቀም በማሰብ ነው፡፡
ሆኖም ግን ይህ ኮታ በሌሎቹ የላይኛው ተፋሰስ አገሮች ዘንድ ተቀባይነት ስለሌለው ግብፃውያኑ ውኃውን ከየት እንደሚያመጡት አሁንም ግልጽ አይደለም፡፡
እንግዲህ የሳዑዲ ዓረቢያ ሚና በዚህ ፕሮጀክት ላይ ምንድን ነው? ስንል ታላቅ ኢንቨስትመንትን እናገኛለን፡፡ የሳዑዲው ልዑል አል ዋሊድ ቢን ጣላል ቢን አብዱላዚዝ አልሳዑድ “ዘ ኪንግደም አግሪካልቸራል ዴቨሎፕመንት” የተሰኘ ኩባንያ ባለቤት ሲሆኑ፣ ግብፅ ውስጥ በጥቅሉ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ካፒታል ያንቀሳቅሳሉ፡፡ በቶሽካ ፕሮጀክት ደግሞ ከ10 ሺሕ ሔክታር በላይ መሬት ተረክበው የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ለማምረት ከግብፅ የውኃና የመስኖ ልማት ሚኒስቴር ጋር ተፈራርመዋል፡፡ በየዓመቱም በሚሊዮኖች ለዚሁ የቶሽካ ፕሮጀክት አካል ለሆነው መሬት እንደሚያፈሱ ገልጸዋል፡፡ ስለዚህ እዚህ ላይ ሊሰመርበት የሚገባው ጉዳይ ግብፅ ውስጥ መዋዕለ ንዋያቸውን እያፈሰሱ ያሉት የሳዑዲ ቤተሰብ የሆኑት የንጉሡ ዘመድና ልዑሉ እንጂ ከኢትዮጵያዊ እናት የተገኙት ሼክ አል አሙዲ አይደሉም፡፡ ይህም ማለት ለሳዑዲ ዓረቢያ ቤተ መንግሥትም ሆነ ለምክትል መከላከያ ሚኒስትሩ የሚቀርቡት ሼክ አል አሙዲ ሳይሆኑ ልዑል አል ዋሊድ ቢን ጣላል ናቸው፡፡ ስለዚህ የምክትል መከላከያ ሚኒስትሩ ንግግር ከዚህ አንፃርም ሊታይ ይችላል፡፡
ዓባይ ኢትዮጵያና ሳዑዲ ዓረቢያ ከሚለው ፅሁፍ የተወሰደ
በዘሪሁን አበበ ይግዛው
ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው zerihun.yigzaw@graduateinstitute.ch ማግኘት ይቻላል፡

Ethnic-based Politics in Ethiopia


Ethnic-based Politics in Ethiopia

by Teklu Abate
According to the National Electoral Board of Ethiopia, there are 79 political parties registered under Proclamation No573/2008. Of these, only 29% have country-wide (national) identity whereas 71% are regional parties that are organized around ethnic lines.
Of those parties dubbed to have national outreach, some such as All Amhara People’s Organization (AAPO), Ethiopian Peoples’ Revolutionary Front (EPRDF), Geda System Advancement Party, Oromo Federalist Democratic Movement, and All Oromo People Democratic Party do actually have, as their names indicate, ethnicity as their organizing logic. Several armed groups and parties are also following suit. Stated simply, Ethiopian politics is heavily smeared with ethnicism. On average, each nationality (ethnic group) has got its own political party.
That means, the political philosophy of the EPRDF (ethnic federalism) seems to have gotten popularity from the opposition. By necessity, affinity, and/or rhetoric, the majority of opposition political parties make ethnicism their core. Meaning, ethnic federalism is what unifies EPRDF and the opposition. Although the former has got the power/legitimation to enforce the ideology, the latter have been playing a no-less-than-important role in giving it real life.
Some people tend to mistakenly trace the commencement of ethnic politics in Ethiopia to the political participation of the late Professor and accomplished surgeon Asrat Woldeyes. Following the ratification of the FDRE Constitution and in response to the rampant persecution and mass killing of the Amharas, which is still the reality, Asrat was ‘forced’ to form the AAPO. Although the party was technically formed to ‘fight’ all the injustices made against the Amharas, the party was tasked to demand and safeguard freedom and democracy at the national level.
In fact, Professor Asrat’s public speeches, some of which are available on YouTube, aimed at ensuring national unity, peace, and freedom. From the beginning, it was only the great surgeon who opposed the endorsement of the Constitution on the grounds that it undermined Ethiopia’s interest as an independent and unified nation. From that point onwards, Asrat attracted a lot of negative energy from the ruling party. Despite all the odds that happened to him (e.g. he was fired from Addis Ababa University), Asrat intensified his struggle for the freedom of the poor. His formation of the AAPO was not in support of ethnic politics but was an immediate reaction to the massacre of the Amharas. Had Asrat been allowd to lead his life and career, we would have seen the immediate ‘translation’ of the AAPO into a national party.
Ethnic politics in reality has its roots in the now Tigray People’s Liberation Front (TPLF). The founders of this party happened to champion the interest of the Tigray people. After the 17 year protracted war with the Derg, with strong support from the West and with a little bit of luck, they managed to emerge victorious. At the eve of the victory, ‘sister’ political parties were formed representing major ethnic groups such as the Amharas, Oromos, and lately the Southern Nationalities. That fabric metamorphosed into ethnic federalism, which defines current Ethiopian politics. Consequently, the creator and God father of ethnic politics in Ethiopia must be the ruling party. The majority of the opposition political parties just contributed to draw its huge public face- they played a legitimating role. But what is an important question is not who started it but what unwanted consequences are there in relation to ethnic politics.
Implications
Seen at the surface, there seems not to be a problem in practicing politics along ethnic lines. There are several people who even argue that such model of politics allows grass-roots-level participation and is an expression of improved democratic governance, equality, social inclusion, and political consciousness. Theoretically and potentially, this argument seems to hold some water.
It is, however, a practical rarity to successfully fight for freedom and democratic governance while staying dear and near to one’s own ethnicity. I strongly advocate for democracy, the rule of law, and presence of alternative voices, but when it comes to ethnic-based political parties, I do have serious reservations. I rather claim that practicing ethnic politics is not the right strategy to fight injustices and to bring genuine democracy.
One, such political fabric bears no fruits so far. Ethnic politics has been on the horizon since 1991. Political parties proliferated over the years since then. But their contribution to ‘fighting’ injustices is nearly unnoticeable. The reason is not only because the ruling party is systematically narrowing down the playing field but also because of the divided and symbolic nature of the opposition. The opposition is itself seriously divided along ethnic lines and some even see each other as potential threats. Ethnic political parties have a problem going beyond their own localities.
Two, forming ethnic parties is thus limiting, both physically and psychologically. The parties are known only to their respective ethnic groups and to the Electoral Board. The Oromo-based parties, for instance, hardly work in Northern Ethiopia. All the promotion and campaigning is done within their own localities only. They could not compete or win members, resources and names elsewhere within the country. They are thinking within their own boxes.
Three, ethnic parties just confuse the general Ethiopian public. Several ethnic groups each have more than two political parties. It is made unnecessarily confusing to join or support either party. They just frustrate the public. Several people seem to consider opposition parties as hopeless, powerless, disorganized, and fragmented and the like. This kills public motivation to get involved in politics.  Ethnic parties retard and at best kill opposition politics much more than what EPRDF does to the latter.
Four, ethnic politics falsely communicates the presence of freedom and political participation and inclusion. There are several who think that forging a party of some kind is itself a success. Their leaderships, who seem to secure tenurships, roam around villages when elections are around. They proudly talk how their ethnic groups are represented in Ethiopian politics. This sends a false signal to at least people external to Ethiopian politics; they are in fact the voiceless voices. They are noises that constantly irritate the public.
Five, national agendas and interests are being undermined mainly because of ethnically-charged politics. Parties tend to exclusively focus on their own constituencies’ practical matters, albeit unsuccessfully. It is hard to get ethnic parties that raise issues related to Ethiopia’s borders, state of the education sector, unemployment and standard of living, individual freedom, the exodus of the youth to foreign lands, the Ethiopian Diaspora, Ethiopian history and future. Because of the obsession and compulsion with ethnic politics, our future integrity and prospect as a nation seem to be less discussed.
Six, ethnic politics contributes little or no to future peace and cooperation. The more parties love their own ethnic groups and cultures, the less they stand on the common platform- being Ethiopian. Along with other aggravating conditions, ethnic politics could be considered a recipe for future conflict and war among the over 80 nationalities.
Concluding remarks
Ethnicism seems to define Ethiopian politics. It is a common denominator to the ruling party and the opposition. The two, precisely speaking, have a lot in common than their differences. If they differ at all, it is related to getting supremacy and power. The less the difference exists between the ruling party and the opposition, the more frustrating and meaningless would be the political struggle. That is mainly why we do not see any promising development both from Ethiopia and abroad. If the opposition really care about and for Ethiopian politics, they must think and act out of their boxes- their ethnicity. Ethiopia is much more than the sum of all the political parties and ethnic groups.

Friday 29 March 2013

ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቅለው ከሚጓዙት ሰዎች መካከል 2 ህጻናት ታፍነው ሞቱ


ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቅለው ከሚጓዙት ሰዎች መካከል 2 ህጻናት ታፍነው ሞቱ

መጋቢት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በዛሬው እለት ከቤንሻንጉል ጉሙዝ  ክልል በሀይል ተፈናቅለው ወደ ክልላቸው በመጓዝ ላይ ከነበሩት የአማራ ተወላጆች መካከል ሁለት ህጻናት ታፍነው መሞታቸውን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ የአካባቢው ነዋሪ  ለኢሳት ገልጸዋል።
እያንዳንዳቸው ከ70 እስከ 80 የሚደርሱ የአማራ ተወላጆችን የጫኑ 6 አይሱዙ መኪኖች ወደ አማራ ክልል የተጓዙ ሲሆን፣ ሁለቱ ህጻናት በመንገድ ላይ የሞቱት አየር አጥሯቸው ነው። እናታቸው ልጆቿን አልቅሳ በወጉ ሳትቀብር በረሀ ላይ እንዲጣሉ መደረጉን  ነዋሪው ገልጸዋል።
በሌላ መኪና የተሳፈረች አንድ ሌላ ህጻንም እንዲሁ አየር አጥሯት ስትደክም ፣ ሾፌሩ አቁሞ ህክምና እንድታገኝ አድርጓል።
አካባቢውን እንዲለቁ ከተጠየቁት መካከል ሁለት ሰዎች ታርደው መገኘታቸውን ግለሰቡ ገልጸዋል።
ከሁለት ቀን በፊት በቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉ 60 የአማራ ተወላጆችን  ይዞ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ መኪና ተገልብጦ 59 ሰዎች መሞታቸውን መዘገባችን ይታወሳል። የአማራ ክልል ተወካዮች ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ባለስልጣናት ጋር ውይይት ማድረግ መጀመራቸውንም ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉት ሰው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያውያን ደቡብ አፍሪካ የኢሕአዴግን ስብሰባ በተኑ፤ ቴዎድሮስ አድሃኖም ተደብቀው አመለጡ



images(ዘ-ሐበሻ) በደቡብ አፍሪካ ሮዝባንክ ከተማ የተጠራው የኢሕ አዴግ ሥብሰባ በኢትዮጵያውያን ብርቱ ትግል መቋረጡንና መበተኑን የዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ሪፖርተር ከሥፍራው ዘገበ። በልማት ስም የተጠራውና በውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የተጠራው ይኸው ስብሰባ የስር ዓቱ ደጋፊ የሆኑ ከ20 የማይበልጡ ሰዎች ቢገኙም ስብሰባው ይደረግበት የነበረውን ሃያት ሆቴል የስር ዓቱ ተቃዋሚዎች በመሙላት ስብሰባው እንዳይደረግ አድርገዋል።
የድምጻችን ይሰማ፣ የኦነግ፣ የግንቦት ሰባት እና የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲ አባላትና ደጋፊዎች በአንድነት የኢሕ አዴግን ስብሰባ እንዳይደረግ በማድረግ
- ከልማት በፊት የሕዝብ ነፃነት ይቅደም
- በቅድሚያ መገደብ ያለበት ወንዝ ሳይሆን የ ኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ነው በሚል ሕዝቡ ጩኸቱን በማሰማቱ ስብሰባው ተቋርጦ ደጋፊው ሕዝቡ ጥቃት ያደርስባቸዋል በሚል ፍራቻ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖምን ደብቆ ከአዳራሹ አስመልጧል።
የኢሕአዴግ ስብሰባ እንዳይደረግ ያስተጓጎሉት ኢትዮጵያውያን ኢሕ አዴግ በከፈለበት የሃያት ሆቴል አድራሽ ስብሰባ በማድረግ በቀጣይ በአንድነት ስለሚያደርጉት የጋራ ትግል ዙሪያ መነጋገራቸውን፤ የተዘጋጀውን ውሃ እና መጠጥም የኛ ገንዘብ ነው በሚል እንደጠጡት የዘገበው የዘሐበሻ ሪፖርተር የኢትዮጵያ ኢምባሲ በሃያት ሆቴል ስብሰባው ከተስተጓጎለበት በኋላ ደጋፊዎቹን በኢምባሲው ውስጥ መሰብሰቡ ታውቋል። ከኢትዮጵያ ኢምባሲ 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው ከሮዝባንክ ከተማም ኢትዮጵያውያን ወደ ኢምባሲው በመሄድ ተቃውሟቸውን እንዳሰሙም ሪፖርተራችን ጨምሮ ዘገቧል።

Monday 25 March 2013

ከለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ የተሰጠ መግለጫ


ከለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ የተሰጠ መግለጫ


london church


ቀን፤ 21/03/2013
ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላትና ወዳጆች፤ እንዲሁም በUK እና በመላው ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ሁሉ።
  የተቀበሉትን የክህነት ኃላፊነት ጠብቀው በንጽሕና በመቆም እግዚአብሔርንና ሰውን ከማገልገል ይልቅ ሥጋዊ ጥቅምን አስቀድመው የተነሱ ጥቂት የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ካህናት በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥ በሰንበት ት/ቤት ወጣቶችና በምእመኑ መካከል ጸብና ጥላቻ ቀስቅሰው ሁከት እንዲሰፍን በማድረግ ባለፈው ሳምንት ለንደን ወደ ሚገኘው የኢህአዲግ መንግሥት ኤምባሲ በመሄድ ቤተ ክርስቲያንን ያህል ነገር እንደ ግል ንብረት ለማስረከብ እንፈልጋለን በማለት  ከጠየቁ በኋላ ከዛ በማስከተል ቤተ ክርስቲያኗን የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት በመባል በኢህአዲግ መንግሥት ጣልቃ ገብነት ለንደን ላይ ለተቋቋመው አካል አሳልፎ በመስጠት የቤተ ክርስቲያኑን አስተዳደርና ንብረት ለማስረከብ በድርድር ላይ እንደሚገኙ ለማረጋገጥ ተችሏል።
ይህ የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት (ETHIOPIAN ORTHODOX TEWAHEDO CHURCH DIOCESE OF NORTH WEST EUROPE) በሚል መጠሪያ የተቋቋመው ከ11 November 2011ጀምሮ ሲሆን በቻሪቲ ቁጥር 1144634 መሠረት በቻሪቲ ኮሚሽን ተመዝግቦ የሚገኝ ነው።
የዚህ ለሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ተብሎ የተቋቋመ ሀገር ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቢ አዕላፍ ተወልደ ገብሩ ሲሆኑ፤ የሃገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ደግሞ አቡነ እንጦስ የተባሉ አባ ጳውሎስ በህይወት ሳሉ በጎሳና በመንደር ልጅነት መርጠው ጵጵስና በመሾም ወደ ለንደን የላኳቸው ናቸው። በዚሁ ሃገረ ስብከት ውስጥ በትረስቲነት (Trustees) ሆነው የተዋቀሩት ደግሞ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2005 ዓ/ም ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቤተ ክርስቲያንን ጥለው በመሄድ ሌላ ቤተ ክርስቲያናትን የመሠረቱ ሰዎች ናቸው።
ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለንደን ላይ ከተመሠረተች 40 ዓመታትን ያስቆጠረች ሲሆን በዚህ ረጅም የስደት ታሪኳ ወቅት ካለፈው ከደርግ መንግሥትም ሆነ አሁን ካለው የኢህአዲግ መንግሥት ጋር ሳትወግን በልጆቿ ጥረትና ተጋድሎ ከማንኛቸውም የመንግሥትና የፓለቲካ ተጽዕኖ ራሷን ነጻ በማድረግ ሁሉም በእኩልነት የሚያመልክባት ቤተ ክርስቲያን ሆና ኖራለች።
በዚህ የፓለቲካ ወገንተኝነት በሌለው አቋሟም ቤተ ክርስቲያኗ በኢትዮጵያም ሆነ በዓለም ዙሪያ ለሚከሰቱ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ሁሉ ነጻና ፍትሐዊ የሆነ መሥመርን በመከተል ከክርስትና ሃይማኖትና ከቤተ ክርስቲያን የሚጠበቅን የእውነት ተግባራት ስታከናውን ቆይታለች።
ዛሬ በሕይወት ያሉና በህይወት የማይገኙ አባላቶቿ ካህናትና ምእመናን ላለፉት 40 ዓመታት ባደረጉት ከፍተኛ ጥረትና ድካምም በአሁኑ ወቅት ቤተ ክርስቲያኗ በእግዚአብሔር ተራዳኢነት ለከፍተኛ የእድገት ደረጃ የበቃች ከመሆኗም በላይ ወደፊትም ከማንኛቸውም የመንግሥትና የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነጻ በመሆን የበለጠ በማደግና በመስፋት ለስደተኛው ሕዝብና በስደት ላይ ለሚፈጠረው ትውልድ የምትተላለፍ የኦርቶዶክስ ሃይማኖትና የኢትዮጵያዊነት መገለጫ፤ ሃብትና ቅርስ ሆና የምትኖር ነች።
ይህንን የመሰለውን የቤተ ክርስቲያኗን ያለፈ ታሪክና የወደፊት ራዕይ በማፍረስ በአሁኑ ወቅት አስተዳደሯንም ሆነ ሃብትና ንብረቷን ዛሬን ኖሮ ነገ በሚያልፍ የኢህአዲግ መንግሥት የእጅ አዙር ቁጥጥርና ተጽዕኖ ሥር ለማዋል የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪና ተከታዮቻቸው በመፈጸም ላይ ያሉት  የክህደት ሥራ ቤተ ክርስቲያኗን ለዚህ ያበቋት አባላቷም ሆኑ ደጋፊዎቿና መላው በስደት ዓላም የሚገኝ ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሚታገሱትና የሚቀበሉት አይሆንም።
በዚህ መሠረት ይህችን በሕዝብ ጥረትና ድካም ደርጅታ በእግዚአብሔር ተራዳኢነት ለከፍተኛ የእድገት ደረጃ የበቃች ቤተ ክርስቲያንን ያለ ሕዝብ ፍቃድ፤ እውቅናና ይሁንታ በስውር በመደራደር ለሌላ አካል አሳልፎ በመሸጥ መሾሚያና መሸለሚያ ለማድረግ መሞከር አጠቃላይ ስደተኛውን ኢትዮጵያዊ ከማዋረድ አልፎ በቁመናው እንደ መግደል ስለሚቆጠር የቤተ ክርስቲያኗ አባላት፤ የማርያም ወዳጆችና በአጠቃላይ በስደት ዓለም የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ሁሉ የተሰነዘረበትን ጥቃት በመረዳት የተንኮሉን ገመድ በመበጣጠስ ሴራውን አክሽፎ ከእግዚአብሔር በታች የቤተ ክርስቲያኗ ባለቤት፤ አዛዥና ወሳኝ ሕዝብ ብቻ መሆኑን በተግባር የማረጋገጥ ሃይማኖታዊና ኢትዮጵያዊ ግዴታ አለበት።
በዚህ መሠረት የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላት፤ ወዳጆችና በUKና በመላው ዓለም የምትገኙ ስደተኛ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ሕግን ተከትሎ በመሄድ ቤተ ክርስቲያኗን ለማዳን የሚደረገው ጥረት ገንዘብ፤ ጊዜና አቅምን የሚጠይቅ መሆኑን በመረዳት አስተባባሪ ኮሚቴው በሚያወጣው መርሃ ግብርና ጥሪ መሠረት አቅማችሁ የፈቀደውን ሁሉ እንድታደርጉ በቅድስት ማርያም ስም ጥሪአችንን እናስተላልፋለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
http://www.goolgule.com/london-debretsion-church-press-release/

የመለስ ዜናዊ ራዕይና መተካካት ያልተንጸባረቀበት የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ስብሰባ ተጠናቀቀ


የመለስ ዜናዊ ራዕይና መተካካት ያልተንጸባረቀበት የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ስብሰባ ተጠናቀቀ


News, Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy.

የመለስን ራዕይ ከግቡ ሳናደርስ እንቅልፍ አይወስደንም ብለዉ ሲዝቱ የከረሙት የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች “መተካካት” የሚለዉን ዋናዉን የመለስ ፖሊሲ ወደ ጎን ትተዉ ሰሞኑን በተከታታይ ባካሄዷቸው ስብሰባዎች በአብዛኛው ነባር አመራራቸዉን መርጠዉ ድህረ መለስ ጉዟቸዉን መጀመራቸዉን ዘጋቢዎቻችን ከአዲስ አበባ በላኩልን ዜና ገለጹ፡፡ በዚህ ባሳለፍዉ ሳምንት ዉስጥ አዋሳ፤ መቀሌ፤ አዳማና ባህርዳር ላይ በተካሄዱት የየፓርቲዉ ጉባኤዎች ላይ መለስ ዜናዊ መተካካት ብሎ የጀመረዉ ነባር የፓርቲ ሹማምንትን በአዲስ የመተካት ፖሊሰ እምብዛም በተግባር ባይዉልም አራቱም ድርጅቶች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን አንዳንድ ነባር አባላቶቻቸዉን ከፓርቲዉ የስራ አስፈጻሚ ከሚቴ አስወግደዋቸዋል፤  በዚህም መሠረት ደአህዴን ተሾመ ቶጋን፤ ህወሀት ስዩም መስፍንን፤ብርሀኔ ገ/ክርስቶስንና አርከበ ዕቁባይን፤ኦህዴድ  አባዱላ ገመዳን፣ ግርማ ብሩንና ኩማ ደመቅሳን ብአዴን ደግሞ ብርሃን ኃይሉን ከስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት አሰናብተዋቸዋል።
ሟቹ መለስ ዜናዊ በቀየሰዉ ዕቅድ መሰረት መተካካት እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ቀጥሎ ከ2007ቱ ምርጫ በሁዋላ ነባር የአመራር አባላት ሙሉ በሙሉ ይለቃሉ ተብሎ የተገመተ ቢሆንም በሰሞኑ የፓርቲዎች ስብሰባ እንደታየዉ ግን ነባር ታጋዮች ስልጣናቸዉን እንደያዙ እንዲቀጥሉ ተደርጓል። በ2003 ዓ.ም በተደረገዉ የመተካካት ሹምሽር የኃላፊነት ቦታዉን አጥቶ የነበዉ የብአዴኑ አዲሱ ለገሰ ተመልሶ ወደ ስልጣን የመጣ ሲሆን በቅርቡ በወጣት መሪዎች ይተካሉ ተብሎ ሲጠበቅ የነበረዉ በረከት ስምኦን፤ ህላዊ ዮሴፍና፣አባይ ወልዱ ጭራሽ ስልጣናቸውን እያጠናከሩ መምጣታቸዉ ታዉቋል።
በ2003 ዓም በተደረገዉ መተካካት የመንግስትና የፓርቲ ኃላፊነታቸውን የለቀቁት ስዩም መስፍንና ሌሎች ዘጠኝ የህወሃት አባላት ከጤና ጋር በተያያዘ በራሳቸው ፈቃድ  ድርጅቱን ለመልቀቅ ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት የተሰናበቱ ሲሆን የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ግን የእነዚህን ሰዎች መሰናበት ከመተካካት ጋር አያይዞ ዘግቧል። በአጠቃላይ ብዙ ዉጣዉረድና ድራማ የታየበት የዘንድሮዉ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ስብሰባ ሲጀመር የመለስ ዜናዉን ራዕይ ከግቡ እናደርሳለን በሚል መሪ ቃል የተጀመረ ሲሆን ሲፈጸም ግን በመርገጥ “መተካካት” የሚለዉን የድርጅቱን መስራች አላማና ራዕይ በሌላ ነገር በመተካት ተፈጽሟል።
ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በአንድ ጊዜ መልቀቂያ ማቅረባቸው አጋጣሚ ሳይሆን ከመለስ ህልፈት በሓላ በህወሃት ውስጥ ከተፈጠረው ልዩነት ጋር በተያያዘ ሳይሆን እንደማይቀር ምንጫችን ቢጠቅስም ይህን በተመለከተ ለማረጋገጥ ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም፡፡ ብዙዎች እንደሚገምቱት ከአርከበ እቁባይ ጋር ጤነኛ ግንኙነት ያልነበራት  አዜብ መስፍን በዚህ ጉባኤ በድል አድራጊነት ወጥታለች።
ከፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን እስከ 17 ቀን 2005 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ የሚካሄደው የኢህአዴግ ጉባዔ ኃይለማርያም ደሳለኝን በሊቀመንበርነት፣ ደመቀ መኮንን በምክትል ሊቀመንበርነት በድጋሚ ይመርጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡
የወያኔ ኢህአዴግ ድርጅቶች ያደረጉትን ሹም ሽር በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸው አንድ የቀድሞ የሀወሀት ነባር ታጋይ ፡ ምርጫውን “ውሀ ቢወቅጡት ነው” ብለውታል። “ከእነዚህ ሰዎች ምንም የሚጠበቅ ነገር የለም፣ ምን አዲስ ነገር እንደማይፈጥሩም ይታወቃል። የአፈና ስርአቱ እንደሚቀጥል ጥሩ ማሳያ ነው” ብለዋል ታጋዩ።
http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/6695

የቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች በርሃብ ተጎድተው ወደ ሆስፒታል እየተወሰዱ ነው


በቤተክህነቱ በዚሁ ጉዳይ ላይ ስብሰባ እየተደረገነው
img_4680

ከመጋቢት 2 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በትምህርት ማቆም አድማ ላይ የነበሩት የኢትዮጵያ ኦርቶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ስላሴ መንፈሰሳዊ ኮሌጅ ደቀመዛሙርት በርሃብ ተጎድተው ወደ ሆስፒታል እየተወሰዱ እንደሆነ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ገለፁ፡፡
የትምህርት ጥራት መጓደል፣ የአስተዳደራዊ ችግሮችና በምግብ ጥራት መጓደል ምክንያት ጥያቄያቸውን ለኮሌጁ አስተዳደር ቢያቀርቡም ምላሽ በማጣታቸው የትምህርት መቆም አድማ ለማድረግ የተገደዱት ቅድስት ስላሴ መንፈሰሳዊ ኮሌጅ ደቀመዛሙርት በርሀብ ተጎድተው ራሳቸውን በመሳት በመጀመራቸው በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል መወሰድ መጀመራቸውን ስምቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ተማሪዎች ተናግረዋል፡፡   ፍኖተ ነፃነት ጋዜጠኛም በቅድስት ስላሴና በየሆስፒታሎቹ ተዘዋውሮ እንደተመለከተው አባ እያሱ ሰብስቤ የተባሉ ተማሪ በየካቲት 12 ሆስፒታል እንዲሁም ደቀመዝሙር በኃይሉ ሰፊ ምኒሊክ ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ መሆኑን አረጋጧል፡፡ አመሻሹ ላይም ገ/እግዚያብሄር የተባሉ ተማሪ በአምቡላንስ ከኮሌጁ ተወስደዋል፡፡ ተማሪዎቹ በደል አድርሰውብናል ከሚሉዋቸው የኮሌጁ ሀላፊዎች ውስጥ መምህር ፍስሀፂዮን ደሞዝ አካዳሚክ ዲን እና መምህር ዘላለም ረድዔት የቀን ተማሪዎች አስተባባሪ በዋነኝነት ተጠቅሰዋል፡፡
ደረሰ ስለተባለው ችግር ለማጣራት ጥያቄ ያቀረብንላቸው የኢትዮጵያ ኦርቶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሀፊ ብፁዕ አቡነ ህዝቅኤል በኮሌጁ ጉዳይ ስብሰባ ላይ እንደሆኑ ተናግረው የነበረ ቢሆንም ተሰብሳቢ ባለመሟላቱ ስባሰባው እንዳልተደረገ ለፍኖተ ነፃነት የደረሱ መረጃዎች አመላክተዋል፡፡

ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ ባሰሪዎቿ የደረሰባት አሰቃቂ ግፍ


3443500116Victim fighting for her life after suffering first and second-degree burns
Sharjah: A female employer of an Ethiopian housemaid who works illegally in the UAE has been summoned by the Sharjah police for questioning in connection with allegations that an assailant poured hot cooking oil on the maid’s head and back, causing serious burns across the victim’s body.
The housemaid is scheduled to undergo skin grafting surgery on Monday, more than a month after being hospitalised following the incident in her sponsor’s Mirdif villa in early February.
The employer could not be reached on her telephone by Gulf News by press time on Sunday.
Al Qassimi Hospital officials said the maid has been fighting for her life in the intensive care unit (ICU) after suffering first- and second-degree burns. The victim has been heavily medicated as the ICU team helps nurse her back to health.
Gulf News visited Room No 5 in the surgery section at the hospital on Sunday where the victim is receiving treatment.
The victim, identified as B.K., alleged in an interview that her employer threw flour, which the maid was preparing to make samosas, on the floor and ordered her to clean up the mess. The victim told police that while she was cleaning, the Moroccan assailant threw boiling oil on her. She alleged that her employer asked her not to scream.
Excruciating pain
The soft-spoken victim told us that the pain was unbearable. “At first, I lost my eyesight,” said the woman, who regained her sight after three days.
The woman said her employer refused to allow her to seek medical treatment.
“She locked me [in the villa] for three days after the incident. She threatened me that if I told police about the incident, I would be affected because I am an illegal worker,” the maid said.
Without proper medical treatment, her condition worsened. She turned weaker as she was confined inside the villa.
After pleading with her employer that she would not report the matter to the police, the maid was finally released and she sought medical assistance.
She later told police that this wasn’t the first time she had suffered burns at her employer’s villa. The maid was burnt by her employers twice over 50 days, she alleged. On the first occasion, the housemaid said she sustained burns on her leg, a pain she still experiences.
End to abuse
“These maids are human and they come here to earn a decent living to support their poor families. We have decided that this abuse must stop,” Dr Faisal Salman, a plastic surgeon at Al Qassimi Hospital, told Gulf News.
Salman said the hospital admitted the victim on February 24 and recorded burns of first- and second-degree on her face and different body parts.
The maid, Salman said, has been provided necessary treatment and a medical team consisting of three doctors are following her case on a daily basis.
Salman said the hospital’s administration reported the case to the authorities.
Meanwhile, an investigation by Sharjah Police continues.

በቆብ ላይ ሚዶ (አንድ) ትምህርትና ተማሪ ቤት


በቆብ ላይ ሚዶ (አንድ) ትምህርትና ተማሪ ቤት

መስፍን ወልደማርያም
ጥር 2005
በአለፉት አርባ ዓመታት ውስጥ አንድ ልብ ያላልነው መሠረታዊ ለውጥ አለ፤ እንዲያውም የመከራችን ሁሉ ምንጭ ነው ለማለት ይቻላል፤ የመሪዎቻችን አለመማር ብቻ ሳይሆን ትምህርትን መናቅ ወይም ጭራሹኑ መጥላት ዋና ባሕርያቸው ሆነ፤ እስከደርግ ዘመን የነበሩት የአገር መሪዎች ቢያንስ የአንደኛ ደረጃውን (ዳዊት መድገም) የአገሩን ባህላዊ ትምህርት ያከናወኑ ነበሩ፤ ከዚያ በኋላ ለጨዋ ቤተሰብ ልጆች ትምህርት ማለት በቤተ መንግሥት በመዋል የሚገኝ ልምድ ነበር፤ ተፈሪ መኮንን በአሥራ ሦስት ዓመቱ ደጃዝማች የሆነውና ሥልጣን ላይ የወጣው በመወለድ ያገኘውን ዕድል በልምድ እንዲያዳብረው ነበር፤ ተክለ ሐዋርያት ከአሥር ዓመታት በላይ ሩስያ ተምሮ ሲመለስ ተፈሪ ያገኘውን አላገኘም።
በአጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ትውልድ ለሥልጣን መነሻ አይሆንም ነበር ባይባልም፣ ለእድገት ትምህርት አስፈላጊ መሆኑ በመታመኑ የዓየር ኃይል እጩ መኮንኖችም ሆኑ መኮንኖቹ ከደብረ ዘይት እየተመላለሱ ይማሩ ነበር፤ በማታው ትምህርት ብዙ የፖሊስና የጦር ሠራዊት መኮንኖች (ኮሎኔል ሚካኤል አንዶም ጭምር) ይማሩ ነበር፤ ማታ ከተማሩት የፖሊስ መኮንኖች ውስጥ ሁለቱ አምባሳደሮችም ሚኒስትሮችም ሆነው ነበር፤ ከሐረር አካደሚ የወጣ መኮንንም አምባሳደር ሆኖ ነበር፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አገዛዝ የደሀ ልጆች ወደሥልጣን ወንበሩ አልተጠጉም የሚሉ ካሉ የማያውቁ ናቸው፤ ትምህርታቸውን በታማኝነት ከፍነው ቀብረው ሚኒስትርና ሌላም ሹመት ያገኙ የደሀ ልጆች ብዙዎች ናቸው።
ከዚያ ወዲህ ከጨዋ በመወለድ ሥልጣንን ከማግኘት በባለጌ ጡንቻ ሥልጣን ወደማግኘት ተዘዋውረናል፤ ትውልድን ወደእኩልነት የሚገፋ አስተሳሰብ ስንቀበል ብልግናንንና ጡንቻን ወይም ሕገ አራዊትን፣ ተሳዳቢነትንና ዘራፊነትን፣ድንቁርናንና ሚዛነ-ቢስነትን የእኩልነትና የነጻነት አካል አድርገን የተቀበልን ይመስላል፤ በስድነትና በነጻነት መሀከል ያለውን ገደል ባለጌ አያየውም፤ የጨዋ ልጅ ዳዊት ከደገመ በኋላ እንደበቅሎ እየተገራ ያድጋል፤ ከጃፓን እስከእንግልጣር ተመሳሳይ ሁኔታ የነበረ ይመስላል፤ ነገር ግን ወደአውሮፓውያን ሥልጣኔ ስንንደረደር በጃፓናውያንና በእኛ መሀከል የታየው ልዩነት እነሱ ጨዋነታቸውን እንደያዙ እኛ ደግሞ ጨዋነታችንን ትተን መነሣታችን ነው።
አብዮት ወይም ወያኔ ማለት ትምህርትም ሆነ ጨዋነት ለሥልጣን አስፈላጊ እንዳልሆኑ በአደባባይ ማሳየት ሆነ፤ (አብዮትን ከማየቴ በፊት አብዮተኛ ነበርሁ ለማለት የምችል ይመስለኛል፤ አብዮትን ካየሁ በኋላ ግን ወዲያው ጠላሁት፤) አብዮተኛ ማለት አእምሮ የሌለው፣ ኅሊና የሌለው፣ እግዜአብሔር የሌለው፣ ሚዛን የሌለው ከጡንቻ በቀር ሌላ ኃይል የማያውቅ ማለት ሆነ፤ በጡንቻ የማይሠራ ነገር ከሌለ ትምህርት ለምን ያስልጋል? ከሁሉም ይበልጥ የሚያስደንቀውና የሚያስደነግጠው ትምህርትን በሥልጣን የመለወጡ ሙከራ በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መጀመሩ ነው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ላዩን በግልቢያ የተደረጉ ጥናቶች ብዙ ቢሆኑም ጠለቅ ያለና የውስጡን መነሻ እየመዘዘ የሚያወጣ አንድም የለም።
       ደርግ ሥልጣን እንደተሸከመ በየመሥሪያ ቤቱ አንዳንድ መኮንኖችን ‹‹የለውጥ ሐዋርያ›› በሚል ስያሜ ፈላጭ-ቆራጭ አድርጎ አስቀመጠ፤ ትእዛዙ በወታደራዊ ፍጥነት እንደውሀ ከላይ ወደታች እንዲፈስ ተፈልጎ ነበር፤ ነገር ግን ሥራ ሁሉ ወደመቆም ስለደረሰ ደርግ ቶሎ ብሎ ተለወጠና የለውጥ ሐዋርያት የሚባሉትን አነሣቸው፤ ከዚያ በኋላ ደርግ በሁለት ተቃራኒ ሁኔታዎች ተወጥሮ ተያዘ፤ በአንድ በኩል ከባሕር ኃይልና ከዓየር ኃይል፣ ከሐረር የጦር ትምህርት ቤትና ከአገር ውጭም የተማሩ መኮንኖች ነበሩ፤ በሌላ በኩል ከሆለታ ማሠልጠኛ የወጡ ነበሩ፤ በነዚህ በሁለቱ በተለያየ የትምህርት መሠረት ላይ በቆሙ መኮንኖች መሀከል አጉል ፉክክርና መናናቅ ነበረ፤ በተለይም ጄኔራል አማን በተማሩት መከበቡ የተማሩትን ዓይን እንዲገቡ አደረጋቸው፤ አብዛኛዎቹ የከፍተኛ ትምህርት ምሩቆች የሆኑ መኮንኖች በየሰበቡ የተጠረጉት በዚህ ምክንያት ይመስለኛል፤ በዚህም ምክንያት ደርግ ገለባ ያንሳፈፈበት ድርጅት ሆኖ ነበር ለማለት ቢቻልም ከደርግ ውጭ የተመለመሉት ሎሌዎች (ባለሥልጣኖች) የተማሩና በማናቸውም መመዘኛ የማያሳፍሩ ነበሩ።
       የደርግ አባሎችም አለመማር ያስከተለባቸውን ጉድለት ለመሙላት በየሶሺያሊስት አገሩ የይድረስ-ይድረስ ለብ ለብ ትምህርት-ቢጤ በጉርሻ እየተሰጣቸው ተመለሱ፤ (የዛሬ ዘመን ትውልድ ያለጉርሻ ያደገ ነው፤ አሽከር ወይም ልጅ ገበታ ከመቅረቡ በፊት እጅ ያስታጥባል፤ ቆሞ፣ ኩራዝ ይዞ ካበላ በኋላ ጉርሻ ይቀበላል፤ ከዚያም እጅ አስታጥቦ ጉርሻውን ይበላል፤) በአቋራጭ ዲግሪም አገኘን ብለውም ተኩራርተው ነበር፤ በሶሺያሊስት አገሮች ሁሉ እየተሽከረከሩ ትምህርት የተባለውን ቢያርከፈክፉባቸውም ውሀ በስንጥቅ መሬት ውስጥ ሰተት ብሎ እንደሚገባ በእነሱ አንጎል ውስጥ አልገባም፤ ሆኖም በሶሺያሊስት መንግሥቶች ዓለም-አቀፋዊ ፍቅርና ብርቱ ሎሌዎችን የማፍራት ፍላጎት ለስድስት ወራት ያህል በድሎት አቆይተው የፈለጉትን ብራና አስታቅፈው ይልኳቸው ነበር፤ ብዙዎቹ ምንም ቢሆን ኢትዮጵያዊ ይሉኝታ እየያዛቸው ‹‹ዶክተር›› የሚለውን የትምህርት ማዕርግ አልደፈሩትም ነበር፤ ከመሀከላቸው አንዱ ግን እንደተመለሰ በያለበት እየዞረ ‹‹ዶክተር›› መሆኑን ሰዎች ሁሉ እንዳይረሱት እያደረገ አስታወቀ፤ ራሱን ለፌዝ አጋለጠ፤ መሳቂያ ሆነ፤ በመጨረሻም አውነቱና አጉል ፍላጎቱ እየተጋጩ በመቸገሩ ከፎቅ ላይ ተከስክሶ ሁለቱንም ራሱን (ማለት የእውነቱንም የውሸቱንም) አጠፋ፤ ያሳዝናል።
       በቆብ ላይ ሚዶ ጥቅም አይሰጥም፤ በቆብ ላይ ሚዶ ለጌጥ አይሆንም፤ ትምህርትን መሣሪያ አድርገው ሊጠቀሙበት የማይችሉ ሰዎች፣ ከዚያም አልፈው ሥልጣንን በትምህርት ማስጌጥ የማይችሉ ሰዎች ሥልጣንን ያዋርዳሉ፤ በኋላ ሥልጣንም ያዋርዳቸዋል።

“አሁን በስልጣን ላይ ያሉ ሰዎች ባመዛኙ ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ የባንዳ ልጆች የነበሩ”ናቸው


“አሁን በስልጣን ላይ ያሉ ሰዎች ባመዛኙ ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ የባንዳ ልጆች የነበሩ”ናቸው

አቶ ታዲዎስ ታንቱ
ለኢትዮጵያ ህዝብ ክብር ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽነት ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ Abay-Tsehaye-tplf-eprdf-chairman-abay-woldu-and-dep-chair-debretsion-gebremikael
የፋሽቱ ጣሊያን የኢትዮጵያውያን ዋና ጨፍጫፊ የነበረውን ሩዶልፍ ግራዚያኒ ሐውልት መሰራት ለመጀመሪያ ጊዜ ተቃውሞው የተጀመረው በውጭ ሀገር ባሉ ኢትዮጵያውያን ነው፡፡ በሀገር ውስጥ ግን የሐሳቡ ጠንሳሽ “ለኢትዮጵያ ህዝብ ክብር ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽነት ኮሚቴ” ነው፡፡ ከዛ በኋላ የባለዕራዕይ ወጣቶች ማኀበር ሰልፉን ለማስተባበር ፈቃደኛ መሆኑን ገለፀልን፤ በዚህም ላይ ሰማያዊ ፓርቲ እንደሚተባበረን ከገለፀ በኋላ መጋቢት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. ሰልፉን ለማካሄድ ወሰንን፡፡
ብዙውን ጊዜ እኔ በጋዜጦች ስለ አርበኞች ታሪክ ያነበብኩትንና ያወቅሁትን እፅፋለሁ፣ እመረምራለሁ፡፡ የጣሊያኑ ፋሽስት ግራዚያኒ ሀገራችንን በመውረር በአባቶቻችንና እናቶቻችን አርበኞች ላይ የፈፀሙት የግፍ ግድያ አሰቃቂ እንደነበር ስለተረዳሁ፤ ያ ሲቆጨኝ ደግሞ አሁን በጣሊያን ሀገር ለእሱ ሙዚየምና ሐውልት የመሰራቱን ወሬ ከኢንተርኔት ምንጮች ስላየሁ በጣም ተናድጄ እንደውም ተቃውሞ ማሰማት አለብን ብዬ ተነሳሁ፡፡ በኋላ ደግሞ እኛም የአንተ ዓይነት ሐሳብ ነበረን ብለው የባለ ዕራዕይ ወጣቶች ማኀበር አነጋገሩን፡፡ ከዛ በመቀጠል ሰማያዊ ፓርቲ በጋራ እንስራ የሚል ጥያቄ አቀረበ፡፡ በዚህ ምክንያት ሶስቱ አካላት በጋራ ሰልፉን ለማድረግ ዝግጅት ማድረግ ጀመርን፡፡ ስለዚህ
ለኢትዮጵያ ጠላት አይደለም ጣሊያን ሀገር ጨረቃም ላይ ቢሆን ሀውልት እንዲሰራ አንፈቅደም………………………………………..,………..  ……………. …………………… ……………………………………………………………….ሙሉ ቃለምልልሱን  http://www.fnotenetsanet.com/ ያንብቡ

Sunday 24 March 2013

በህወሓት መሪዎች ምርጫ የትግራይ ህዝብ ኣሳዘነ (Abraha Desta from Mekele)


በህወሓት መሪዎች ምርጫ የትግራይ ህዝብ ኣሳዘነ (Abraha Desta from Mekele)

24MAR

ኣንድ

በቅድመ ጉባኤ ስብሰባቸው፣ ሁለቱም ቡድኖች ልዩነታቸውን ለማጥበብ ‘የመተካካት መርህ’ እንደሚተገብሩ ቃል ገብተው ነበር። ከሁለቱም ቡድኖች የተወሰኑ እንደሚቀነሱ (የቀሩ ደግሞ ስልጣን እንደ ሚከፋፈሉ) ስምምነት ነበር። ሸምጋዮቹ ኣዲሱ ለገሰ፣ ሃይለማርያም ደሳለኝና ቴድሮስ ኣድሓኖም (በረከት ስምዖንም እጅ ነበረው) የነ ኣባይ ወልዱ ኣደረጃጀት ስለተረዱ በነ ኣርከበ ቡድን ጫና ፈጥረዋል።

የሸምጋዮቹ ኣቋም ‘ህወሓት መከፋፈል የለበትም፤ ህወሓት ከተዳከመ ኢህኣዴግ ኣቅሙ ይዳከማል፣ ስለዚ compromise ማድረግ ኣለባቹ’ የሚል ነበር። ግዝያዊ ሽምግልናው ሰራና ወደ ጉባኤ ተገባ።
ሁለት
የነ ኣባይ ወልዱ ቡድን ራሱ የመለመላቸው ጉባኤተኞች (በራስ ኣለመተማመን ይመስላል) በስብሰባው 1ለ5 ኣደረጃጀት (የድርጅት ስራ) ተግባራዊ በማድረግ እነሆ የነ ኣርከበ ቡድን መምታት ችለዋል። ዕቅዱ የነ ኣርከበ ቡድን ሙሉ በሙሉ ከስራ ኣስፈፃሚነት ማስወገድ ነበር።
በጉባኤው ‘የመለስ ታሪክና ራእይ’ የኣንድ ቀን ሙሉ ኣጀንዳ ነበር። ‘የመለስ ራእይ’ ተብለው የሚነገሩ ፖሊሲና ስትራተጂዎች በቡድኖቹ ልዩነት ፈጥረው ሲያከራክሩ ውለዋል። ኣንዱ ቡድን ‘የመለስ ራእይ ሳይከለስ ሳይበረዝ መተግበር ኣለበት’ ሲል (እነ ኣባይና ኣዜብ) ሌላኛው ደግሞ ‘መለስ የራሱ ሚና ተጫውተዋል፣ ሁሉም የህወሓት ታሪክ ለመለስ መስጠት ግን የሰማእታት ሚና ማራከስ ይሆንብናል’ ተብሏል (የነ ኣርከበ ቡድን)።
ኣርከበ ‘መለስን ኣታካብዱት የራሳችሁን ታሪክ ስሩ’ (ቃል በቃል ኣይደለም) የሚል ሓሳብ ሲያንፀባርቅ፣ ስዩም መስፍን ደግሞ ‘መለስ ጥሩ ነገር ሰርተዋል ግን በዲፕሎማሲ እሱ የሰራውን ካለ ‘እስቲ የሰራቸውን ነገሮች ዘርዝሩልኝ’ ዓይነት ኣንድምታ ያለው ሓሳብ ሲሰጥ የመለስን ሚና ኣታጋንኑት ለማለት ነበር። ነገር ግን የስዩምን ሓሳብ በኢቲቪና ሬድዮ ፋና ሲቀርብ መለስን ያሞካሸበት ሓሳብ ኣስመስለው እንዳቀረቡት ስምቻለሁ።
ባጠቃላይ ልዩነታቸው ግልፅ ነበር። የነ ኣርከበ ቡድን በነ ኣባይ ወልዱ የተደራጀ 1ለ5 ታክቲክ ተረድተውታል። እንደሚሸነፉ ገብቷቸዋል። ተመካከሩ። በምርጫ ተሸንፈዋል ከሚባሉ ራሳቸው እንድያገሉ (እንዲቀነሱ) ተገደዱ። ጥሩ ማምለጫ ኣገኙ፤ ‘ተገንጥለው ወጡ’ ወይ ምርጫ ተሸነፉ ከሚባሉ ‘በፍቃደኝነት ተሰናበቱ’ ቢባሉ ይሻላል።
ከተቀነሱ ዘጠኝ ሰዎች ሰባቱ የነ ኣርከበ ናቸው። ኣንዱ የነ ኣባይ ወልዱ ሲሆን ኣንድ ደግሞ ከመሃል ሰፋሪዎች ነው። ጸጋይ በርሀ እንዲቀነስ ታስቦ የነበረ ቢሆንም ባልታወቀ ምክንያት ንጉሰ ገበረ ተቀነሰ። ከተመረጡት 45 የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ኣባላት ዘጠኙ ሲቪል እንደሆኑ ከመንግስት ሚድያ ሰምተናል። ዘጠኝ ከኣርባ ኣምስት ትንሽ ነው። ይባስ ብሎ ደግሞ እነዚህ ሲቪሎች የኣለቆቻቸው ታማኝ ኣገልጋዮች የነበሩ ናቸው። በራሳቸው መቆም የሚችሉ ኣይደልም።
በስራ ኣስፈፃሚ ኮሚቴ ኣባልነት ሙሉ በሙሉ በሚባል ሁኔታ እነ ኣባይ ወልዱ ኣሸናፊ ናቸው። ስምንት ለ ኣንድ (ቴድሮስ መሃል ሰፋሪ ቢሆንም) በሆነ ውጤት ኣሸንፈዋል። የነ ኣርከበ ቡድን ኣንድ ነጥብ (ዶ/ር ደብረፅዮን ብቻ) ኣለው። የነ ኣባይ ቡድን ኣባዲ ዘሞና ፀጋይ በርሀ (ሁለቱም የነ ኣርከበ ቡድን ነበሩ) ከስራ ኣስፈፃሚነት በማባረር ኣለም ገብረዋህድ (የኣባይ ወልዱ የቅርብ ወዳጅ)ና ገብረመስቀል ታረቀ ኣስገብተዋል። መለስ ዜናዊ ደግሞ በትርፉ ኪዳነማርያም (የኣባይ ወልዱ ሚስት የነበረች ወይ የሆነች) ተይዘዋል።
የትርፉ ኪዳነማርያም ፖሊትብሮ ኣባል መሆን የነ ኣባይ ወልዱ ቡድን ማሸነፉ ማረጋገጫ ነው የሚሉ ኣስተያየት ሰጪዎች ኣሉ። ‘ትርፉ የፖሊት ቢሮ ኣባል ሆነች’ ሲባል ማን ትዝ እንዳለኝ ታውቃላቹ??? ተወልደ ወልደማርያም። ይህንን ሲሰማ ብፃይ ተወልደ ምን ብሎ ይሆን (ኣጠገቡ በነበርኩ!)?
ሦስት
ባሰባሰብኩት የህዝብ ኣስተያየት መሰረት በህወሓት ጉባኤና ወጤቱ የትግራይ ህዝብ (ኣብዛኛው የፓርቲው ኣባል ጨምሮ) በጣም ኣዝነዋል። በተመረጡ ሰዎች ተስፋ የለውም። ህዝቡ ኣዳዲስ የህወሓት ኣመራሮች በመጠባበቅ ላይ ነበር። የፓርቲው ሊቀመንበርነቱን ይዞ የቀጠለው ኣባይ ወልዱና ምክትሉ እንደሆነ የሚቆየው ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ይቀየራሉ (በሌሎች ወጣት ሙሁራን ይተካሉ ብሎ) ሲጠባበቅ ነበር።
የትርፉ ኪዳነማርያም ፖሊት ቢሮ ኣባል መሆን ብዙ ሰው ኣስገርሟል። ኣባይ ወልዱና ኣዜብ መስፍንም ኣልተጠበቁም። ቴድሮስ ሓጎስ ስልጣኑ ይለቃል የሚል ግምት ነበር። ኣባይ ፀሃየና ኣርከበ ዕቁባይ ለፓርቲው ሊቀመንበርነት ታስበው ነበር (በህዝቡ)። ባጠቃላይ የፖሊት ቢሮ ኣባላት ማንነት ኣስጨናቂ ሁነዋል። ‘እነዚህ ሰዎች መርተው የት ያደርሱናል?’ በሚል የፓርቲው ኣባላት ግራ ተጋብተዋል። በጉባኤው የተሳተፉ ኣባላት ጭምር በድራማው ተገርመዋል።
ህዝቡን በጣም ተስፋ ያስቆረጠው ጉዳይ ‘መተካካት’ ነው። ‘የመተካካት ዕቅድ’ በህወሓቶች ከሽፈዋል ማለት ይቻላል። የመተካካት መንፈስ ፈፅሞ ኣልታየም። ከጉባኤው በፊት በነበረ የማእከላዊ ኮሚቴ ኣባላት ስብሰባ የተስማሙበት ነጥብ ዋነኛው ‘መተካካት’ እንደሚኖር ነበር። ኣሁን የታየው ግን ‘መተካካት’ ሳይሆን የተወሰኑ ሰዎች የመቀያየር ሁኔታ ብቻ ነው።
እነዚህ የተቀያየሩ ሰዎች በምን መስፈርት ነው? በዕድሜ? በስልጣን ሰኔሪቲ? በብቃት? NO. በሁሉም ኣይደለም። በፖለቲካ ልዩነትና በዝምድና ነው። ይሄን የሚያሳየን ህወሓት ተተኪ ወጣቶች ማበራታታት ኣይፈልግም። የመሪዎቻችን ዓላማ በስልጣን መቆየት መሆኑ ግልፅ ሁነዋል። በህወሓት ውስጥ ጥሩ ሓሳብ የያዘ ወጣት ተቀባይነት ኣይኖረውም። በህወሓት ውስጥ ሁነው ለለውጥ መታገል ውጤት ሊያመጣ ኣይችልም።
ደግሞ የትእምት ሃብት ለማን ትተው ስልጣን ሊለቁ??? መተካካት፣ ስልጣን መልቀቅ ኣይታሰብም። በፓርቲው ኣባላት ጥያቄ (በጉባኤ) ቀርቶ በህዝብ ጥያቄም (በምርጫ) ከስልጣን ለመውረድ ፍቃደኞች ኣይሆኑም። የሚያስገደድ ሁኔታ ካላጋጠማቸው በቀር። ዋናው መፍትሔ የሚሆነው የህዝቡ የፖለቲካ ንቃተ-ህልና ከፍ እንዲል ማድረግ ነው።