Saturday 25 July 2015

አርበኞች ግንቦት 7 ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጠ “ሕወሓት እራሱ የሽብር ጥቃት አድርሶ በኛ ላይ ሊያላክክ ስለሆነ ሕዝብ ሆይ ተጠንቀቅ”

እያንዳንዱ ዜጋ የህወሓትን እኩይ ሴራ ተገንዝቦ ራሱን፣ ቤተሰቡንና አካባቢውን ከጥቃት እንዲጠብቅ
* ዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ፣ በሕዝባዊ ኃይሎች ላይ ሊወስድ ያሰበው እርምጃ ተቀባይነት እንዲያገኝለት የሽብር ተግባር ፈጽሞ በአርበኞች ግንቦት 7 ላይ ለማላከክ ወስኗል
* በህወሓት የተደገሰልንን የሽብር ጥቃት ማምከን ይኖርብናል

ዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ፣ በሕዝባዊ ኃይሎች ላይ ሊወስድ ያሰበው እርምጃ ተቀባይነት እንዲያገኝለት የሽብር ተግባር ፈጽሞ በአርበኞች ግንቦት 7 ላይ ለማላከክ ወስኗል። እንዲህ ዓይነቱ እኩይ ተግባር ህወሓት ስልጣን ከመያዙ በፊትም በኋላም ሲያደርገው የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ህወሓት እንዲህ ዓይነቱ ኢሰብዓዊና ዘግናኝ ተግባር ለመፈፀም የሚያስችሉ እኩይ ስለልቦና እና ልምድ አለው።
ginbot 7
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ በቅርቡ የጀመረው የነፃነት ትግል የፈጠረበት መደናገጥ ለመሸፈንና ንቅናቄውን በኢትዮጵያ ሕዝብና በዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብ ለማስወገዝ ያግዘኛል ብሎ ያመነበት ይህን ዘግናኝ ሴራ ከሳምንት በፊት ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁቱን አጠናቆ የነበረ ቢሆንም በወቅቱ የነፃ ሚዲያ አባላት ደርሰውበት ለሕዝብ ይፋ በማድረጋቸው እንዲዘገይ ተደርጎ ነበር። አሁን በደረሰን መረጃ ደግሞ ሴራው ከበፊቱ በባሰ እና ይበልጥ አውዳሚ በሆነ መጠን ተግባራዊ ለማድረግ የህወሓት “ስውር” መንግሥት ወስኗል። በዚህም ምክንያት ይህ የማስጠንቀቂያ መግለጫ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በማያሻማ ሁኔታ እንዲገነዘብ የምንፈልገው ሀቅ የሚከተለው ነው። አርበኞች ግንቦት 7 በደረሰው መረጃ መሠረት ህወሓት በሰላማዊ ዜጎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ወስኗል። የእቅዱ ዓላማ ዘግናኝ እርምጃ በንፁሃን ዜጎችና ሕፃናት ላይ በማድረስ “የሽብር ጥቃቶች ሰለባ” ነኝ በማለት የኢትዮጵያ እና የዓለም ዓቀፉ ማኅበረሰብ አዘኔታ ማግኘት ነው። የዩ. ኤስ. አሜሪካ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን የሚጎበኙ መሆኑ ደግሞ ይህንን እቅድ ተግባራዊ የማድረግ ጉጉቱ እንዲጨምር አድርጓል። ስለሆነም ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ በህወሓት የሽብር አደጋ ውስጥ ነች። የቦሌ ዓለም ዓቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ እና ወደዚያ የሚያደርሰው መንገድ፣ የአፍሪቃ ኅብረት ጽ/ቤት እና የአሜሪካ ኤምባሲ ህወሓት በሽብር ጥቃት ዒላማነት ከመዘገባቸው ውስጥ ቀዳሚዎቹ ናቸው።
አርበኞች ግንቦት 7 በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚቃጡ የሽብር ጥቃቶችን መቃወም ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ተባብሮ ያመክናል። ይህ በህወሓት የተደገሰልንን የሽብር ጥቃት ማምከን ይኖርብናል። እኩይ እቅድን አስቀድሞ አውቆ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ አንድ ዓይነተኛ የሽብር መከላከያ ዘዴ ነው። በዚህ ረገድ በአገዛዙ ውስጥ ያላችሁ የሕዝብ ወገኖች ባለውለታዎች ናችሁ።
የእያንዳንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሕይወት መለኪያ በሌለው መጠን ውድና ክቡር ነው። በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ዜጋ የህወሓትን እኩይ ሴራ ተገንዝቦ ራሱን፣ ቤተሰቡንና አካባቢውን ከጥቃት እንዲጠብቅ አርበኞች ግንቦት 7 በጥብቅ ያሳስባል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45334

Thursday 9 July 2015



Mitsat; የምጻት ቀን ሳይመጣ ከነጻነት ትግሉ ጎን እንሰለፍ!(Yibeltal Gashu)

Thursday 25 June 2015

Philip Hammond warns Ethiopia over treatment of Briton on death row

Foreign secretary condemns detention of Andargachew Tsige in solitary confinement with no access to consular help or right to appeal

Placards demand the immediate release of UK citizen Andargachew Tsige, also sometimes spelled Tsege, who was given a death sentence in his absence. Photograph: Alamy
The treatment of a Briton on death row in Ethiopia is threatening to undermine the country’s relationship with the UK, the foreign secretary has warned.
In an unusually blunt statement, Philip Hammond has called for rapid progress in the case of Andargachew Tsige, who is being held in solitary confinement in an unknown location in Ethiopia.
The foreign secretary’s comments, released a year after Tsige was abducted while transiting through Yemen, is a clear sign of official disapproval of the approach taken by the regime in Addis Abbaba. The Foreign Office is escalating the case beyond confidential diplomatic exchanges.

Andy Tsige pictured with his family. Photograph: Yemi Hailemariam/Family

On Wednesday, Hammond spoke to the Ethiopian foreign minister, Tedros Adhanom Ghebreyesus, about the case on the phone. His statement said: “I am deeply concerned that, a year after he was first detained, British national Andargachew Tsige remains in solitary confinement in Ethiopia without a legal process to challenge his detention.
“I am also concerned for his welfare and disappointed that our repeated requests for regular consular access have not been granted, despite promises made.
“I spoke to foreign minister Tedros and made clear that Ethiopia’s failure to grant our repeated and basic requests is not acceptable. I informed Dr Tedros that the lack of progress risks undermining the UK’s much valued bilateral relationship with Ethiopia.

UN investigates Briton on death row in Ethiopia

“I asked Dr Tedros once again to permit immediate regular consular access and for our concerns regarding Mr Tsige’s welfare to be addressed. I have also asked that the Ethiopian authorities facilitate a visit by Mr Tsige’s family. Foreign Office officials will continue to provide consular support both to Mr Tsige and to his family during this difficult time.”
Tsige’s partner, Yemi Hailemariam, also a British national, lives in London with their three children. She has spoken to him only once by phone since his abduction.
“He’s in prison but we have no idea where he is being held,” she told the Guardian last month. “He said he was okay, but I’m sure the call was being listened to. He had been in Dubai and was flying on to Eritrea when the plane stopped over in Yemen. He hadn’t even been through immigration. We think Yemeni security took him and handed him over to the Ethiopians.
Yemi Hailemariam outside the Foreign Commonwealth Office in April Photograph: Alamy

“They say there was an extradition agreement, but it was so quick there was no time for any semblance of a legal hearing. Yemen and Ethiopia had close relations then. The [Ethiopian] government have put him on television three times in heavily edited interviews, saying he was revealing secrets.
Advertisement
“He has been kept under artificial light 24 hours a day and no one [other than the UK ambassador] has had access to him.”
Tsige, 60 – known as Andy – had previously been secretary general of Ginbot 7, a political opposition party that called for democracy, free elections and civil rights. He first came to the UK in 1979.
The Ethiopian government has accused him of being a terrorist. In 2009, he was tried with others in his absence and sentenced to death. The latest reports suggest that his health is deteriorating.
His lawyer, Ben Cooper, of Doughty Street Chambers, said: “We welcome the Foreign Secretary condemning the illegality of Andy Tsige’s detention, confirming the fact of his solitary confinement and demanding consular visits. But we have a simple ask: please request Andy Tsige’s return home to his family in London. Mr Tsige was kidnapped by Ethiopia at an international airport and the only remedy for kidnap is release. Why has Mr Hammond not yet asked Ethiopia to release Andy so he can return home to England?”
Juan Méndez, the UN special rapporteur on torture, has written to the Ethiopian and UK governments saying he is investigating Tsige’s treatment.

Who is Andargachew Tsige?
Andargachew, or Andy, Tsige fled Addis Abbaba in the 1970s following threats against his life from the military regime, the Derg, which then controlled Ethiopia.
A student activist, he had attracted the attention of the authorities. His younger brother was killed by the security forces. Tsige escaped into the mountains to join opposition groups.
In 1979, after falling out with fellow rebels, he sought asylum in the UK. He studied at the University of Greenwich and obtained full UK citizenship.
Tsige returned to Ethiopia after the Derg was overthrown but moved back to the UK in the early 1990s where he became active in opposition politics.
In 2005, he returned to Addis Abbaba again. He took part in that year’s election and was briefly imprisoned. after being freed, he founded a new political movement, Ginbot 7, from his exile in London.
The organisation was alleged by the Ethiopian government to have launched a failed coup in 2009. Tsige was condemned to death in his absence.
In June 2014, he had flown to the Gulf to give lectures. An unexpected change to his return route saw him fly back via Yemen where he changed planes. At Sana’a airport, he was arrested by guards and put on a plane to Ethiopia on the grounds that there was an extradition agreement between the two countries.
Supporters say that had he been born white and in the UK, the Foreign Office would have taken a more forceful line in campaigning for his release from death row in east Africa.
His partner, Yemisrach Hailemariam, and their three children live in London. She has campaigned actively for his freedom.
In February a delegation of MPs, led by Jeremy Corbyn, his local member, was scheduled to visit Ethiopia in an attempt to secure his release. The trip was abandoned following a meeting with the Ethiopian ambassador.


Source: Theguardian

Tuesday 23 June 2015

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የታፈኑበትን አንደኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ከዓርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በወያኔ ከሰነዓ አለም አቀፍ አውሮፓላን ጣቢያ ታፍነው ከተወሰዱ በዛሬው ዕለት ሰኔ 16 ቀን 2007 ዓ. ም፣ አንድ ዓመት ይሞላቸዋል። የወያኔ አረመኔዎች ይህን ዓይነት የውንብድና ተግባር ሲፈጽሙ በከፍተኛ ደረጃ ያሰሉት፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን በማፈን፣ ንቅናቄው ብሎም ሕዝቡ፣ ለዕኩልነት፣ ለፍትህና ለነጻነት፣ የሚያደርገውን ትግል ለማዳከምና ከተቻለም ደግሞ ለማጥፋት እንደሆነ፣ ምንም የማያጠራጥር ጉዳይ ነው።
ለመሆኑ የወያኔዎች ስሌት በምን ያህል ትክክል ነበር ?
ባለፈው አንድ አመት ውስጥ፣ ወያኔ በአቶ አንዳርጋቸው ላይ የፈጸመው የውንብድና አፈና ተግባር፣ ንቅናቄያችን ከመቼውም ጊዜ ይልቅ በሐገር ውስጥም ሆነ በውጭ ባለው ሕዝብ ልብ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል። ሌላው ቀርቶ ከአፈናው በፊት በተለያዩ ምክንያቶች ንቅናቄያችንን በጥርጣሬ የሚመለከቱ ወገኖች በአደባባይ ወጥተው፣ ” እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ” በማለት አቶ አንዳርጋቸውና ንቅናቄው ለሚታገሉለት ሕዝባዊና ሐገራዊ ዓላማ መቆማቸውን በግልጽ አሳይተዋል። እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎች በሐገር ውስጥ፣ በምድር ላይና በውጭ ሐገር የሚገኘውን የንቅናቄያችንን አካላት ተቀላቅለዋል። ቀደም ሲል በንቅናቄያችን በተለያዩ ደረጃዎች ይሰሩ የነበሩ ዓባላቶች ከአፈናው በኋላ ለትግሉ ያላቸውን ቁርጠኝነት በከፍተኛ ደረጃ ጨምረዋል።
የአቶ አንዳርጋቸውን አፈና ተከትሎ፣ የንቅናቄው አመራር መሰረታዊ የትግል እንቅስቃሴዎቹን በስፋትና በጥልቀት በመፈተሽ አስፈላጊውን ማሻሻያዎችና ማስተካካያዎችን አድርጓል። ንቅናቄያችን አቶ አንዳርጋቸው ለረጅም ጊዜ የደከሙለትን ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በጋራ የመታገለን ጥረት አሳክቶ፣ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዓርበኞች ግንባር ጋር ሙሉ ለሙሉ ተዋህዷል። ከዚህም በተጨማሪ የትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄን ጨምሮ፣ ከሌሎች አምስት በምድር ላይ ከሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ጋራ በጥምረት ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሷል።
በሌላ በኩል ያለፈው አንድ አመት የወያኔ የዘረኛ ዓምባገነን ቡድን ከመቼውም ጊዜ ይልቅ በሕዝብ ላይ የሚፈጽመውን የአፈና፣ የግድያ፣ የዕስርና የድብደባ ውንብድና ተግባር አጠናክሮ የቀጠለበት ዓመት ነበር ። ለዚህም ጸረ ሕዝብ ተግባሩ፣ በባህርዳር ከተማ ሰላማዊ ሰዎች ላይ ያደረሰውን ግድያ፣ በሰላም እንታገላለን ብለው ይንቀሳቀሱ የነበሩትን የአንድነትና የመኢሀድ ድርጅቶች ማፍረስ ብቻ ሳይሆን፣ ዓባሎቻቸው ላይ ያደረሰውን ከፍተኛ የድብደባና የዕስር ወንጀል መጥቀስ ይቻላል። ከዚህም በተጨማሪ በኦሮምያ፤ በአፋር፤ በጋምቤላ፤ በኦጋዴን፤ በትግራይና በደቡብ ክልሎች ይህ ነው የማይባል አፈና፤ ግድያና የሕዝብ መፈናቀል በሰፊው አከናውኗል:: ከምርጫው ጋር ተያይዞም በአደረበት ስጋት የተነሳ በርካታ፣ በተለይ ወጣቶች ላይ፣ የመደብደብ፣የማዋከብ የዕስርና የግድያ ተግባር የፈጸመው በዚሁ አቶ አንዳርጋቸውን ከአፈነበት ቀን ጀምሮ በተቆጠረው የአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ነበር። በጣም የሚገርመው ለራሱ አመቻችቶ ያዘጋጅውን ምርጫ እንኳን ሙሉ በሙሉ አሸነፍኩ ብሎ ከአወጀም በኋላም፣ ከምርጫው በፊት በሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን ወንጀል አጠናክሮ መቀጠሉ ያለበትን የስጋትና ጭንቀት ደረጃ የሚያሳይ መረጃ ነው ።
የወያኔ በራስ የመተማመን ደረጃ ከመቼውም ወቅት ይልቅ እጅግ አሽቆልቁሎ የታየውም ባለፈው አንድ አመት ጊዜ ውስጥ ነበር። በሐገር ውስጥ ይነሳብኛል ብሎ በሚያስበው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ስጋት ምክንያት ይህን ስጋት ለመቀነስ በአንድ መንገድም ይሁን በሌላ ይረዱኛል ብሎ ያሰባቸውን በአካባቢው የራሳቸው ጥቅምና ፍላጎት ያላቸውን ቀደም ሲል ወቀሳ ቢጤ እንደመሰንዘርም ዕልህም እንደመጋባትም ይዳዳቸው የነበሩትን መንግስታት ባለሥልጣኖች በመማጸንና ሐገር ውስጥ በመጋበዝ ማንነቱን አበጥሮ ለሚያውቀው የኢትዮጵያ ሕዝብ በአደባባይ ወጥተው ወያኔ ያልሆነውን ነው ብለው ምስክርነት እንዲሰጡለት ማድረጉ የወያኔ ስጋት የደረሰበትን ከፍተኛ ደረጃ የሚያሳይ ሌላው መረጃ ነው።
በዚህ አጋጣሚ ንቅናቄያችን አቶ አንዳርጋቸውን አፍነው ለወያኔ የሸጡትን የየመን ባለሥልጣኖች ድርጊት በሚመለከት በጊዜው በሰጠው መግለጫ ላይ በግልጽ እንዳስቀመጠው፣ “ጊዚያዊ ጥቅምን በማየት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዕኩልነት፣ ለፍትህና ለነጻነት የሚያደርገውን ትግል ከወያኔ ጋር በቀጥታም ሆን በተዘዋዋሪ በመተባበር ለማፋን መሞከር፣ ታሪካዊ ስህተት መስራት ነው!” እንዳለው ሁሉ፣ ዛሬም የሌሎች መንግስታት ባለ ሥልጣኖች እንደ ትላንትናዎቹ የየመን ባለሥልጣኖች ጊዚያዊ ጥቅምን ብቻ በማየት ሌላ ታሪካዊ ስህተት እንዳይደግሙ ከወዲሁ ለማሳሰብ ይወዳል።
በንቅናቂያችን እምነት ከዚህ በላይ በጥቂቱም ቢሆን ለማሳየት እንደተሞከረው ያለፈው አንድ ዓመት ያሉት መረጃዎች በሙሉ የሚያሳዩት ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን በማፈን ለማዳከም ያሰበው ትግል ይበልጥ ተጠናክሮና ተቀጣጥሎ በርካታ አንዳርጋቸውዎችን ከማፍራቱም በላይ ብዙዎች ለነጻነታቸው መተኪያ የሌላትን ህይወታቸውን እስከመስጠት የሚያደርስ ዕልህ ውስጥ ገብተዋል። ወያኔ እንዳሰበውና እንዳሰላው ትግሉ መዳከም ሳይሆን መሬት እያያዘና እየተጠናከረ በመምጣቱ የወያኔ ስጋት ከመቼውም ጊዜ ይልቅ እየጨመረ ሄዷል። ይህም ሁኔታ የዛሬ አንድ ዓመት በፊት ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን ሲያፍን ያሰላው ስሌት እጅጉኑ የተሳሳተ እንደነበረ በግልጽ አረጋግጧል። የወያኔ የአፈና ተስፋ ገና በአፈናው ማግስት እንደ ጧዋት ጤዛ ተኗል። ከአለፈው አንድ ዓመት ወዲህ በመላው ሀገሪቷ ተጠናክሮ የምናያቸው የወያኔ የጭካኔ እርምጃዎች የሚያመለክቱት ይህንኑ ስጋትና ጭንቀት ነው። የወያኔ የቅዥትና የስጋት የዛፍ ላይ እንቅልፍ፣ ወደ ከፍተኛ ደረጃ ተሸጋግሮና ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ንቅናቄያችን፣ አርበኞች ግንቦት 7፣ ለዕኩልነት ለፍትህና ነጻነት የሚደረግ ትግል፣ በተለይ እንደወያኔ ባለ ዘረኛ አምባገነን ቡድን በበላይነት በሚዘወር ሐገራዊ ሁኔታ ውስጥ፣ ምን ያህል ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን አስቀድሞ ጠንቅቆ ያውቃል። ይህም ሆኖ ግን ባለፈው አንድ ዓመት፣ የትግል ጓዳችን የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው በወያኔ እጅ ከወደቁበት ጊዜ ጀምሮ እየደረሰባቸው ያለውን መከራና ስቃይ እንዲሁም ይህ ሁኔታ በቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ ያስጀመረውን የጭንቀት ዘመን፣ ለአንድ ሴኮንድም ቢሆን መዘንጋት አይችልም።
ንቅናቄያችን አርበኞች ግንቦት 7 በአቶ አንዳርጋቸው ላይ በአፈናው የተነሳ የደረሰው መከራና ስቃይ ብቻ ሳይሆን በአሁኑ ጊዜ ለፍትህ ለዕኩልነትና ለነጻነት በመቆማቸው በወያኔ አረመኔዎች ቁም ስቅላቸውን የሚያዩት በርካታ ቁጥር ያላቸው ዜጎች ሰቆቃ የሚያበቃው፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተባብሮ በሚያደርገው ሁለ ገብ ትግል በመሆኑ ማንኛችንም በአቶ አንዳርጋቸውም ሆነ በሌሎች ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት እንደራሳችን ጥቃት አድርገን የሚሰማን ወገኖች በሙሉ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከታፈኑበት አንድ አመት ወዲህ የተጀመረውን ተስፋ የሚሰጥ እንቅስቃሴ አጠናክረን ወደ ውጤት ደረጃ በማድረስ መጭው ዘመን የሕዝብ የፍትህ የእኩልነትና የነጻነት ተስፋ የሚለመልምበት ፣ የወያኔ አምባገነን ሥርዓት እድሜ የሚያጥርበት ዘመን እንዲሆን የምንችለውን ሁሉ እንድናደርግ ንቅናቄያን ወገናዊ ጥሪውን ያቀርባል።
ክብር ለፍትህ ለእኩልነትና ነጻነት መስዋትዕነት ለከፈሉና እየከፈሉ ላሉ ታጋዮች!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
አርበኞች ግንቦት7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ
ሰኔ 16 ቀን 2007 ዓ.ም.

Saturday 20 June 2015

Ethiopian General Election: An Insult to the People and Democracy (by Graham Peebles)


Every five years the Ethiopian people are invited by the ruling party to take part in a democratic pantomime called ‘General Elections’. Sunday 24th May saw the latest production take to the national stage.
With most opposition party leaders either in prison or abroad, the populace living under a suffocating blanket of fear, and the ruling party having total control over the media, the election result was a foregone conclusion. The European Union, which had observed the 2005 and 2010 elections, refused to send a delegation this time, maintaining their presence would legitimize the farce, and give credibility to the government.
With most ballots counted, the National Election Board of Ethiopia announced the incumbent party to have ‘won’ all “442 seats declared [from a total of 547], leaving the opposition empty-handed…the remaining 105 seats are yet to be announced.” ‘Won’ is not really an accurate description of the election result; as the chairman of the Oromo Federalist Congress, Merera Gudina, put it, this “was not an election, it was an organised armed robbery”.
The days leading up to the election saw a regimented display of state arrogance and paranoia, as the government deployed huge numbers of camouflaged security personnel and tanks onto the streets of Addis Ababa and Bahir Dar. For months beforehand anyone suspected of political dissent had been arrested and imprisoned; fabricated charges drawn up with extreme sentencing for the courts, which operate as an extension of the government, to dutifully enforce.
Despite the ruling party’s claims to the contrary, this was not a democratic election and Ethiopia is not, nor has it ever been, a democracy.
The country is governed by a brutal dictatorship in the form of the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) that has been in power since 1991, when they violently overthrew the repressive Derg regime. The EPRDF speaks generously of democracy and freedom, but they act in violation of democratic principles, trample on universal human rights, ignore international law, and violently control the people.
Independent international bodies and financial donors, from Human Rights Watch and Amnesty International to the European Union and the US State Department, are well aware of the nature and methods of the EPRDF, which is one of the most repressive regimes in Africa. The Committee to Protect Journalists reports that Ethiopia is “the fourth most heavily censored country in the World”, with more journalists forced to leave the country last year than anywhere except Iran.
In the lead up to the recent election, CPJ found that, “the state systematically cracked down on the country’s remaining independent publications through the arrests of journalists and intimidation of printing and distribution companies. Filing lawsuits against editors and forcing publishers to cease production.” Various draconian laws are used to gag the media and stifle dissent, the Anti Terrorist Proclamation being the most common weapon deployed against anyone who dares speak out against the government, which rules through fear, and yet, riddled with guilt as they must surely be, seem themselves fearful.

Democracy and Development

The government proudly talks a great deal about economic development, which it believes to be more important than democracy, human rights and the rule of law, all of which are absent in the country. And, yes, during the past decade the country has seen economic development, with between 4% and 9% (depending on who you believe) GDP growth per annum achieved, the CIA states “through government-led infrastructure expansion and commercial agriculture development.” It is growth, however, that depends, the Oakland Institute make clear, on “state force and the denial of human and civil rights.”
GDP figures are only one indicator of a country’s progress, and a very narrow one at that. The broader Ethiopian picture, beyond the debatable statistics, paints a less rosy image:
Around 50% of Ethiopia’s federal budget is met by various aid packages, totaling $3.5 billion annually. Making it “the world’s second-largest recipient of total external assistance, after Indonesia” (excluding war torn nations, Afghanistan and Iraq), Human Rights Watch states. The country remains 173rd (of 187 countries) in the UN Human Development Index and is one of the poorest nations in the world, with, the CIA says, over 39% of the population living below the low poverty line of $1.25 a day (the World Bank worldwide poverty line is $2 a day) – many Ethiopians question this figure and would put the number in dire need much higher.
Per capita income is among the lowest in the world and less than half the rest of sub-Sahara Africa, averaging, according to the World Bank, “$470 (£287)”. This statistic is also questionable, as Dr. Daniel Teferra (Professor of Economics, Emeritus at Ferris State University,) explains, “In 2008-2011 income per capita (after inflation), was only $131,” contrary to the International Monetary Fund’s (IMF) 2013 report, which put the figure at $320.
The cost of living has risen sharply (current inflation is around 8%) and, as The Guardian reports, “growing economic inequality threatens to undermine the political stability and popular legitimacy that a developmental state acutely needs. Who benefits from economic growth is a much-contested issue in contemporary Ethiopia.” Not amongst the majority of Ethiopians it isn’t: they know very well who the winners are. As ever it is the 1%, who sit in the seats of power, and have the education and the funds to capitalize on foreign investment and development opportunities.
Some of those suffering as a result of the government’s development policies are the 1.5 million threatened with ‘relocation’ as their land is taken – or ‘grabbed’ from them. Leveled and turned into industrial-sized farms by foreign multinationals which grow crops, not for local people, but for consumers in their home countries – India or China for example.
Indigenous people cleared from their land are violently herded into camps under the government’s universally criticised “Villagization” program, which is causing the erosion of ancient lifestyles, “increased food insecurity, destruction of livelihoods, and the loss of cultural heritage”, relates the Oakland Institute. Any resistance is met with a wooden baton or the butt or bullet of a rifle; reports of beatings, torture and rape by security forces are widespread. No compensation is paid to the affected people, who are abandoned in camps with no essential services, such as water, health care and education facilities – all of which are promised by the EPRDF in their hollow development rhetoric.

An Insult to the People

Economic development is not democracy, and whilst development is clearly essential to address the dire levels of poverty in Ethiopia, it needs to be democratic, sustainable development. First and foremost human rights must be observed, and there must be participation, and consultation, which – despite the Prime Minister Hailemariam Desalegn’s duplicitous comments to Al Jazeera that, “we make our people to be part and parcel of all the [developmental] engagements,” – never happens.
The Prime Minister describes Ethiopia as a “fledgling democracy”, and says the government is “on the right track in democratizing the country”. Nonsense. Democracy is rooted in the observation of human rights, freedom of expression, the rule of law and social participation. None of these values are currently to be found in Ethiopia.
Not only is the EPRDF universally denying the people their fundamental human rights, in many areas they are committing acts of state terrorism (one thinks of the abuses taking place in the Ogaden region and the atrocities being committed against the Oromo people, for example, that amount to crimes against humanity.
The recent election was an insult to the people of Ethiopia, who are being intimidated, abused and suppressed by a brutal, arrogant regime that talks the democratic talk, but acts in violation of all democratic ideals.

==============

Graham is Director of The Create Trust, a UK registered charity supporting fundamental social change and the human rights of individuals in acute need. He can be reached at: graham@thecreatetrust.org.

Wednesday 17 June 2015

Popular Opposition Party Semayawi Leadership Beaten and Stabbed to Death by Ethiopia's TPLF Security Operatives

A young, fearless, intelligent, and peaceful man that hails from the small town of Debre Markos in The Amhara Regional State, has been beaten to death by the ruling junta (TPLF) security operatives. Even though Samuel was taken to a nearby hospital, he was determined dead on site during the beating. 

Semayawi Party officials told ESAT Radio on an interview that he was beaten and stabbed to death near his house by the main bus station in Debre Markos city around 7PM on Monday June, 15, 2015. His face was horribly mutilated by beating and stabbing and he lost a lot of blood. He was determined dead before he was even reached the nearby hospital. The Washington based ESAT Radio also replayed the audio of Samuel's interview before the election last month stating that he was taken to the woods by TPLF security agents. He said "two of the men pointed pistols at me and took me to the jungle and I was severely beaten and warned that I will be killed if I won't stop my political activity." His picture after the beating went viral on Facebook. 


Samuel was buried today at a church's graveyard at another small town. However, the mourners were intercepted by police before they reached the town of Debre Markos and were handed over to militias. Up until this report was prepared, their vehicle driver's license was taken and they were surrounded by the militias and prevented to enter the town of Debre Markos. 


Samuel was the co-founder and council member of the popular Semayawi Party. He was a respected Lawyer by profession.

http://ireport.cnn.com/docs/DOC-1250281

ለነጻነት ትግሉ የሴቶች ተሳትፎ (ኤልሳቤጥ ግርማ -ኖርዌይ)

ነጻነትን በተለያየ መልኩ ትርጓሜ መስጠት ይቻላል። ለምሳሌ፦ ተፈጥሯዊ፣ ሰባዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሁም ሀይማኖታዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ነጻነት በማለት መተንተን ይቻላል። ነጻነት የሚለው ቃል በቀላል አገላለጽ ሲገለጽ ከማነኛውም ተጽኖዎች መውጣት፤ ከግዞት ወይም ከባርነት መውጣት እና በራስ መወሰን ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት የጾታ፣ የእድሜና የአካል ልዩነት ሳይገድብ ወይም ማንም ሌላ አካል ሳያስገድደን እና የማንንም መብት ሳንነፍግ በነገሮች ላይ በራስ ወይም በጋራ መወሰን መቻል ነው፡፡ በትክክል ከተረዱት ዲሞክራሲም ሊባል ይችላል፡፡
 በአንድ ሀገር ውስጥ ነጻነትን ለማስፈን የሁሉም ህብረተሰብ አስተዋጾ ወሳኝ ነው። ለምሳሌ ለበለጸጉ ሀገሮች ነጻነት፣ ፍትህ እና ዲሞክራሲ መስፈን የሴቶች ድርሻ በቀላሉ ሊታይ የማይችል ነው። ዛሬም በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና በምጣኔ ሃብታዊ መስክ የሴቶች አስተዋጾ  ከፍተኛ ነው። ካለ ሴቶች አስተዋጾ የሀገር ለውጥ በታሪክ አጋጣሚ ተዘግቦ የተቀመጠ አላየሁም። ምናልባትም የሴቶችን ድርሻች አጉልቶ ካለማሳየት የመጣ ካልሆነ በስተቀር።  የብዙ ሴቶችን ቀጥተኛ ተሳትፎ ብንተወው እንኳ በእናትነት፣ በእህትነትና በሚስትነት ለነጻነት ትግሉ ትልቅ አስተዋጾ አድርገዋል፤ እያደረጉም ይገኛሉ።
በማነኛውም መስክ ውጤታማ ለመሆን በጥሩ ሥነ ምግባር አንጻ፣ ተንከባክባና አስፈላጊውን ድጋፍ ልታደርግ የምትችል እናት፣ አይዞህ የምትል እህት እና ስነ ልቦናዊም ሆነ አካላዊ ብቃት የምትገነባ፣ የደስታ ምንጭ የሆነችና እና ጥበበኛ ሚስት ያስፈልጋል። ሴቶች ትውልድን የመግደልም ሆነ የማዳን ችሎታውና እድሉ አላቸው። እኛ ሴቶች ሁኔታዎች ከተመቻቹልን ሀገርን ሊጠቅም የሚችል ትውልድ ማፍራት እንችላለን፤ ነጻነትና ፍትህን የማስፈን ብቃቱና ችሎታው ያንሰናል ብዬ አላምንም። ይህን ያደረጉ እናቶቻችን በታሪክ ተዘግበው እናገኛቸዋለን። ለአብነት ያክልም ኢትዮጵያውያንን እትጌ ጣይቱን እና ንግሥተ ሳባን ማንሳት ይቻላል።
እትጌ ጣይቱ በነበረችበት ዘመን የወንድ የበላይነት በእጅጉ የነገሠበት ቢሆንም የነበረው ሕግና ባህል ሳይገድባት በፖለቲካው መስክ የነበራት ተሳትፎ ቀላል አልነበረም። ታሪክ እንደሚያስረዳን እቴጌ ጣይቱ በዘመኑ በነበረው ባህልና ወግ መሰረት የአጼ ምኒሊክ ታማኝ ሚስትና የቤት እመቤት መሆኗ ወደ ኋላ ሳያስቀራት የወታደር መሪ፣ የጦርነት ስልት ቀያሽ፣ ታላቅ ሥልጣን የነበራት እና የሴቶችን እኩልነት በተግባር ያሳየች እናትና ወታደር እንዲሁም ባለስልጣንና አስተዋይ መሪ ነበረች። ኢትዮጵያ ሀገራችን በቅኝ እንዳትገዛ አፄ ምንሊክ የውጫሌን ውል በመቅደድ/በመሰረዝ  ሀገሪቱ በጣልያን ላይ ጦርነት እንዲታወጅና ድልን እንድትቀዳጅ ጠንካራ አቋም እንዲወሰዱ ያደረገች ጀግናዋ ጣይቱ ስለመሆኗ ታሪክ ህያው ምስክር ነው።  እቴጌ  ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለመብቱ፣ ለነፃነቱና ለክብሩ የጣሊያንን ወረራ መመከት እንደሚገባው በአጽንኦት አሳስባለች፡፡ በጦርነቱ ወቅትም ጣይቱ በርካታ ወታደር በብቃት መምራቷ፣ አስተማማኝ የሆነ ወታደራዊ ስልት በመንደፍ እና ለጣሊያን የውኃ ምንጭ የነበረውን የውኃ ግድብ በወታደር አስከብባ ጣሊያን እንዲዳከም ማድረጓ፣ ከዚያም ኢትዮጵያውያን ሴቶች በተዋጊነትና በጦርነቱ የተጎዱትን ወታደሮች የህክምና እርዳታ እንዲሰጡ በማድረግ የሴቶች ድርሻ ከፍተኛ እንዲሆን አድርጋለች። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ሀገራችንን በዓለም ከአስጠሩ ነገሥታት መካከል ንግሥተ ሳባ በእንስትነት ቀዳሚውን ቦታ በመያዝ በታሪክ መዘክር ለዘላለም ስትወሳ ትኖራለች።  
አገራችን ኢትዮጵያ የሴቶችን ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዋስትና ለመሰጠት የሚደረጉ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ለመፈረም ብዙ ችግር የለባትም። በተጨማሪም የሚሊኒየም ግብ እንፈጽማለን ከሚሉ ሀገሮች መካከል እንደሆነች በወረቀት ደረጃ ለማስመሰል እየሞከረች ነው። አገራችን የጾታ መድሎን ለማስቀረት እና የጾታ እኩልነትን ለማስፈን በተለያዩ ብሔራዊና ክልላዊ ፖሊሲዎች ውስጥ የሴቶችን ጉዳይ እንዲካተት ማድረጓ ባልከፋ ነበር፡፡ ነገር ግን አድሎው፣ ጭቆናው፣ የጾታ ጥቃቱ እና ከባድ ማኅበራዊ ኃላፊነት መሸከሙ እንዲሁም ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽኖዎች በዘመናዊ መልክ ተጠናክሮ ከመቀጠል ባሻገር ኢትዮጵያ ውስጥ በተግባር የሴቶችን ዋስትና ማረጋገጥ አልተቻለም። ሴቶች በአደባባይ ሲደፈሩ፣ ሲዋረዱ፣ በስደት ማንነታቸው ሲገፈፍ እና ተቃውሞ ለመግለጽ ሲሞከር ሕጉ ከለላ ሊሰጠን አልቻለም። በሕገ መንግሥቱ የተቀመጠው የሴቶችና የሕጻናት መብት፣ የቤተሰብና የወንጀል ሕጉ የሴቶችን ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለማረጋገጥ ተስፋ ሰጪ አልሆነም።
ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማለት ገዥውን ፓርቲ ብቻ መደገፍ፣ ለወያኔ መላላክ፣ ለወያኔ አሽከር መሆንና ለባለ ሥልጣን ሚስት፣ እናትና እህት መሆን ሳይሆን በሀገሪቱ ጉዳይ ላይ የመወሰን፣ በሙሉ ነጻነት የመምራት፣ ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣ የመደራጀት እና የመቃዎም መብት ሲከበር ብቻ ነው። ፖለቲካ ማለት መደገፍ ብቻ ሳይሆን መቃዎምም ነው። ፖለቲካ  ማለት በሀገር ጉዳይ ያገባኛል፣ ይመለከተኛል ማለት ነው። ፖለቲካ ማለት ነጻነት፣ፍትህና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን መታገል ማለት ነው እንጂ እንደ  ወያኔ ለስልጣን ብሎ ህዝብን ማሰቃየት፣ ሀገርን መሸጥ፣ በብሄር፣ በቋንቋ ከፋፍሎ መግዛት እና የሀገርን ሀብት ንብረት ጠቅልሎ  መያዝ ማለት አይደልም።
ኢትዮጵያ ውስጥ ነጻነት፣ ፍትህ፣ የሰባዊ መብት መከበርና ዲሞክራሲ የሚባል ነገር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ መጥቷል። ሴት፣ ወንድ፣ወጣት፣ አዛውንት፣ የተማረ፣ ያልተማረ እና ንጹሃን ዜጎች ሳይባል እስር፣ እንግልት፣ ስደትና ሞት በይፋ እና በስውር በወያኔ ባለስልጣናት ይደርስባቸዋል። በሀገራችን ላይ የሰባዊ መብት ጥሰቶች፣ በዜጎች ላይ የሚፈጸመው ግፍና ጭቆና ከሚባለው በላይ ጨምሯል። የሴቶች መደፈርና የወሲብ ንግዱም በእጅጉ ተባብሶ  ቀጥሏል። አለም ዓቀፍ ድርጅቶች ይህንን በገሀድ እየገለጹ ይገኛሉ። ሆኖም ግን የህወሓትን ማፍያ ቡድን ተቋቁመው ብዙዎች በብዙ ስቃይና መከራ ለነጻነት ዋጋ እየከፈሉ ነው። ሴት እህቶቻችንም በዚህ እውነተኛ ትግል ውስጥ ሰማዕትነትን እየተቀበሉ ይገኛሉ። ብዙ እህቶቻችን በእስር ቤት ውስጥ ስቃይ፣ መከራና ጾታዊ ጥቃት ያስተናግዳሉ። ርዮት ዓለሙን በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። እነ ማህሌት ፋንታሁን፣ ወይንሸት አስፋውን እና ሌሎች በእስር ቤት ለነጻነት ሲሉ ስቃይና መከራ የሚቀበሉ እንስት እህቶቾን ሳላወሳ ማለፍ አልፈልግም።
ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ በሃገራችን ለማስፈን፣ ሰባዊ መብትን ለማስከበር እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የእኛ የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነው። ተፈጥሮና ባህል ለሴትም ለወንድም የተለያየ ኃላፊነቶችን ሰጥተውናል፡፡ በዚህም መሰረት ሴት ልጅ በተፈጥሮ ልጅ በሆዷ ዘጠኝ ወር ተሸክማ መውለድ እና የማጥባት ስራ የሷ ብቻ ነው፡፡ ይህን ምንም ልናደርገው የማንችለው ተፈጥሮ የለገሰችን ጸጋና ኃላፊነት ነው።ነገር ግን በተፈጥሮ የተሰጠን ጾታ እና ማንነት ከትግል ሊበግረን አይገባም። በይበልጥም እኛ ሴቶች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ እኩል እንደወንዶች የመወሰን እና የመምራት ኃላፊነት ቢኖረን በተሻለ መልኩ ሀገርን መለወጥና ትውልድን መቅረጽ እንችላለን። ስለሰባዊ መብት መከበርም ተግተን እንሰራለን፤ ምክንያቱም ርህራሄና ሰባዊነት ተፈጥሮ በለገሰችን በእናትነት አማካኝነት እንዲሁም አመራርንና ማስተዳደርን በማህበራዊ ህይወታችን በሚገባ እናውቃለንና።
ስለዚህ ፖለቲካዊ ተሳትፎ፣ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ መታገል በተፈጥሮ ለወንድ ብቻ የተሰጠ አይደለም። እኛም ሴቶች የሀገር ጉዳይ ያገባናል። በትዳር ደስተኛ ሁኖ ለመኖር፣ ልጆቻችን ስደትን ከመናፈቅ ይልቅ በሰላም በሀገራቸው ታሪክና ባህል ይኮሩ ዘንድ፣ ዜጎች በእኩልነት ተከባብረው ይኖሩ ዘንድ እና ወጣት እህቶቻችን የወሲብ ንግድ እንዳይፈጸምባቸው ለማድረግ በመጀመርያ እኛ ሴቶች ለነጻነት ትግሉ በምንችለው አቅም አስተዋጾ ማበርከት ይጠበቅብናል። ዝናር ታጥቀው፣ ብረት አንግበውና ጋሻ አንስተው ነጻነት ፍለጋ በርሃ የወረዱ እህቶቻችን ቆራጥነትና የዓላማ ጽናታቸውን እኛም ልንላበሰው ይገባል። በእያለንበት ትግሉ ወደፊት ይሄድ ዘንድ እና ትውልድ ሁሉ በነጻነት በሀገሩ ይኖር ዘንድ የድርሻችንን እንወጣ።  ወንድ አደባባይ ሴት ወደ ቤት የሚለውን የማይጠቅም ኋላ ቀር ብሂል ወደ ጎን ትተን በአንድነት፣ በመደራጀትና ዘመናዊ ስልት በመንደፍ ከፋፋይና ዘረኛ ወያኔን ከህዝብ ትክሻ ላይ ለማስወገድ እንትጋ። እኛ ሴቶች ለነጻነት ትግሉ ከፍተኛ አስተዋጾ ማድረግ እንደምንችል በተግባር ማሳየት አለብን። ምክንያቱም ለነጻነት ትግሉ የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነውና።

ፍትህና ነጻነት ለታሰሩ ወገኖቻችን! ፍትህ ለርዮት፣ ለማህሌት፣ ለወይንሸት!!!

Thursday 21 May 2015

የእኛ ዝምታ ለወያኔዎች

በይበልጣል ጋሹ
እኛ ኢትዮጵያውያን ዝምታ ወርቅ ነው እየተባልን ማደጋችን የጠቀመንን ያክል ጉዳቱም በዛው ልክ ነው። እውነት ነው በዝምታ ውስጥ ትዕግስት ፣ ማስተዋልና አርቆ አሳቢነት ይንጸባረቅበታል። ይህንን የማይረዱ አካላት ግን ፍርሃት ወይም ድንቁርና ይመስላቸውና ሰባዊና ዲሞክራሲያዊ መብታችንን ይገፋሉ፣ ይነጥቃሉ፣ ይጨቁናሉም። ሁልጊዜም በዝምታ ውስጥ እንድንኖር ይመክራሉ፣ ያበረታታሉ፣ ያስፈራራሉም። ዛሬ የመገናኛ ብዙኃን በረቀቀበትና በተስፋፋበት ዘመን ያለውን እውነታ ግን በሚገባ እናውቃለን። ነገር ግን እውነትን በውስጣችን አፍነን መናገር እየቻልን እንዳንናገር፣ መስራት እየቻልን እንዳንሰራ፣ ለውጥ ማምጣት እየቻልን እንዳንለወጥ፣ ነጻነትና ዲሞክራሲን መጎናጸፍ እየቻልን የነጻነት እጦት እያሰቃየን ለዘመናት በአምባገነን ስርዓት ተጉዘናል። ከመቼውም በበለጠ ደግሞ ዛሬ ላይ ችግሩ ገዝፎና እጥፍ ድርብ ሁኖ ለብዙ ወገኖቻችን የስደትና እስራት ምክንያት ሁኗል።Ethiopian Silence
እርግጥ ነው ዝምታን ሰብረው ስለ ነጻነት ብዙ የተናገሩ፣ የጻፉ እና በአደባባይ የመሰከሩ ሰዎች እጣ ፈንታቸው ወደ እስር ቤት ተወርውረው የህሌና እስረኞች ሆነው ወርቃማ የአለግባብ ጊዜያቸውን እንዲያሳልፉ መደረጉ ይታወቃል። ለእነዚህም እውነተኛ ኢትዮጵያውያን ስቃይና መከራ መብዛት አይነተኛ ምክንያት የእኛ የብዙዎቻችን ዝምታ መጨመሩ ነው። ምንም በደል ሳይገኝባቸው በሀገራቸው አረመኔያዊ ቡድን ሲታሰሩ፣ ሲደበደቡ፣ ሲንገላቱ፣ ውድ ህይወታቸው በከንቱ ሲሰዋ እያየንና እየሰማን “ነግ በእኔ” የሚለውን እረስተን በዝምታ ቁመን እንመለከታለን። ብዙዎቻችንም ችግሩን የግለሰብ ወይም የፖለቲካ ድርጅቶች ወይም ደግሞ የሰባዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ብቻ እናደርገዋለን።
ምስጋና አይድረሳቸውና ወያኔዎች “እኩልነትን” በተግባር የሚያሳዩበት ትልቁ ተቋም እስር ቤት ነው። ማንኛውም ስርዓቱን የሚቃዎምም ሆነ ግላዊ አስተያየት ሰጪ ሴት፣ ወንድ፣ ወጣት፣ ጎልማሳ፣ አዛውንት ሳይባል ሁሉም በእኩልነት ስቃይ፣ መከራና እስራት ይጠብቀዋል።ከመተቸት/ ከመቃወም እራሱን እስካልገታ ድረስ የወያኔ የማሰቃያ ቦታዎች በራችውን ከፍተው ዘወትር ይጠባበቃሉ። ወገኖቻችን ለነጻነት ብለው ሲታገሉ፣ ለዲሞክራሲ ብለው ሲደሙ፣ ለእኩልነት ብለው ህይወታቸውን አሳልፈው ሲሰጡ እኛ በምን አገባኝነት ቁመን እናያለን። ይህን እኩይ ተግባር ለማስቆም ህዝብ እንደ ህዝብ በአንድነት ከመናገር ይልቅ ዝምታን ስለመረጠ ለወያኔዎች ጋሻና መከታ ሆኗቸዋል።
ወያኔዎች ለሥልጣን ማራዘሚያ አይነተኛ መሳርያ አድርገው የሚጠቀሙበት የህዝብን ዝምታ ነው። ጸሎት አይሉት ድሎት ህዝብ በአርምሞ ውስጥ ”ተመሰገን ማለት ነው የባሰ እንዳይመጣ መጸለይ ነው“ እያለ እንዲኖር በተለይ የወያኔ ተላላኪ የሀይማኖት መሪዎች ሳይቀሩ ህዝብን ለዝምታ ይገፋፋሉ። ወያኔወችም ዝምታን ለማስፈን በአጽንኦት ይሰራሉ፤ ተሳክቶላቸዋል ማለትም ይቻላል። ወያኔዎች ለክፋትና ለተንኮል፣ ሀገርን ለማጥፋት ህዝብን ለመበደል ያእቀዱትን እቅድ ተግባራዊ ለማድረግ የሚደርስባቸው የለም። ምክንያቱም ሰውን ለመግደልም ሆነ ለማሰቃየት ምንም አይነት ሰባዊ ርህራሄ የሚባል ነገር በውስጣቸው የለምና።
መቼም በዚህ በአለንበት በሰለጠነው ዘመን የወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ ለሀገራችን ኢትዮጵያ ይበጃል፣ ይጠቅማል፣ ይመጥናል የሚል ህሊና ያለው እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ይኖራል ብሎ መገመት ያዳግታል። ሥርዓቱ ከአምባገነናዊነት ባሻገር ብሄራዊ ቀውስ እና የሀገርርን ሉዓላዊነት ጥያቄ ውስጥ ያስገባ፣ የብዙ ንጹኃንን ደም ያፈሰሰ፣ ብዙዎችን ለስደትና እስራት የዳረገ አረመኔያዊ አገዛዝ ነው። በዓለም አቀፍ ደረጃም ይህ የወያኔ እኩይ ተግባር የተገለጠና የተመሰከረለት ነው። ለዚህም መረጃም ማስረጃም እኛው እራሳችን ነን። በዝምታ ውስጥ የማንኖር እና እንደ ሀገር የምናስብ ከሆነ በቀጥታ ማስፈራርያ፣ ዘለፋ፣ እስራትና እንግልት በወያኔዎችና ተላላኪዎች ደርሶብናል፤ እየደረሰብንም እንገኛለን። ነገር ግን ይህ ገደብ የለሽ ማስፈራርያ ለዝምታችን ምክንያት መሆን የለበትም፤ ይልቁንም ለመብት፣ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ እንድንነሳ ግፊት ያደርጋል እንጂ። እውነት ነው ፍርሃት እስኪመስል ድረስ ዝምታችን በእጅጉ በዝቷል፤ የዝምታችንም ውጤት ለወያኔወች አረመኔያዊ ኃይል እንዲያገኙ እና በወገኖቻችን ላይ ሰይጣናዊ ድርጊት እንዲፈጽሙ፣ ጥጋብንና ማንአለብኝነትን እንዲላበሱ እድል ፈጥሮላቸዋል።
እንደሚታወቀው በየአምስት ዓመቱ የይስሙላና የቅርጫ ምርጫ በደረሰ ጊዜ ለሀገርና ለወገን ዴንታ የሌለውን ጥቅመኛ ቡድን ፍትሃዊ ምርጫ ለማስመሰል መራጭ በማድረግ አብዛኛውን ህብረተሰብ ደግሞ በዝምታ እንዲያሳልፍ ይደረጋል። ይህ ሥርዓት ለሀገር የሚበጅ ሥርዓት አይደለምና ይወገድ ብሎ እንዳይናገር “ብንናገር እናልቃለን” የሚለውን የሞኝ ፈሊጥ እንዲያስተጋባ የዝምታ ካባ ይደረብለታል። ምርጫው እንደሆነ የተበላ እቁብ መሆኑ ዓለም በሙሉ ያውቀዋል። በወያኔ “በጎ ፈቃድ” በምርጫ እንዲሳተፉ የተደረጉት ተቀዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችም ምርጫውን ዲሞክራሲያዊ ለማስመሰል ቅመም ወይም ቅባት እንጂ ወያኔ በስልጣን ላይ እያለ መቀመጫ ወንበር አግኝተው ፓርላማውን እንዲቀላቀሉ አይደለም። ውይይት፣ ትችት፣ ማካፈልና አብሮ መስራት የወያኔ ባህሪ አይደለም። 24 ዓመታት የወያኔን ስርዓት በሚገባ አይተናል፤ ባህሪውንም ተረድተናል። “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” እንዳለች አህያ ህዝብና ሀገር ለማጥፋት በአህያ አስተሳሰባቸው ተግተው እየሰሩ ነው።
የተባበሩት የዓለም መንግስታት፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ዲሞክራሲን የሚናፍቁ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና ግለሰቦች የኢትዮጵያ ምርጫ የይስሙላና ኢ-ፍትሃዊ እንደሆነ ከአለፉት ምርጫዎች ስላረጋገጡ ከመታዘብ እራሳቸውን አቅበዋል። እውነት ነው ለውጥ ለማይመጣ ነገር ገንዘብ፣ ጉልበትና ጊዜ ማቃጠሉ ከንቱ ነው። እኛም በምርጫ ለውጥ እንደማይመጣ በሚገባ እናውቃለን፤ ግን ዝምታችን እስከ መቼ ይዘልቃል? በዝምታስ ለውጥ ማምጣት ይቻላልን? በዝምታ ለውጥ ያመጣ ሀገር በታሪክ አጋጣሚ ተዘግቦ አላየንም። እውነት እላችኋለው “እውነትን እውነት፡ ሀሰትን ሀሰት” እስካላልን ድረስ ለውጥ ሊመጣ በፍጹም አይችልም። ነጻነትን፣ ፍትህንና ለውጥን እኛ እናመጣዋለን እንጂ እራሱ በር አንኳኩቶ ሊመጣ አይችልም።
ጭቆናው ጨምሯል! ሰው በሰውነቱ፣ በኢትዮጵያውነቱ፣ በተግባሩና በሥራው ሳይሆን በማንነቱ፣ በሚናገረው ቋንቋ፣ በተወለደበት አካባቢ ስም እየወጣለት ለስቃይና ለመከራ ይዳረጋል። የሥጋ ቆጠራ ይመስል የዘር ግንዱ እየተመዘዘ፣ የተጸውዖ ስም ሳይቀር እየታየ አድሎ ይደረግበታል። ወያኔን የሚቃረን የፖለቲካ አመለካከት ማንጸባረቅ እንኳ የማይታሰብ ነው። ወያኔዎች የጸረ ሽብር ህጉን ተፈጻሚ የሚያደርጉት በእንዲህ አይነት ሰዎች ላይ ነው። ይህን እያየንም፣ እያወቅንም ዝምታ!
ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ ጦማርያን፣ የሰባዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ተማሪዎች፣ ነጋዴዎች፣ አርሶ አደሮችና አያሌ ንጹሃን ዜጎች በግፍ ሲታሰሩ፣ ሲሰደዱና ሲገደሉ በዝምታ ከመመልከት በላይ ምን የከፋ ነገር ይኖራል። ፈሪ የሚል ቅጽል ስም ቢወጣልንም ስህተት ነው የማለት የሞራል ድፍረት አይኖረንም። አዎ ብዙዎች በግፍ ሲታሰሩና ሲሰደዱ በዝምታ ተመልክተናል፤ ዛሬም ሰማያዊ ወይም ምዕራባዊ ኃይል እየጠበቅን ይሆን እንጇ ቁመን እያየን ነው። ለውጥ ለሌለው የይስሙላ ምርጫ ጆሮአችንን ሰጠን የወያኔን ተራ የሀሰት ወሬ በዝምታ ውስጥ ሆነን እየሰማን እንገኛለን።
በአጠቃላይ የእኛ ዝምታ ለወያኔች መከታ፣ ስልጣን ማራዘሚያ፣ ሃብት ማካበቻ፣ ድንቁርና፣ ማንአለብኝነት ማጎልበቻ ሲሆናቸው ለሀገራችን ኢትዮጵያ ድህነት፣ ኋላ ቀርነት፣ ለውጭ ዜጎች ገነት ለልጆቿ ሲዎል እንድትሆን ሲያደርጋት ለእኛ ለህዝቧ ደግሞ እስራት፣ ስደት፣ እንግልት፣ መከራ፣ የነጻነትና ፍትህ እጦት፣ የመብት ጥሰት እና ውርደትን እንድናስተናግድ አድርጎናል። እኛ በሌሎች ሀገሮችም ሳይቀር እንደ ሰው እንዳንታይ እና ክብር እንድናጣ ዝምታችን አሉታዊ አስተዋጾ አድርጓል።
ስለዚህ ዝምታን በመስበር “የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውን እንመሰክራለን” እንዲሉ ለሀገር የማይጠቅም ለህዝብ የማይሆን ይህን አረመኔያዊ የወያኔ አገዛዝ ከስር መሰረቱ ማስወገድ ጊዜ የማይሰጠው የቀን ተቀንና የዕለት ተግባር ማድረግ ይገባናል። ሀገር ለባዕድ ስትሸጥ፣ ህዝብ በድህነት ሲሰቃይ፣ ብዙዎች በግፍ ሲሰደዱ፣ ሲታሰሩና ሲገደሉ እያዩ እንዳላዩ፣ እየሰሙ እንዳልሰሙ መሆን የታሪክ ተወቃሽ ያደርጋልና ዝምታ ይብቃ። ሌባን ሌባ ለማለት እንደምንደፍር ሁሉ ወያኔንም የሌቦች፣ የቀማኞችና የወንበደኞች አለቃ ነውና በቃ ከህዝብ ጫንቃ ላይ ውረድ ማለትን እንድፈር።
ከአለመናገር ደጃዝማችነት ይቀራል እንደሚባለው ዝምታን አስወግደው ለነጻነትና ለፍትህ የሚናገሩ ብዙ ኢትዮጵያውያን በተለያየ ቦታ ዝምታ ይብቃ እያሉን ነው። በእስር ቤት ሆነውም ሀገራዊ መንፈሳቸው ነጻነት! ነጻነት! ነጻነት! እያለ በአደባባይ ይሰብካል። እውነተኛ ኢትዮጵያዊ አንደበታቸው ወያኔን ያሸብራል። ሰውን ያክል ክቡር ፍጡር በእስር እያሰቃዩ ፍትሃዊ ምርጫ እያሉ ማውራት አግባብ እንዳልሆነ በዝዋይ፣ በቃሊቲ፣ በቂሊንጦ፣ በማዕከላዊ፣ በሽዋ ሮቢት እና በሁሉም የማሰቃያ እስር ቤቶች የሚገኙ ውድ ኢትዮጵያውያን ድምጻቸው ያስተጋባል። ለይስሙላ ምርጫ ከመሰለፍ ይልቅ ለነጻነት ተሰለፉ ይሉናል።
ለነጻነትና ለዲሞክራሲ ግንባታ በርሃ ወርደው ብረት አንግበው የሚታገሉ ወገኖቻችን ኑ በህብረት ወያኔን እናስወግድ፤ ጉልበት ያለህ በጉልበት፣ እውቀት ያለህ በእውቀት፣ ገንዘብ ያለህ በገንዘብ ተደጋግፈን ለተከበረች ኢትዮጵያ እንድረስላት በማለት ሀገራዊ ጥሪ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። ነገር ግን በያለንበት ወያኔን ማሳደድና ማዋከብ ከቻልን ሁላችንም በርሃ መውረድ ላይጠበቅብን ይችላል። በተለይ እኛ ወጣቶች!ጉልበታችንን፣ ኃይላችንንና አቅማችንን ተጠቅመን ወያኔን የምናስወግድበትን ስልት በመንደፍ ከሁልጊዜ ስቃይና መከራ ለተወሰነ ጊዜ ትግል ማድረጉ በእጅጉ የተሻለ ነውና በህብረትና በአንድነት ሀገር የማዳንን ትግል እንቀላቀል። በሀገር ተከብሮና ተዝናንቶ መኖር ሲቻል ስደትን አማራጭ መንገድ በማድረግ ለባህር ቀለብ፣ ለአሸባሪዎች የትንሳኤ በግ፣ ለአረብ የጥጋብ ማስታገሻ መሆን የለብንም። በአጠቃላይ ዝምታን በማስወገድ ህዝብን በማስተባበር ነጻነትን ለማወጅ ቆርጠን እንነሳ እላለሁ።
ዝምታ ይብቃና የወያኔን የይስሙላ ምርጫ በመቃወም ነጻነታችንን ለመጎናጸፍ አማራጭ መንገዶችን እንጠቀም!!!
አስተያየታችሁን በ“gashuy@gmail.com ” ጻፉልኝ።

Wednesday 20 May 2015

ግልጽ ደብዳቤ ለፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ ከየሸዋስ አሰፋ ቅሊንጦ (ዞን9)

Yeshiwas
ክቡር ፕሬዘዳንት ለመጀመሪያ ጊዜ በቴሌቪዥን ያየሁዎትበፕሬዘዳንትነት ለመመረጥ በተወዳደሩባቸው ጊዜያት ሲሆን በወቅቱ ከእርስዎ ምርጫ ጋር በተገናኘ ድምጽ መስጠት ባልችልም ምርጫውንለመከታተል ብዙ ጊዜዬን እነዳሳለፍኩ አስታውሳለሁ፡፡ በወቅቱ ይህንንያደረኩት የተመረጡት ለአሜሪካን መሆኑን አጥቼው ሳይሆን የታላቅዋ አገር መሆንዎ በወቅቱ ከነበረው ተስፋ ጋር ተደምሮ ለአለም ሰላምሊያበረክቱ የሚችሉትን በጎ ምግባር ተስፋ በማድረግ ነበር ፡፡
አሁን ይህንን ደብዳቤ እንድጽፍልዎት ያነሳሳኝግን ዛሬ መንግሰትዎ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሰራተኛ እና የመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ምክትክ ሚኒስትሯ ዌንዲ ሸርማንአዲስ አበባ መጥተው የተናገሩት ንግግር ነው ፡፡ መቼም አንደሚገምቱትአንደማንኛውም ኢትዮጲያዊ ንግግራቸው ስሜቴን መርዞታል፡፡
ምክትል ሚኒስትሯ የተናገሩት ብዙ ጉዳይ ላይ ነው፡፡ ስለሽብርተኛነት ፣ ስለምስራቅ አፍሪካ ሰላም፣ ስለግንቦት 7 ስለ ኢትዬጵያ እድገት ሰላም ዴሞክራሲ ወዘተ፡፡ ዋና ጉዳይ ብለውየገለጹት የቀጣዩ የ2007 ምርጫ ላይ የሰጡት አስተያየት ግን እጅጉንአሳዝኖኛል፡፡ ምርጫው ከጊዜ ወደጊዜ እየተሻሻለ ነው መጪው ምርጫ ዴሞክራሲያዊ ፍትሃዊና ተአማኒነት ያለው እንደሚሆን አንጠብቃለን ነበር ያሉት፡፡ ይበልጥ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ የልእለ ሃያልዋ አሜሪካ አቋምመሆኑን መግለጻቸው ነው ፡፡ መቼም በፍቃደኝነት ካልሆነ በስተቀር ምንም አይነት አጭበርባሪ አምባገነን በዚህ ደረጃ ያጃጅላቸዋልብሎ ማመን ይከብዳል፡፡
ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችበመዘርዘር ውድ ጊዜዎን አላጠፋም፡፡ ነገር ግን በኢትዮጵያ በየአምስት አመቱ ምርጫ በመጣ ቁጥር የሚሰሩና እየተሰሩ ያሉ ምርጫ አደናቃፌዎችንልገልጽልዎት እፈልጋለሁ፡፡ ከእነዚህ አደናቃፌዎች መካከል መጨውን ምርጫ 2007 ከመቼውም ጊዜ በላይ የከፋ የሚያደርጉት
1. ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከመዋቅሩ ውጪ ባሉ ግለሰቦች የሚሽከረከር አቅመቢስ ተቋም ከመሆኑም ባሻገርዛሬ ገዥው ቡድን አንደራሱ የፓርቲ አካል የሚያሽከረከረው መሆኑ
2. ገዥው ቡድንም ምንም አይነትየፓርቲ ቅርጽ የሌለውና ከ20 አመታት በፌት ጀምሮ በአሜሪካን መንግሰት በአሸባሪነት ተፈርጆ የነበረው ህወሃት በጠርናፌነት ጠቅልሎየያዘውና ምርጫውንም የስልጣን ጊዜውን ለማራዘም ብቻ የሚጠቀምበትመሆኑ
3. ምርጫ በመጣ ቁጥር 1987ኦነግን ፣ በ1992 መአህድን፣ በ1997 ቅንጅትን ፣ በ2002 አንድነትን በ2007 ሰማያዊን ኢላማ በማድረግ የተሻሉ ተፎካካሪፓርቲዎቸን በማጥፋት አመራርና አባላቶቸን በማሰር ብቻውን የሚወዳደር መሆኑ
4. በፓርቲና በመንግሰት መካከልያለው ልዬነት ጭራሽ ጠፍቶ የፍትህ አካላትና ፍርድ ቤቶቸን ሳይቀር በቀጥታ የፓርቲ አገልጋዮች ያደረገ መሆኑ
5. ከመቼውም ጊዜ በባሰ ሁኔታዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ምንም የግል ሚዲያ የሌለ መሆኑና 90 ሚሊዬን ህዝብ በሚኖርበት አገር 2000 ኮፒ የሚያሳትሙ ህትመቶችን ሳይቀርበመዝጋት ጋዜጠኞችና ጦማርያንን ወህኒ የከተተ መሆኑ
6. ከምርጫ 97 በኋላ በወጣውአፋኝ አዋጅ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ምንም አንዳይሰሩ ተደርገው ትውልዱ መሪ እና አስተማሪ ያጣ መሆኑ
7. ህገ መንግስቱ ን በጸረ ሽብርአዋጅ በመጣስ የተለያዬ የአገሪቱን ዜጎች በተለይ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ኢትዮጲያውያንን በጅምላ ማሰር ፣ በሃይማኖት ጣልቃ መግባት በተለይየእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያንን በጅምላ በማሰር እስርቤቶችን በፓለቲካ እስረኛ የሞላቸው በመሆኑ
8. በአገዛዙ በተለያዬ የስልጣንእርከን ያሉ ግለሰቦች ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ ከልክ ያለፈ ገንዘብ እየመነዘሩና ሙስና ውስጥ የተዘፈቁ በመሆኑ እና ዛሬም በአልጠግብባይነት በዚሁ መቀጠል የሚፈልጉ መሆኑ
9. ምርጫ 2007 የአውሮፓ ህብረትንጨምሮ ሌሎች ተአማኒነት ያላቸውና አምባገነኖችን የማጋለትጥ ልምድ ያላቸው ድርጅቶች የማይታዘቡት መሆኑ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ፕሬዘዳንት ኦባማ-በዛሬዋ ኢትዮጵያ እነዚህ ችግሮች አይኑን ለጨፈነ አንኳን የሚዳሰሱ ሃቆች ሆነው ሳለ የመረጃ ሰዎችዎ ይስቷቸዋል ብዬ አላምንም፡፡ የገዥዎችፕሮፓጋንዳ ስክሪን ሴቨር ኑሮ የሚገለጸውን እውነታም የሚሸፍንባችሁ አይመስለኝም፡፡ ታዲያ ከላይ የተገለጹት መባባሶች መሻሻል ተብለውሲገለጹ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ምን የሚሰማው ይመስልዎታል? ይህ የተገለጸው ደግሞ በዴሞክራሲ በተመረጠ መንግስትና መሪ ካለበት አገርሲሆንና ገዥው ቡድን ለሚደርገው ግፍና ጭቆና አሜሪካ እውቅና ስትሰጥስ ?
እነደሃያል አገር ሲሆንሲሆን የነጻነት ትግል ላይ ያሉ ህዝቦችን ማገዝ ሲገባ ፣ ማገዝ ካልተቻለም ደሞ ቁስላቸው ላይ ሚጥሚጣ ባለመጨመር ዝም ማለት አይቻልም?የአለምን ሰላም ካለነጻነት ማሰብ አንደማይቻል የተቀመጡበት የአባቶችዎም ዙፋን አንደሚያሳይዎት አውቃለሁ ታዲያ የህዝቦችን የነጻነት ትግል ማጣጣል ለምን ??
እርስዎም ሆኑ ሸርማንየአሜሪካንን ጥቅም አንደምታስቀድሙ እናውቃለን፡፡ መረሳት የሌለበት ቁም ነገር ግን ህዝባዊ ወዳጅነትን አንጂ አምባገነን አገዛዙንበመተማመን የሚገኘው ጥቅም ዘላቂ አለመሆኑ ነው፡። ከአገዛዞች ጋር የሚደረገው ቁማር አሜሪካን ቆምኩለት የምትለውን የሞራል ልእልናእና እሴት የሚመጥን አይመስለኝም፡፡ ቢያንስ በአገር ደረጃ ጥቅም ህሊናን ገርስሶ የፓለቲካ ትርፍ ሰው መሆንን ጨርሶ መደምሰስ የለበትም፡፡ትልቅነት የአለምን ሰላም መጠበቅ ከሚወሰድ ሃላፌነት ቀርቶ ሌላውን ለመዋጥ ለሚከፈት አፍ ከተለካ ህገ አራዊት የአለም ትልቁመተዳደሪያ ይሆናል፡፡
ፕሬዘዳንት ኦባማ-ለዴሞክራሲያዊ ስርአት አንጂ ለአምባገነንነት ጥሩ ፊት አንደማይኖርዎት እረዳለሁ፡፡ በአሁኑ መልእክት ግራ የተጋባሁትም ከዚህ የተነሳነው፡፡ አምባገነን የሚያስበው በአይኑ ነው እንደሚባለው የኢትዮጵያ አገዛዝ በአሁኑ ሰአት እውነት ቢነገረውም እንደማይሰማ ይታወቃል፡፡የወይዘሮዌንዲ ሸርማን መግለጫ ሊወድቅ ሳምንታት ሲቀሩት የግብጽ አገዛዝ “strong and stable government” ….. “ጠንካራ እና የተረጋጋ መንግስት” ከሚለው በወቅቱ የአሜሪካንየውጪ ጉዳይ ሚኒስተር ከነበሩት ወ/ሮ ሂላሪ ክሊንተን መግለጫ ጋር ተመሳሳይ ሆኖብኛል፡፡ ይህ አይነት ከእውነታው ያፈነገጠ አገላለጽለሁለቱም አገሮች አንደማይጠቅም ይገባዎታልም ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ፕሬዘዳንት ኦባማ- የኢትዬጵያ ታላቅነት ይመለሳል፡፡ በእርግጥም በነጻነትና በዴሞክራሲ ምርጫ ወደስልጣን የሚወጣ ተርሙን ሲጨርስ ለቀጣዬ በሰላምየሚያስረክብ መሪ ይኖራታል፡፡ ህዝቦቿ በእርቅ ይተቃቀፋሉ፡፡ ጨቋኝም ተጨቋኝም ነጻ ይወጣሉ ፡፡ ኢትዬጵያ ጦር በመስበቅ ሳይሆንፍቅርን በተግባር በመስበክ ለአካባቢዋም ለአለምም አስተዋእጾ የምታበረክትበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም ፡፡ ለዚህ ታላቅ ሽግግር እርሶምአንደመሪ አገርዎም እነደሃያል አገር ከኢትዮጲያ ጎን ብትቆሙ የሁለቱ አገሮች ጥቅም በአለት ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡
ቀሪው የስራ ዘመንዎምይህን የአሜሪካን የሞራል ልእልና በተግባር የሚያሳዩበት አንዲሆን እመኝልዎታለሁ፡፡ ፈጣሪ ኢትዮጵያንም አሜሪካንንም ይባርክ፡፡
የሸዋስ አሰፋ! ከቅሊንጦኢትዮጵያ
http://ecadforum.com/Amharic/archives/15055/

Wednesday 13 May 2015

ኢትዮጵያ፡ የምንወድሽ ሀገራችን ደግመሽ አልቅሽ! (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
የኢትዮጵያውያን/ት ህይወት ያሳስበናል!
እ.ኤ.አ በ2005 ልክ የዛሬ 10 ዓመት በያዝነው ወር ገደማ አሁን በህይወት የሌለው እና እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አድራጊ ፈጣሪ አምባገነን መሪ የነበረው መለስ ዜናዊ በዚያን ዓመት ተካሂዶ የነበረውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ ተከስቶ በነበረው ሁከት የደህንነት እና የጦር ኃይሉን በእራሱ ቁጥጥር ስር በማዋል በሰላማዊ እና ባልታጠቁ ንጹሀን ዜጎች ላይ ጭካኔ የተሞላበት እልቂት እና መከራን ያዘለ ዘመቻ አካሂዷል፡፡Cry Once Again, Our Beloved Country
እ.ኤ.አ ግንቦት 16/2005 መለስ ዜናዊ የፖሊስ፣ የደህንነት እና ወታደራዊ ኃይሉን በእራሱ ቁጥጥር ስር በማደረግ እና የአዲስ አበባ ከተማን የፖሊስ ኃይል ከፌዴራል ፖሊስ እና ከልዩ ኃይል ጋር በማቀናጀት ሁሉንም የህዝብ ስብሰባዎች ህገወጥ ናቸው በማለት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ ነበር፡፡ በቀጣዮቹ ሳምንታት የመለስ የጭፍጨፋ ኃይሎች አረመኒያዊ ጭፍጨፋ በማካሄድ 193 ሰላማዊ ንጹሀን ዜጎችን ግንባራቸውን እና ደረታቸውን በጥይት እያነጣጠሩ በመምታት የገደሉ ሲሆን ሌሎች 800 የሚሆኑ ወገኖቻችንን ደግሞ በጽኑ እንዲቆስሉ አድርገዋል፡፡ ምንም ዓይነት ትጥቅ ያልነበራቸው ሰላማዊ አመጸኞች ያንን ሸፍጥ እና ተንኮል የተሞላበትን የተጭበረበረ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ በመቃወማቸው እና መብታቸውን ለመጠቀም በመምረጣቸው ብቻ በየመንገዶች እና በየቤቶቻቸው እንደ አውሬ እየታደኑ ያለምንም ርህራሄ በጥይት እየተደበደቡ በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲገደሉ ተደርገዋል፡፡ እነዚያ ጀግኖች ሰላማዊ አማጺ ወገኖቻችን በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እንዲሰፍን በጽናት ታግለው ውድ ህይወታቸውን በመገበር ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ማበብ ሲሉ መስዋዕት ሆነዋል፡፡
ያ የአረመኔዎች እና የፈሪዎች አሰቃቂ ዕልቂት ላለፉት አስርት ዓመታት በየዕለቱ የእራስ ምታት፣ የልብ ቁስል፣ የሆድ ቁርጠት እና የደረት ውጋት ሆኖብኝ ቆይቷል፡፡ ይህንንም ከግንዛቤ በማስገባት ስለዚሁ ጉዳይ አንዲትምሳምንትሳታልፈኝ በማዘጋጀው ትችቴ ለበርካታ ዓመታት ሳስተምር እና ስሰብክ ቆይቻለሁ፡፡ እ.ኤ.አ በ2005 የተካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ ተከስቶ በነበረው ውዝግብ የመለስን እልቂት በመቃወም በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን የሰብአዊ መብት ትግል ተቀላቅዬ በመታገል ላይ እገኛለሁ፡፡ የመለስ እልቂት ሰለባዎች የፍትህ ያለህ እያሉ በመጮህ ላይ ይገኛሉ፡፡ እኔ የእነርሱ ድምጽ ነኝ፡፡
ያ በሰላማዊ እና ንጹሀን ዜጎች ላይ በመለስ ትዕዛዝ ተካሂዶ የነበረው ሰይጣናዊ አሰቃቂ ዕልቂት የተፈጸመበት አስር ዓመት ከመሙላቱ ከአንድ ወር በፊት እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2015 እራሱን የኢራቅ እና የሊባኖስ እስላማዊ መንግስት (ኢሊእመ)/Islamic State of Iraq and the Levant (ISIL) (እንደዚሁም ደግሞ የኢራቅ እና የሶርያ እስላማዊ መንግስት (ኢሶእመ)/Islamic State of Iraq and Syria (ISIS) እያለ የሚጠራው አሸባሪ ቡድን በሊቢያ 30ኢትዮጵያውያንወገኖቻችንን አሳዛኝ እና አስደንጋጭ በሆነ መልኩ ያረደ መሆኑን በቪዲዮ ምስል ተመልክቻለሁ፡፡ (በዚህ በቀሪው ትችቴ ይህንን እየተስፋፋ የመጣውን ነቀርሳ/ካንሰር አሸባሪ ድርጅት “አሸባሪ ቡድን/ድርጅት/the terrorist group/organization“ እያልኩ እጠራዋለሁ ምክንያቱም በዓለም ላይ ከሚገኙ ታላላቅ ኃይማኖቶች መካከል አንዱ በሆነው የእስልምና እምነት ኃይማኖት ስም እየማለ እና እየተገዘተ ሆኖም ግን በተግባራዊ እንቅስቃሴው ግን የኃይማኖቱን ቅዱስነት ያዋረደ፣ የማያስብ፣ ኋላቀር፣ ደም የጠማው፣ ጨካኝ እና ስብዕና የሌለው አሸባሪ ቡድን ከእስላም ሃይማኖት ጋር አየገናኝም፡፡)
ይኸ በሊቢያ የሚገኘው ጨካኝ አሸባሪ ቡድን የወጣት ኢትዮጵያውያንን አንገት በማረጃ ቤት ውስጥ እንደሚታረድ የበግ ጠቦት እየቀነጠሰ አርዶ ጥሏል ምክንያቱም እነዚህ የኢትዮጵያ ወጣቶች ከኢትዮጵያ ጠላቶች በተለዬ መልኩ የክርስትና ኃይማኖት እምነት ተከታዮች የሆኑ እና እምነታቸውን ለመቀየር እምቢ አሻፈረኝ በማለት በእምነታቸው የጸኑ ዜጎች ናቸው፡፡ እነዚህ 30 ወጣት ኢትዮጵያውያን ለክርስትና ኃይማኖት እምነት ሲባል መስዋዕትነትን የተቀበሉ ብቻ አይደሉም፣ ሆኖም ግን ከዚህም በተጨማሪ ለሰው ልጆች እምነቶች እና አስተሳሰቦች ሲሉ ጭምር እንጅ፡፡ እነዚህ ወጣቶች ትክክለኛውን እምነታቸውን በመከተል የአምላክ የበግ ጠቦት በመሆን መስዋዕትነትን ተቀብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ወጣት ወንዶች እና በሌሎችም ከግብጽ፣ ከዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ፣ ከእንግሊዝ፣ ከጃፓን፣ ከኢራቅ እና ከሶርያ የመጡ ወጣቶችን ጨምሮ ሰለባ ያደረገው ይኸ ምንም ዓይነት ርህራሄ የሌው አረመኔ እና ጨካኝ አሸባሪ ቡድን ከፊል ኢራቅን፣ ሶርያን፣ ሊቢያን እና ናይጀሪያን ተቆጣጥሯል፡፡ እ.ኤ.አ ሰኔ 2014 ያ አሸባሪ ቡድን በነብዩ መሀመድ ቦታ አቡ ባከር አል ባግዳድን መሪ በማድረግ እራሱን ዓለም አቀፍ የእስልምና ኃይማኖት መንግስት አድርጎ አውጇል፡፡
ያ አሸባሪ ድርጅት የተለያዩ ሰብዕናየለሽ ቡድኖችን፣ ጀብድ ፈላጊዎችን እና ሌሎችን ከመካከለኛው ምስራቅ እና ከአውሮፓ ደስተኛ ያልሆኑትን እና መብታቸውን የተነፈጉትን  ሰብስቦች እየሳበ እንደሚጠቀምባቸው አምናለሁ፡፡ የዚህ ድርጅት አባላት በዓለም ላይ ጉዳት ለማድረስ በስሜታዊነት የተሞሉ ናቸው፡፡ የሮምን ወታደር (በተለምዶ በሮም ጳጳስ የተላኩ ተዋጊዎች ወይም ደግሞ የበለጠ በሚመሳሰል መልኩ እምነት የሌላቸው የምዕራብ ወታደሮች በዳቢቅ እና በሶርያ በሚገናኙበት ጊዜ የዓለምን ፍጻሜ የመጀመሪያ ምዕራፍ ይጠብቃሉ፡፡ እርግጠኛ ለመሆን ለዚያ አሸባሪ ቡድን እምነት የሌላቸውን እና ለአሸባሪ ድርጅቶች ርዕዮት ዓለም ድጋፍ የማያደርጉትን የሻአ ሙስሊሞችን እና ሌሎችን ሙስሊሞች እንዲሁም ማንኛውንም የሙስሊም መንግስት ያካትታል፡፡ ያ አሸባሪ ቡድን በአሁኑ ጊዜ በኢራቅ፣ በሶርያ፣ በሊቢያ እና በናይጀሪያ ተቆጥረው ለማያውቁ እልቂቶች ቀጥታ ተጠያቂ ነው፡፡ በዳቢቅ አሸባሪዎቹ እምነት የላቸውም ብለው የሚያስቧቸውን ማለትም ክርስቲያኖችን፣ ሙስሊሞችን እና ሌሎችን በማሸነፍ የእስልምና ግዛታቸውን በዓለም ላይ ሁሉ ለማስፋፋት እና ኃያል ሆነው ለመውጣት ይፈልጋሉ፡፡ ኋላቀርና  ኢ-ሰባዊ ድርጊትን ማራመድ የዚያ አሸባሪ ቡድን መለያ ፍልስናው ነው፡፡ ፍልስናው የእነርሱን ዓይነት የሙስሊም እምነት የማያራምደውን የእስልምና እምነት ተከታይ፣ ምንም ዓይነት እምነት የሌለውን ወይም ደግሞ ይዞት የቆየውን እምነቱን ያቆመውን ሰው ለመግደል እንደምክንያት የሚጠቀሙበት ነው፡፡ የእነዚህ የተንሸዋረረ ፍልስፍና የያዙት አሸባሪዎች ዓለምን ለማጽዳት የሚቻለው እነርሱ አማኞች አይደሉም ብለው የሚያስቧቸውን ሰዎች መግደል ነው፡፡
ባለፈው ሳምንት በአሸባሪ ቡድኑ ተቀርጾ በተለቀቀው የቪዲዮ ምስል የወጣት ኢትዮጵያውያን ወንዶችን ጭንቅላት ለመቅላት/አንገታቸውን ለመቁረጥ እጆቻቸውን ይዘው በረሀውን በማቋረጥ ወደ ባህሩ ዳርቻ ሲወስዷቸው ነበር፡፡ ጥቂቶቹ ወጥ የሆነ ብርቱካናማ ልብስ ለብሰው ነበር፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ጥቁር ልብስ ነበር የለበሱት፡፡ አሸባሪዎቹ የወጣት ኢትዮጵያውያንን ጭንቅላት ለመቅላት እንደ ምክንያት ማስረጃ አድርገው የሚያቀርቡት ጠላታቸው የሆነቸው የእትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እምነት የሆነውን የክርስትና ኃይማኖት እምነት ተከታይ የመሆናቸው ጉዳይ ብቻ ነው፡፡
ይህ በሊቢያ እና እንደእርሱ ባሉት በሌሎች ሀገሮች የሚገኙት የደንቆሮ ስብስብ ወሮበላ የአሸባሪ ቡድን አባላት ከስቃይ እና መከራ እንዲሁም ከነብዩ ትምህርት በመሸሽ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩትን የመጀመሪያዎችን የእስልምና እምነት ተከታዮች በኢትዮጵያውን ህዝቦች ተደርጎላቸው የነበረውን የአቀባበል መስተንግዶ ሙልጭ አድርጎ ረስቶታል፡፡ በቅርቡ አንድ ግለሰብ በሰጠው ቃለ መጠይቅ መሰረት በኢራቅ ቃለ መጠይቅ የተደረገላቸው እና ለዕኩይ ምግባራቸው ስኬታማነት በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት የአሸባሪ ቡድኑ አባላት የትምህርት ደረጃቸው ከአንደኛ ደረጃ ያልዘለለ መሆኑን ግልጽ አድርገዋል፡፡ እስላም ምንድን ነው ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ እንዲህ የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፣ “ሕይወቴ ነው፡፡’ ስለቁራን ወይም ደግሞ ስለቁራን ባህላዊ ስብስቦች ወይም ስለድሮው ነብይ ኦማር እና ኦትማን ምንም የሚያውቁት ነገር የላቸውም፣ ሆኖም ግን ስለእስልምና ከአልቃይዳ እና ከአይሲስ ፕሮፓጋንዳ፣ እንዲሁም ሙስሊም ያልጠራውን እምነት ቀደም ብሎ ያልጠራውን እምነት ካላስተማረ እርሱም የእምነቱ ተከታዮች እንዳልሆኑት ሰዎች ሁሉ መወገድ እንዳለባቸው እና ዒላማ ውስጥ እንደሚወድቁ አሳምረው ያውቃሉ፡፡“ እነዚህ የአሸባሪ ቡድን አባላት እንዲህ በማለት ተናግረዋል፣ “ሳዳም ሁሴን ከወደቀ በኋላ በገሀነም ዓይነት የማያቋርጥ የሽምቅ ውጊያ ያደጉ፣ ቤተሰቦቻቸው የሞቱባቸው እና የተበታተኑባቸው እንዲሁም ከቤቶቻቸው መውጣት የማይችሉ ወይም ደግሞ እስከ ወሩ መጨረሻ ምንም ዓይነት መጠለያ የሌላቸው መሆናቸው ታውቋል፡፡“
ሌሎች የአሸባሪ ቡድን አባላትም ከዚህ የተለዬ የተሻለ ስብዕና የላቸውም፡፡ በአብዛኛው በህይወታቸው በሽግግር ላይ ያሉ ወጣቶች ማለትም ተማሪዎች፣ ስደተኞች፣ ስራ ለመስራት የማይፈልጉ አውደልዳዮች፣ ቤተሰቦቻቸውን የተው ወይም ደግሞ ለመተው የተዘጋጁ እና አንድ ዓይነት ጥቅም ሊያስገኝላቸው የሚችል ሌላ ዓይነት የጓደኝነት ቤተሰብ ለመመስረት ሲሉ ጥረት የሚያደርጉ ናቸው፡፡ አብዛኞቹ የተለመደው የኃይማኖት ትምህርት እውቀት የላቸውም፣ እናም ጥብቅ በሆነ እና በጠባብ የማህበራዊ ፍልስፍና እምነት የታሰሩ ናቸው፣ ሆኖም ግን እነዚህ የአሸባሪ ቡድን አባላት ዓለምን ሊገምድ በሚችል የኃይማኖት ተልዕኮ ስሜት የተሞሉ ናቸው፡፡
እነዚህ በድንቁርና ተቀፍድደው የተያዙት አሸባሪዎች እና ከነባራዊ ሁኔታው ጋር መራመድ የማይችሉ ጉዶች ኢትዮጵያ ለነብዩ መሐመድ እምነት ተከታዮች የመጀመሪያው የእስልምና ኃይማኖት እምነት ስደተኞች ተቀባይ ገነት ስለመሆኗ ምንም ዓይነት ፍንጭ የላቸውም፡፡ ነብዩ መሐመድ በዚያ የመከራ ስደት ወቅት ለተከታዮቻቸው እንዲህ ብለው ተናግረው ነበር፣ “መካን መልቀቅ እና በዚያን ጊዜ በክርስቲያን ንጉስ ትተዳደር በነበረች እና ንጉሷም ፈሪሀ እግዚአብሔር ያደረበት እና ፍትህን የሚከተል ስለሆነ በአቢሲኒያ ሀገር (ኢትዮጵያ) በጥገኝነት መቆየት አለባችሁ፡፡“ የአክሱሙ ንጉስ እና የሐበሻ ህዝብ (ኢትዮጵያውያን) ከክርስቶስ ልደት በኋላ  በ615 ዓ.ም መጀመሪያ አካባቢ በስቃይ እና በመከራ ሸሽተው የመጡትን ሙስሊሞች ተቀብለው በመልካም ሁኔታ አስተናገዱ፡፡ እናም ታላቅ የሆነ መስተንግዶ አደረጉላቸው፣ እንዲሁም አባራሪዎቻቸው እና ጠላቶቻቸው ተመልሰው ወደ ሀገራቸው እንዲላኩላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ተንከባክበው እና ደግፈው አስተማማኝ መጠለያ በመስጠት ሊሰነዘርባቸው ከሚችለው አስከፊ አደጋ አድነዋቸዋል፡፡  እነዚህ ወሮበላ የአሸባሪ ቡድን አባላት ነብዩ መሐመድ የሀበሻን (አቢሲኒያ) ህዝብ ማመስገናቸውን እና እንዲህ የሚለውን ንግግራቸውን ፍጹም በሆነ መልኩ ረስተውታል፣ “እርምጃ እስካልወሰዱባችሁ ድረስ ሐበሻዎችን አትንኳቸው!“ ከዚህም በተጨማሪ ነብዩ መሐመድ እንዲህ በማለት አስተምረዋል፣ “አምላክ ለሌሎች ምህረትን ለማያደርጉ ምህረትን አይሰጥም፡፡“
በሊቢያ አሸባሪዎች አንገታቸውን የተቀሉት ኢትዮጵያውያን በማንም ዘንድ ጥቃትን አላደረሱም ነበር፡፡ እነዚህ ወጣቶች ሁሉም ድሆች እና ምንም ዓይነት ተስፋ የሌላቸው ሊቢያን እንደመሸጋገሪያ አድርገው መድረሻቸውን ወደ አውሮፓ ሀገሮች ያደረጉ ስደተኞች ነበሩ፡፡ ምህረትን፣ መጠለያን ማግኘት እና አንገታቸው እንዳይቀላ ይፈልጉ ነበር፡፡ እነዚህ እምነቱን ያዋረዱ አሸባሪዎች የኢትዮጵያውያንን አንገት መቅላት ሲጀምሩ ነብዩ መሐመድ ሲያስተምሩ የነበሩትን ትምህርት ወደ ጎን አሽቀንጥረው ጣሉት፡፡ ለእነዚህ የሽብር እና የነውጥ ተዋንያን አላህ ምህረቱን አይሰጣቸውም! እነዚህን ምስኪን እና ጨዋ ኢትዮጵያውያን የአላህ ዓይን ይጎበኛቸዋል! አላህ አክብር ሞት ለአሸባሪዎች እና ለግፈኞች!
መለስ እና እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ እ.ኤ.አ በ2005 የተደረገውን ሀገር አቀፍ ምደርጫ ውዝግብ ተከትሎ በተፈጠረው ሁከት ሰላማዊዎቹን ኢትዮጵያውያን አንገታቸውን አልቀሉም፣ ሆኖም ግን በአልሞ ተኳሾች እያነጣጠሩ ጭንቅላቶቻቸውን በጥይት ነበር የደበደቡ እንጅ አንገት አልቀሉም ነበር፡፡ በአንድ በቪዲዮ በተቀረጸ ቃለ መጠይቅ መለስ በዚያን ጊዜ ለፈጸመው እልቂት ምክንያት ለመስጠት እስከ 194 ሰዎች ላለቁበት እኩይ ምግባር እንዲህ የሚል ማሳመኛ ለመስጠት ሞክሮ ነበር፣ “በኢትዮጵያ ህገመንግስታዊ ትዕዛዝን ለመፈጸም ህገመንግስታዊ ተግዳሮት ነበር፣ እናም ያ ተግዳሮት አጋጥሞን ነበር፡፡“ በሌላ አባባል ሰላማዊ ሰዎች እልቂት እንዲፈጸምባቸው አድርጓል ምክንያቱም የእርሱን ህግ ተገዳድረዋልና፡፡ አምባገነኑ መለስ እንዲህ ብሎ ነበር፣ “ያ ዕልቂት የዓለም መሪዎችን አስተያየት በመቀየር ወደ እርሱ የሚያደላ መሆኑን ተጠራጥሮ ነበር፡፡ ሆኖም ግን በግልጽ የኢትዮጵያን ገጽታ ጥላሸት ቀብቶ ነው የሄደው፡፡“
በእራሱ በመለስ ዜናዊ የተሾሙት እና የአጣሪ ኮሚሽኑ ሊቀመንበር የነበሩት የዳኛ ፍሬህይወት ዘገባ ፍጹም በሆነ መልኩ ሰላማዊ አመጸኞችን ነጻ በማድረግ አጠቃላይ ኃላፊነቱን እንዲህ በማለት በመለስ አገዛዝ ላይ ደፍድፎታል፡
የጦር መሳሪያ ጠብመንጃ ያነገበ ወይም ደግሞ የእጅ ቦምብ የታጠቀ አንድም ሰው አልነበረም፣ (የመንግስት መገናኛ ብዙሀን እንደገለጹት ጥቂት ሰላማዊ አመጸኞች ጠብመንጃ እና ቦምብ ታጥቀው ነበር፡፡) የአጣሪ ኮሚሽኑ አባላት በመንግስት ኃይሎች የተተኮሱት ጥይቶች ሰላማዊ አመጸኞችን ለመበተን አልነበረም፡፡ ሆኖም ግን የሰላማዊሰልፈኞችንጭንቅላት እና ደረት በአልሞ ተኳሾች እያነጣጠሩ በመምታት ለመግደል የተደረገ ድርጊት ነበር፡፡ (አጽንኦ ተጨምሯል፡፡)
እ.ኤ.አ በ2005 የተካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ እና ሁከት በሰላማዊ ዜጎች ላይ እልቂት የፈጸሙት ወሮበላ ነብሰገዳይ ፖሊሶች እና የጸጥታ ኃይሎች ማንነት በትክክል ታውቆ እና ተመዝግቦ ይገኛል፡፡ “በኢትዮጵያ የውስጥ የደህንነት ጥበቃን ማዘመን” በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ዘገባ ላይ የጸረ ሽብር ባለሙያ የሆኑት እና የእግሊዝ ወታደራዊ ኃይል አባል የሆኑት ኮሎኔል ሚካኤል ደዋር የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ወርቅነህ ገበየሁ እንዲህ በማለት የገለጹላቸውን በመጥቀስ ተናግረዋል፣ “እ.ኤ.አ በ2005 በተካሄደው አመጽ 237 ፖሊስ አባላትን ከመደበኛ ስራቸው አባረዋል፡፡“ ምንም ዓይነት መሳሪያ ባልታጠቁ በኢትዮጵያ ንጹሀን ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ያሳስበናል! እ.ኤ.አ በ2005 የተካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ ተፈጥሮ በነበረው ውዝግብ በርካታ ሰላማዊ ወገኖቻችንን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በጥይት እየደበደቡ እልቂት ሲፈጥሩ የነበሩት ወሮበላ ቅጥር ነብሰገዳዮች በአሁኑ ጊዜ ደረታቸውን ነፍተው በዋና ዋና መንገዶች ላይ ሲንገዳወሉ ይውላሉ፡፡ ያንን የመሰለ ዘግናኝ እልቂት የፈጸሙት ወይም ደግሞ እልቂቱ እንዲፈጸም ትዕዛዝ የሰጡት አንዳቸውም ወንጀለኞች እስከ አሁን ድረስ ለፍትህ አካል አልቀረቡም፡፡
በዚህ በያዝነው ሳምንት ከአንድ ዓመት በፊት እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው የወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ከአዲስ አበባ በስተምዕራብ በኩል በ80 ማይሎች ርቀት ላይ በምትገኘው የአምቦ ከተማ ቢያንስ በ47 የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እና በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ላይ እልቂት ፈጽሟል፡፡ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አገዛዝ ይህንን አሰቃቂ እልቂት ሙልጭ አድርጎ በመካድ ዓይኑን በጨው በመታጠብ “ጥቂት ጸረ ሰላም ኃይሎች የለኮሱት እና ያቀነባበሩት አመጽ ነው” ብሎታል፡፡ በዚያን ጊዜ እንዲህ በማለት ተቃውሞዬን አሰምቸ ነበር፣ “በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ አዝኛለሁ፡፡ እነዚህ እምቦቃቅላ ሰላማዊ ወጣት ተማሪዎች በጥይት እየተደበደቡ በእንደዚህ ያለ አሰቃቂ ሁኔታ እልቂት የተፈጸመባቸው በመሆኑ በጣም አዝኛለሁ፡፡ በእነዚህ ለኢትዮጵያ ባለብሩህ ተስፋ ባለለቤቶች ላይ በተፈጸመው እልቂት ላይ እጅግ በጣም አዝናለሁ፡፡ ለእነዚህ የእኩይ ምግባር ሰለባ ለሆኑት ወጣቶች ቤተሰቦች እና ጓደኞቻቸው ሁሉ የማይሳነው አምላክ መጽናናቱን እንዲሰጣቸው እመኛለሁ፡፡“  የኢትዮጵያ ወጣቶች ህይወት ያሳስበናል!
በአምቦ ከተማ በንጹሀን ወገኖቻችን ላይ በጠራራ ጸሐይ ጥይት ያርከፈከፉት እነዚህ አረመኔ ቅጥር ነብሰ ገዳዮች በአሁኑ ጊዜ ያለምንም ተጠያቂነት በዋና ዋና መንገዶች ላይ ደረቶቻቸውን ገልብጠው በነጻነት ከወዲያ ወዲህ እያሉ ሲንገዳወሉ ይውላሉ፡፡ ይህንን ሰይጣናዊ የእልቂት ምግባር የፈጸሙት እና እልቂቱም እንዲፈጸም ትዕዛዝ የሰጡት ወሮበላ ባለስልጣኖች ለሕግ ሳይቀርቡ ያለምንም ተጠያቂነት እጆቻቸው በሰው ልጆች ደም ተጨማልቀው ይገኛሉ፡፡
እ.ኤ.አ በ2013 በሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ሰራተኞች እና ስደተኞች ላይ የሽብር እና የእልቂት ዘመቻ ተከፈተባቸው፡፡ የሳውዲ ፖሊስ፣ የደህንነት ኃይል ባለስልጣኖች፣ ዱርዬዎች እና ወሮበሎች ለአንድ ሙሉ ቀን ያህል በየመንገዶች ኢትዮጵያውያንን እያደኑ እና እየያዙ ሲደበድቡ፣ ሲያሰቃዩ እና ሲገድሉ ነበር፡፡ በዩቱቤ ቪዲዮ የተለቀቀው ምስል እንደሚያሳየው የሳውዲ አረቢያ ፖሊስ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ ሲፈጽም የነበረው ዘግናኝ ድርጊት እጅግ በጣም አስደንጋጭ፣ ለህሊናም የሚዘገንን እንዲሁም ምንም ዓይነት ማብራሪያ የማያስፈልገው የፈሪዎች እኩይ ምግባር ነበር፡፡ እንደዚህም ሆኖ ጥቂት የኢትዮጵያ ዜጎች በመንፈሰ ጠንካራነት በጽናት በመቆም የኢትዮጵያን ባንዲራ በራሳቸው ላይ ጠምጥመው እስከመጨረሻው በመታገል በሳውዲ አረቢያ ፖሊሶች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ የጥንት የትውልድ ዘሮቻቸውም እንደዚሁ በኩራት የተወጠሩ እና ለነጻነታቸው ቀናኢ የሆኑ ጀግኖች ነበሩ፡፡!
የወባ ትንኝ ተመራማሪው እና በብርህን ፍጥነት ከጤና ጥበቃ ሚኒስትርነት ወደ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት የተተኮሰው ቴዎድሮስ አድኃኖም በዚያን ጊዜ እንዲህ የሚል ንግግር አድርጎ ነበር፣ “የወገኖቻችን መጋዝ እና መሞት እጅግ በጣም አሳስቦኛል፡፡“ አድኃኖም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ለሳውዲ አረቢያው አምባሳደር እንዲህ የሚል የተማጽዕኖ ጥሪ አስተላልፎ ነበር፣ ኢትዮጵያ የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣኖች ህገወጥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችንወደ ሀገርለመመለስ እያደረገችያለችውን የማጋዝ እቅስቃሴ መሰረት በማድረግ ላስተላለፈቻቸው ውሳኔዎችየተሰማትን አድናቆት ትገልጻለች፡፡ በዚህ አጋጣሚ በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመውን ግድያ እና በዜጎቻቸው ላይ እየተተገበረ ያለውን ተገቢ ያልሆነ አያያዝ እናወግዛለን፡፡“ (አጽንኦ ተጨምሯል፡፡)
ለአድኃኖም እና ለእርሱ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ቡድን ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረቢያ ወሮበሎች ስለሚደርስባቸው የስብዕና እጦት፣ የሰብአዊ መብት ረገጣ እና ግድያ ጉዳያቸው አይደለም፡፡ ይኸ ጉዳይ ለእነርሱ ምንም ዓይነት የሚያናድዳቸው ነገር አይደለም፡፡ በዚያን ጊዜ “የሰው የዝውውር መጨናነቅ የታየበት ዋና ጊዜ” በሚል ርዕስ እጅግ በጣም በመናደድ ጽሑፍ አውጥቸ ነበር፡፡ የቤት ስራዎቻቸውን ሳይሰሩ ወደ ክፍል የሚመጡ ተማሪዎች እጅግ በጣም ያናድዱኛል፡፡ ደሜን እንዲፈላ ያደርጉታል፡፡ የሳውዲን ፖሊስ በሰው ልጆች ላይ የሚያደርገውን የሰብአዊ መብት ረገጣ፣ ኃላቀርነት እና አረመኔነት በተመለከትኩበት ጊዜ ግን እንደ እሳት ተቀጣጥዬ ነበር፡፡ የሳውዲ ወሮበሎች እና ዱርየዎች ሲያከናውኗቸው በነበሩት ድርጊቶች ላይ ከብስጭት ብዛት ከቁጥጥር ውጭ ሆኘ ነበር፡፡ የሳውዲ አገዛዝ በኢትዮጵያውያን ስደተኛ ወገኖቻችን ላይ ሲፈጽም የነበረው መጠነሰፊ ወንጀል እና የሰብአዊ መብት ረገጣ ላይ እጅግ በጣም ደንግጨ እና ተበሳጭቸ ነበር፡፡ በሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው የሰብአዊ መብት ረገጣ አድሃኖምን ብዙም ያላሳሰበው እና ያላበሳጨው መሆኑ በንዴት ላይ ንዴት ተጨምሮብኝ የበለጠ እንድበሳጭ አድርጎኛል፡፡
እ.ኤ.አ ከ2013 ጀምሮ ስለኢትዮጵያውያን ጉዳይ ከመካከለኛው ምስራቅ እና ከደቡብ አፍሪካ የሚወጡ ዜናዎች አሳዛኝ እና ተመሳሳይነት ያላቸው ናቸው፡፡ (በደቡብ አፍሪካ ወሮበሎች እና ዘራፊዎች በኢትዮጵያውያን እና በሌሎች አፍሪካውያን ወገኖቻችን ዘንድ እየፈጸሙ ያሉትን ህገወጥ ወንጀል ወደፊት የማቀርበው ይሆናል፡፡) አሁን በቅርቡ ከሳምንት ባልበለጠ ጊዜ በመካከለኛው ምስራቅ አሰሪዋ በኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ ላይ የተፈጸመውን ህገወጥ ድርጊት በመቃወም እራሷን ያጠፋችውን ወይም ደግሞ ሌላ እራስን የሚያሰቃይ ድርጊት ወይም ክብርን የሚነካ ድርጊት የፈጸመችውን ኢትዮጵያዊት ስንመለከት እንደ ኢትዮጵያዊነታችን የሚሰማን መንፈስን የሚሰብር ድርጊት አለ፡፡ ከጥቂት ቀናት በፊት የ23 ዓመት እድሜ ያላት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ በቤይሩት ሊባኖስ እራሷን ሰቅላ ተገኝታለች፡፡ በመካከለኛው ምስራቅ በንጹሀን ኢትዮጵያውያት የቤት ሰራተኛ ወገኖቻችን ህይወትላይየሚደረገው አስፈሪ እናአስደንጋጭ ሁኔታ ያሳስበናል!
በአሁኑ ጊዜ በሳውዲ አረቢያ እና በሌሎች የመካከለኛው ምስራቅ ሀገሮች በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ ኢሰብአዊነት ድርጊት እየፈጸሙ ያለምንም ተጠያቂነት ደረታቸውን ገልብጠው በዋና ዋና መንገዶች ላይ ሲንገዳወሉ ይታያሉ፡፡ በዚህ ሁሉ የሰብአዊ መብት ረገጣ ማለትም ድብደባ፣ ማሰቃየት እና ግድያ ሲፈጽሙ በነበሩት የዕኩይ ምግባር አራማጅ የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ወደ ህግ ሳይቀርቡ እና ምንም ዓይነት ተጠያቂነት ሳይኖርባቸው ነጻ ሆነው ይኖራሉ፡፡
እ.ኤ.አ ጥቅምት 2007 መለስ ዜናዊ እና የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በኦጋዴን የሽምቅ ውጊያ ሲያካሂዱ በነበሩት ዜጎች ላይ መጠነሰፊ የሆነ ጥቃት በመሰንዘር ወዲያውኑ ብዙም ሳይቆይ የጥቃት አድማሱን በማስፋት በሲቪሉ ህዝብ ላይ የጅምላ ጥቃት ፕሮግራም ተግባራዊ እንዲሆን ተደረገ፡፡ የመለስ ተዋጊ ጦር የኦጋዴንን መንደሮች በሙሉ አወደመ፣ የአስገድዶ መድፈር ተግባራትን ፈጸመ፣ ግድያ እና አጠቃላይ ዘረፋዎችን ፈጸመ፡፡ ህዝቡን ለማስፈራራት እና ለማሸማቀቅ በሚል እኩይ ሀሳብ ዜጎችን በማነቅ እና አንገታቸውን በመቅላት በአደባባይ እንዲጣሉ ተደረጉ፡፡ ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅት ለዩኤስ አሜሪካ የአፍሪካ የውጭ ጉዳዮች እና ለዓለም ጤና ጥበቃ ንኡስ ኮሚቴ የሚከተለውን ተናግሮ ነበር፣ “ኦጋዴን ዳርፉር አይደለችም፡፡ ሆኖም ግን በኦጋዴን ያለው ሁኔታ አስደንጋጭ የሆነ ተመሳሳይ የሆነ አስፈሪ ነገርን ያመላክታል፡፡“ በኦጋዴን ያሉወገኖቻችን ህይወትም ያሳስበናል፡፡!  
በምስራቅ ኢትዮጵያ በኦጋዴን አካባቢ በሰው ልጆች ላይ እልቂትን፣ የዘር ማጥፋት ወንጀልን የፈጸሙ እና ወንጀሉ እንዲፈጸምም ትዕዛዙን የሰጡት ኃላፊዎች ምንም ዓይነት እርምጃ ሳይወሰድባቸው እና አንዳቸውም ለህግ ሳይቀርቡ እስከ አሁንም ድረስ በነጻነት በየመንገዶች ደረቶቻቸውን ነፍተው በመንገዋለል ላይ ይገኛሉ፡፡
እ.ኤአ. ታህሳስ 2003 መለስ ዜናዊ እና የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላ ህዝቦች ላይ መጠነ ሰፊ የሆነ ጦርነት እንዲካሄድባቸው የጦር ኃይላቸውን በማዘዝ 400 የአኟክ ህዝቦች እንዲገደሉ ሲደረግ ከ1,000 በላይ የሚሆኑ ቤቶች ደግሞ እንዲወድሙ ተደርገዋል፡፡ በቀጣይነትም የመለስ አገዛዝ እንዲህ የሚል መግለጫ አውጥቶ ነበር፣ “በዚህ ጉዳይ ላይ ፈጣን የሆነ እርምጃ ባለመወሰዱ ይቅርታ እየጠየቅን ወደፊት ግን የጥቃቱ ሰለባ ከሆኑት ወገኖች ጎን በጽናት በመቆም አጥፊዎቹ ለህግ እንዲቀርቡ እናደርጋለን፡፡“ በዚያን ጊዜ አገዛዙ በአኟክ እልቂት ላይ ተዋንያን የነበሩ እና እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ተጠርጣሪዎች ተለይተው ነበር፡፡ እስከ አሁኗ ደቂቃ ድረስ ማናቸውም ቢሆኑ ለህግ አልቀረቡም፡፡ በጋምቤላ ያሉወገኖቻችን ህይወትም ያሳስበናል፡፡! በምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላ አካባቢ በሰው ልጆች ላይ እልቂትን፣ የዘር ማጥፋት ወንጀልን የፈጸሙ እና ወንጀሉ እንዲፈጸምም ትዕዛዙን የሰጡት ኃላፊዎች ምንም ዓይነት እርምጃ ሳይወሰድባቸው እና አንዳቸውም ለህግ ሳይቀርቡ እስከ አሁንም ድረስ በነጻነት በየመንገዶች ደረቶቻቸውን ገልበጠው በመንገዋለል ላይ ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ጊዜ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብን በማገልገል ላይ የሚገኝ ምንም ዓይነት ወታደር፣ ፖሊስ፣ የደህንነት ኃላፊ እና ሌላ የሲቪል ባለስልጣን በህግ ፊት እንዲቀርብ ተደርጎ የተቀጣ፣ ላጠፋው ጥፋት ተጠያቂ የሆነ ወይም ደግሞ ለፈጸማቸው ግድያዎች፣ ወንጀሎች እና የዘር ማጥፋት ወንጀሎች፣ የጦር ወንጀሎች ወይም ጦrኝነት ተጠያቂ ሆኖ አያውቅም፡፡
በኢትዮጵያውያን/ እና በኢትዮጵያዊ/ያት ስደተኛ ላይ እየተካሄደ ያለው ነጻ የሰው አደን መቆም አለበት!
የንዴት ሞት እና በኢትዮጵያውያን መሞት ላይ ያለው ንዴት፣ 
ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ምንም ዓይነት ርህራሄ በሌለው አሸባሪ ቡድን እንደ በግ የመታረዳቸው ሁኔታ በዓለም ህዝብ ዘንድ ታላቅ ቁጣን ቀስቅሷል፡፡ ጳጳስ ፍራንሲስ እንዲህ ብለዋል፣ “ሰላማዊ በሆኑ የክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ በሊቢያ በጨካኝ ሸፍጠኞች የተደረገው እልቂት በጣም አስደንጋጭ እና አሳዛኝ ነገር ነው፡፡“ በመቀጠልም እንዲህ በማለት ሀሳባቸውን ቋጭተዋል፣ “በአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምስራቅ እና በጥቂት የኤስያ ሀገሮች በዚህ ዓይነት ቀጣይነት ባለው እንደዚህ ባለ ጭካኔ በተመላበት የክርስቲያኖች መስዋዕትነት ከልብ የሆነ መንፈሳዊ ትብብር አስፈላጊ ነው፡፡“ ጳጳሱ እነዚህ አሸባሪ ቡድኖች ከሰይጣን ጎን የቆሙ ናቸው በማለት እንዲህ ብለዋል፡፡ “የእኛ የክርስቲያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ደም በእያንዳንዱ ሰው ልብ ውስጥ ገብቶ በመጮህ በደግ ነገር እና በሰይጣናዊ ድርጊት መካከል ያለውን ልዩነት ለማወቅ የሚሰማ ምስክርነት ነው፡፡“
የኦባማ አሰተዳደር በአይኤስአይኤል/ISIL እና ተባባሪዎቹ በሊቢያ በኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመውን ጭካኔነት የተሞላበት የሽብር የግድያ እልቂት ጠንካራ በሆነ መልኩ አውግዘዋል፡፡ እነዚህ አሸባሪዎች የጥቃት ሰለባዎቹ በአሸባሪዎች ላይ ባላቸው እምነት፣ ጦረኝነት፣ እደገኛነት እና ጨካኝነት ምክንያት ብቻ እነዚህን ወንዶች ገድለዋቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት እየተባለ የሚጠራው የአምባገነን ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በመጀመሪያ ይህንን አሸባሪዎች የጥቃት ሰለባዎችን አንገት እየቀሉ አሰቃቂ በሆነ መልኩ የገደሏቸውን ዜጎች ኢትዮጵያውያን ናቸው ብሎ ለመቀበል እና ዕውቅና ለመስጠት ተቃውሞውን አሰምቶ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል አቀባይ የሆነው ሬድዋን ሁሴን የእርሱ መንግስት የጥቃቱ ሰለባ የኢትዮጵያ ዜጎች መሆናቸውን ገና ማረጋገጥ ሳይችል የኢትዮጵያ መንግስት ይህንን በሰው ልጆች ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ድርጊት ያወግዛል ብሏል፡፡
አንገታቸውን እየተቀሉ የተገደሉት የጥቃቱ ሰለባዎች ኢትዮጵያውያን ናቸው የሚለውን ዘገባ ሲኤንኤን/CNN የተባለው ዓለም አቀፍ የዜና ወኪል ቢዘግብም እንኳ ለወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ጉዳዩ አይደለም፡፡ አልጃዚራ/Al Jazeera የተባለው ዓለም አቀፍ የዜና ወኪል አንገታቸውን እየተቀሉ እንዲገደሉ የተደረጉት ዜጎች ኢትዮጵያውያን ናቸው የሚል ዘገባ ቢያቀርብም ለወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ምኑም አይደለም፡፡ ሬውተርስ/Reuters፣ ኤጀንስ ፍራንስ ፕሬስ/Agence France Press ቢቢሲ/BBC፣ ቪኦኤ/VOA እንደ ኒዮርክ ታይምስ ያሉ የዜና ወኪሎች በሙሉ በአሸባሪዎች ዕኩይ ምግባር የጥቃቱ ሰለባ ለሆኑት ኢትዮጵያውያን ዕውቅና በመስጠት ሀዘናቸውን የገለጹ ሲሆን የእኛዎቹ ፈጣጣዎች ግን እውነታውን በመቀበል ዕውቅና ለመስጠት ባለመፈለግ አሻፈረኝ ብለዋል፡፡ ለመሆኑ እነዚህ ደንታቢሶች ስለምን ጉዳይ ነው ሊያሳስባቸው የሚችል? አንገታቸውን እየተቀሉ የተገደሉ የሌላ ሀገር ዜጎች መሆናቸውን በስህተት የገለጹ በመሆናቸው ምክንያት ቀደም ሲል ስለዚህ ጉዳይ መረጃው ነበራቸውን? በዓለም ላይ በየትኛውም ቦታ ቢሆን የማንም ጨዋ ሀገር መንግስት በዓለም አቀፍ የዜና ወኪሎች በተደጋጋሚ የተገለጸን እውነታ በጥሬው እንዳለ እውነት ነው ብሎ መውሰድ እና ቁጣውን እና የሚያሳስበው መሆኑን መግለጽ የለበትምን!?
እውነታው ግን፡ ለወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ምንም ዓይነት ደንታ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም፡፡ ደምበጠማቸውአሸባሪ ዘራፊዎች ስለጠፋውይህ የወጣት ኢትዮጵያውያን ዕልቂት ለወያኔ ምኑም አይደለም!!! 
የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ እነዚህ የጥቃቱ ሰለባዎች አንድ ጊዜ ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን ካረጋገጠ በኋላ የአዞ እንባ በማንባት እንዲህ የሚል መግለጫ አወጣ፣ “ጭካኔ በተሞላበት መልኩ ምንም ነገር በሌላቸው በንጹሀን ዜጎቻችን ላይ በተፈጸመው እኩይ ድርጊት ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶናል፡፡”
ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በሊቢያ አሸባሪዎች በግፍ ያለቁት የጥቃቱ ሰለባ ኢትዮጵያውያን መሆናቸው ከታወቀ በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት የሶስት ቀናትየሀዘን ቀን በማለት አውጇል፡፡ 
አድኃኖም እና የእርሱ የወረቀት አለቃው እና የኢትዮጵያ የይስሙላው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በሊቢያ ለቀሩት ኢትዮጵያውያን ወገኖች አስተማማኝ ደህንነት ሲባል ምንም ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ ሳይወስድ ለይስሙላ እንኳ ለታዕይታ ያህል ምንም ነገር ሳይደርግ ዝም በማለት አልፎታል፡፡ ምንም ዓይነት ዲፕሎማሲያዊ ተቃውሞ እንኳ አልተደረገም፡፡ አስገዳጅ በሆነው የዲፕሎማሲ አካሄድ መንገድ እንኳ ለመንቀሳቀስ አልተሞከረም፡፡ በሊቢያ ለቀሩት ኢትዮጵያውያን ደህንነት ሲባል ለተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር መጠለያ በመስጠት እርዳታ እንዲደረግላቸው እንኳ አስቸኳይ የሆነ ጥያቄ አላቀረበም፡፡ ኃይለማርያም እና አድኃኖም የእነርሱ ቃል አቀባይ ሁሉንም ንግግር እንዲናገር በመተው በቤተክርስቲያን ውስጥ እንዳሉ አይጦች ጸጥ በማለት አልፈውታል፡፡ ይኸ ጉዳይ የሚያስደንቅ አይደለም ምክንያቱም የኢትዮጵያ ስደተኞች የትም ሀገር እንዲሄዱ አይፈልጉም!
ለታሪክ ምዝገባ ያህል አድኃኖም እና የእርሱ የወረቀት አለቃው ኃይለማርያም ደሳለኝ እ.ኤ.አ ጥቅምት 2013 በአፍሪካ ህብረት የስብሰባ አዳራሽ በመገኘት የእነርሱ የምግባር ጓደኛ የሆነው ኡሁሩ ኬንያታ በዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በመከሰሱ ምክንያት ያዙኝ ልቀቁኝ በማለት ድርጅቱ ሰው ገዳይ እና ዘር አዳኝ እንደሆነ አድርገው ቡራ ከረዩ ሲሉ የነበሩትን ሁኔታ ለመግለጽ እፈልጋለሁ፡፡ በዚያ ስብሰባ ወቅት ሁሉም ሀገሮች የሮምን ስምምነት በመጠቀም ስብሰባውን ረግጠው ከድርጅቱም እንዲወጡ ለማድረግ ግንባር ቀደም የመድረክ ላይ ተዋናይ ሆነው ታይተዋል፡፡
ዛሬ ወገኖቻቸው በሊቢያ እና በመካከለኛው ምስራቅ የተለያዩ ቦታዎች እንደ አውሬ እየታደኑ ሲገደሉ እና በየቀጣሪዎቻቸው መኖሪያ ቤቶች እንደላውንድሪ ልብስ ሲሰቀሉ እና ሲሰጡ  እያዩ እና እየተመለከቱ ምላሳቸው ታሽጓል፣ አንደበታቸው ተሸብቧል፡፡ የአፍሪካ ህብረት በእነዚህ አሸባሪዎች ላይ እርምጃ  እንዲወስድ የመድረክ ላይ ትወና ያላደረጉት ወይም ደግሞ ቁጣቸውን ለመግለጽ ድፍረቱን ያጡት ለምንድን ነው? ለአድኃኖም፣ ለኃይለማርያም እና ለወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ እ.ኤ.አ በ2013 በሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እንደተፈጸመው፣ እ.ኤ.አ በ2005 በኢትዮጵያ የድሀረ ምርጫውን ውዝግብ ተከትሎ ተፈጥሮ እንደነበረው…ሁሉ ተመሳሳይ እንደሆነ አድርገው ነው የሚመለከቱት፡፡ ጉዳዩ ለአንድ ሳምንት ወይም ለሁለት ሳምንታት ያህል የሚያነጋግር ይሆን እና ከዚያ በኋላ እልም ሙልጭ ብሎ በመጥፋት ያው የተለመደው አካሄድ ይቀጥላል፡፡
በዚህ ባሳለፍነው የካቲት ወር ከ21 በላይ የግብጽ ጳጳሳት በጭራቃዊ አሸባሪ ቡድን አባላት በታረዱበት ጊዜም እንደዚሁ ምንም ነገር ሳይደረግ ነው የቀረው፡፡ በሊቢያ አንገታቸውን እንደተቀሉት ኢትዮጵያውያን ሁሉ የግብጽ ጳጳሳትም ብርቱካናማ ልብስ እንዲለብሱ ተደርገው እና እጃቸውን ወደ ጀርባቸው አድርገው በማሰር እልቂቱ እንዲፈጸምባቸው ተደርጓል፡፡ የግብጽ ወንዶች እንደ ኢትዮጵያ ወንዶች ሁሉ አንገታቸው ከመቀላቱ በፊት እንዲንበረከኩ ተደርገዋል፡፡
ፕሬዚዳንት አብደል ኤል ሲሲ የግብጽ ጳጳሳት አንገት መቀላቱን በሰሙ ጊዜ እንደ እብድ ሆነው ነበር፡፡ በቴሌቪዥን የዘለቀ ንግግር በማድረግ ለዚህ ዕኩይ ድርጊት ግብጽ ወዲያውኑ የአጻፋ እርምጃ እንዳትወስድ እና የመቆጠብ መብት እንዳላት አሳስበው ነበር፡፡ ጥልቅ የሆነ ሀዘናቸውን እንዲህ በማለት ገልጸው ነብር፣ “በሊቢያ የሞራል ስብዕና በጎደለው መልኩ ያለቁትን የግብጽ የጥቃት ሰለባዎች የዓለም ህዝብ እንዲገነዘበው እና በዚህ አሰቃቂ ዕልቂት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እና የግብጽ ህዝብ የተጎዳውን ጉዳት ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡“ በሰዓታት ጊዜ ውስጥ ኤል ሲሲ በሊቢያ ከመከላከያ ምክር ቤታቸው ጋር በመምከር የአሸባሪዎች መቀመጫ ከተማ በሆነችው ዴርና ተብላ በምትጠራው የሊቢያ ከተማ ላይ የግብጽን ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች ለማሰማራት ስምምነት አደረጉ፡፡ በአሰቃቂ ሁኔታ በግፍ ለተገደሉት 21 የግብጽክርስቲያኖች ሰማአታት ክብር ሲባል ግብጽ የሰባት ቀናትየሀዘን ቀናት አድርጋ አወጀች! በጣም የሚያበሳጨው እውነታ ደግሞ በሊቢያ የሚገኙት ቀሪዎቹ የኢትዮጵያ ስደተኞች እና በሊቢያ ከወያኔ አገዛዝ አምባሳደር የስልክ ቁጥር ተስጥቷቸው ግንኙነት እንዲያደርጉ ቢነገራቸውም ምንም ዓይነት የማቴሪያል እና የሞራል ድጋፍ ያለመደረጉ ጉዳይ ነው፡፡ እርዳታ ለማግኘት ሲያደርጓቸው የነበሩት ጥረቶች ሁሉ በግዴለሽነት ምክንያት ስኬታማ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡ አሁን በቅርቡ ከአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ፕሮግራም ጋር ከኢትዮጵያ ስደተኞች ጋር ከተደረገ ቃለ መጠይቅ በተገኘ ዘገባ መሰረት ስደተኞቹ እርዳታ ከማግኘት ይልቅ ቸልተኝነትን እና ግድየለሽነትን አሳይተዋቸዋል፡፡ አንድ ቃለመጠይቅ አድራጊ እንዲህ የሚል ዘገባ አቅርቦ ነበር፡
“በግብጽ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር ለመገናኘት እና ድጋፍ ለማግኘት የኤምባሲውን ስልክ ቁጥር አግኘተን ነበር፡፡ ሆኖም ግን ከኢትዮጵያ መንግስት ምንም ዓይነት እርዳታ አላገኘንም፡፡ ይልቁንም በገዛናት ትንሽ የስልክ ጥሪ ካርድ በመጠቀም በግብጽ ካለው የኢትዮጵያ  ኤምባሲ ጋር ለመገናኘት የተቻለንን ያህል ጥረት በማድረግ ስንደውል ነበር፡፡ በምንደውልበት ጊዜ ስልኩን ያነሱ እና ያሾፉብን ነበር፡፡ ከእኛ ጋር ንግግር አያደርጉም ነበር፡፡ ስልኩን ያነሱ እና ከእኛ ጋር ባለመነጋገር ስልኩ የጥሪ ካርዱን ያለምንም ፋይዳ እንዲጨርስ ያደርጉብን ነበር፡፡ ከዚያም ሌላ ካርድ እንገዛ እና እንይዛለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ ምላሽ ይሰጣሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ምንም ዓይነት ምላሽ አይሰጡም…”
ሌላ በአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ፕሮግራም ቃለ መጠይቅ የተደረገለት ሰው ደግሞ እንዲህ የሚል ተመሳሳይነት ተሞክሮ ያለው ዘገባ አቅርቧል፡
“በእርግጥ አድኃኖም፣ ኃይለማርያም እና ወያኔ ለእነርሱ ምን እንደሚናገሩ ሁላችንም እናውቃለን፡ ምንም ነገር አይተውም፡፡ እድሉን አግኝተው ነበር ነገር ግን አልተጠቀሙበትም፡፡ ስለዚህም ቀደም ሲል ነግረናቸዋ፡፡ ከዚያም ትምህርት ይቀስማሉ ብለን እናስባለን…ዘበት! ዘበት! ዘበት! …“
ግን የኢትዮጵያ ወጣቶች እግሮቻቸው ወደመሯቸው የሚሄዱት ለምንድን ነው?
በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ወጣቶች ሀገራቸውን በመልቀቅ እንደዚህ ላለ አደገኛ የሆነ ችግር ውስጥ የሚገቡት ለምንድን ነው?
ወተት እና ማር የሚፈስባትን እና ባለሁለት አሀዝ የምጣኔ ሀብት ዕድገት እያስመዘገበች ነው እየተባለ የሚደሰኮርላትን ሀገራቸውን እየለቀቁ ለመሰደድ የሚመርጡት በምን ምክንያት ነው?
ዕድለቢሶቹ ኢትዮጵያውያን አሰቃቂ የሆነውን የዕልቂት ዕጣ ፈንታ ለመገናኘት ወደ ሊቢያ የሚጓዙት ለምንድን ነው?
ለእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልሱ ቀላል እና አጭር ነው፡፡ እነዚህ ወጣቶች ኢትዮጵያን ጥለው የሚሄዱት በትምህርት እና በሥራ ዕድል በተንበሸበሸ ስርዓት ውስጥ ስለኖሩ ነው?  እነዚህ ወጣቶች ኢትዮጵያን ጥለው የሚሄዱት የምጣኔ ሀብት ነጻነትን ተጎናጽፈው ስለኖሩ ነው? እነዚህ ወጣቶች ኢትዮጵያን ኢትዮጵያን ጥለው የሚሄዱት በሰሜን አፍሪካ ባሉ በረሀዎች ላይ ጀብዶችን ለመስራት ስለሚፈልጉ ነው?  እነዚህ ወጣቶች ለሁሉም ነገር አደጋን ህይወታቸውን ጨምሮ የመጋፈጥ ድፍረቱ አላቸው ምክንያቱም ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚያገኙት የኑሮ ሁኔታ የበለጠ ወደ ውጭ በመሰደድ የተሻለ የኑሮ ሁኔታ ማግኘት ስለሚችሉ ነው፡፡ ህይወታቸውን ለማሻሻል ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖሩ ነበር፣ ሆኖም ግን በድህነት አረንቋ ውስጥ ተዘፍቀው የሚገኙትን ደኃ ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት ሲሉ በተቃጠለው የአፍሪካ በረሀ በመጓዝ የመሞት አደጋን ይጋፈጣሉ፣ ወይም ደግሞ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚገኙ ጨካኝ ለሆነ ወይም ለሆነች የቤተሰብ ኃላፊ አገልጋዮች ይሆናሉ፡፡
በአሁኑ ጊዜ ወጣት ኢትዮጵያውያን በወያኔ አምባገነን ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ቁጥጥር ስር በድህነት እና በነጻነት እጦት ተዋርደው ከሚኖሩ ይልቅ እግራቸው ወደመራቸው በበረሀ እና በጫካ ውስጥ ሄደው ለመሞት ፈቃደኞች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ወጣቶች ወደ ሊቢያ በመሄድ እንዲህ የሚለውን ታዋቂ የነጻነት መፈክር በማሰማት የሞት ጽዋቸውን ተጎንጭተዋል፡ “ሞቴን ስጠኝ ወይም ደግሞ ነጻነቴን ስጠኝ!“ እነዚህ ወጣቶች ከወሮበላ አምባገነኖች የግፍ አገዛዝ ነጻ ሆነው ለመኖር ሲሉ በሌሎች ወሮበሎች እጅ ወድቀው ህይወታቸውን አጥተዋል! ሆኖም ግን በነጻነት ለመኖር ሙከራ ሲያደርጉ በመስዋዕትነት አልፈዋል!
ኢትዮጵያውያን/ት ሀገራቸውን ከልብ ይወዳሉ፡፡ ሀገራቸው በዲኤንኤ ዘረመላቸው ውስጥ ተቀብሮ የሚኖር ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን የመጨረሻዎቹ ወንድ እና ሴት እስከሚቀሩ ድረስ የምጣኔ ሀብት ፍላጎታቸውን ለማሻሻል ሲሉ ብቻ ሀገራቸውን ትተው እና በከፍተኛ አደጋ ውስጥ ገብተው በፈቃደኝነትም ሆነ በሌላ መልክ ከሀገር በመውጣት ስደተኛ አይሆኑም ወይም ደግሞ በረሀውን እና ጫካውን እያቋረጡ የአውሬ እና የአሞራ እራት አይሆኑም፡፡ ወጣቶች ሀገራቸውን ባለመውደዳቸው ምክንያት አይደለም እየተሰደዱ ያሉት ሆኖም ግን የፍቅር እና የሰላም የነበረችው መሬት ወደ ጥላቻ መሬትነት በመሸጋገሯ ምክንያት ነው፡፡ የ13 ወራት የጸሐይ ብርሀን ባለቤት የሆነችው ሀገራቸው አስከፊ በሆነ የአምባገነንነት የጨለማ መጋረጃ ለሩብ ምዕተ ዓመት ያህል በመሸፈኗ ብቻ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን ትተው ከሚሰደዱ ይልቅ ለሀገራቸው ያላቸው ፍቅር የበለጠ ነው፡፡
እንደ ጣሴ አብይ ዘገባ የኢትዮጵያውያን/ት ወደ ውጭ ሀገር የሚደረግ ፍልሰት እንደማዕበል ሆኖ በታሪክ ተመዝግቧል፡፡ እ.ኤ.አ በ1960ዎቹ የተካሄደው የመጀመሪያው ማዕበል በጣም ጥቂት በሆኑ ምሁራን እና በጊዚያዊነት ብቻ አብዛኛውን ጊዜ ወደ ምዕራቡ ዓለም በዋናነት በትምህርት እና በስልጠና ስም ከሀገር የሚወጡ እና ወደ እናት ሀገራቸው የመመለስ ዓላማን ያነገቡ ነበሩ፡፡ ያ አዝማሚያ እ.ኤ.አ ከ1974 – 1982 ባሉት ዓመታት ውስጥ የተከናወነው ሁለተኛው የስደት ማዕበል ነው፡፡ በዚህ ጊዜ አምባገነኑ እና አረመኔው የወታደራዊ መንግስት እ.ኤ.አ ከ1974 ጀምሮ ማንኛውም ዜጋ ሀገሩን ትቶ መሰደድ እንዳይችል ከፍተኛ የሆነ ችግር ፈጥሮበት ነበር፡፡ እናም በተለያየ ሁኔታ ከሀገር ሾልከው ለመኮብለል ሲሞክሩ የተገኙ ዜጎች ላይ አደገኛ የሆነ ቅጣት ይጣል ነበር፡፡ የደርግ ወታደራዊ ጭቆና የኢትዮጵያውያንን የስደተኞች የጎርፍ በር ብርግድ አድርጎ ከፈተው፡፡
በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት የኑሮ መሰረታቸውን በሰሜን አሜሪካ ለማድረግ ሀገራቸውን ትተው ይሰደዳሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ1965 የዩኤስ አሜሪካ የስደተኞች እና የዜግነት ድንጋጌ ሕግ ሀኖ ከወጣ በኋላ ኢትዮጵያውያን/ት ወደ ዩኤስ አሜሪካ ለመሰደድ ከአፍሪካ ሶስተኛ በመሆን ትልቅ ደረጃ ላይ ሆና ተገኝታለች፡፡
አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን/ት ወደ አሜሪካ የደረሱት ዩናይትድ ስቴትስ እ.ኤ.አ በ1980 በምክር ቤቱ ህግ ሆኖ ከወጣ በኋላ ሶማሌዎች እ.ኤ.አ በ1994 በመቅደም የመሪነቱን ቦታ እስከሚይዙት ድረስ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ታላቁ የስደተኞች ቡድን ሆና ቆይታለች፡፡
እንደ ጣሴ ዘገባ እ.ኤ.አ በ1991 የኮሎኔል መንግስቱ አገዛዝ ከወደቀ በኋላ አራተኛው የስደተኛ የጎርፍ ማዕበል አብዛኛውን ጊዜ የጎሳ ግጭትን ለማምለጥ እና የፖለቲካ ጭቆናን ለማስወገድ ሲባል የጎሳ ባለሙያዎች በገፍ ከሀገር መሰደድ ጀመሩ፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ ለመኖር  በጣም አስቸጋሪ የሆነበት እና ሀገርን ጥሎ ለመሰደድ የተቻለበት ጊዜ አምስተኛው ማዕበል እየተባለ የሚጠራው የስደተኞች ጊዜ ነው፡፡ “ከዓለም አቀፍ የባሪያ ንግድ ወደ ዓለም አቀፍ የቤት ሰራተኛ ንግድ“ በሚል ርዕስ እ.ኤ.አ ጥር 2012 ባቀረብኩት ትችት መሰረት ወደ ውጭ ለሚደረግ ስደት ዋናው ምክንያት የኢትዮጵያ ውስጣዊ የፖለቲካ ሁኔታ ነው፡፡
በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አገዛዝ ዘመናዊ የባሪያ በንግድ አስፈጻሚዎች ትስስር እና ፈቃድ አውጥተው እየሰሩ ያሉ የግል ቀጣሪ ኤጀንሲዎች በመካከለኛው ምስራቅ በኢትዮጵያውያን ሴቶች ላይ ታላቅ ችግርን ፈጥሯል፡፡ እነዚህ የሰው ንግድ የሚያካሂዱ ድርጅቶች የኮንትራት ባርነትን በመፍጠር በድብቅ በባለስልጣኖች የሚሰጥ ድጋፍ እና ምንም ዓይነት የክትትል ስራ ሳይሰራ የሰራተኞችን ደህንነት እና የኑሮ ሁኔታ በሄዱበት ሀገር የሚረጋገጥ ይሆናል፡፡
በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞች በቢና ፌርናንድዝ ጥናት በ7ኛው ምዕራፍ ላይ ተመዝግቦ ይገኛል፡፡ እ.ኤ.አ በ2009 በየመን አድርገው ወደ ሳውዲ አረቢያ ለመሸጋገር 74 ሺህ ህዝብ በአደጋ ውስጥ ወድቆ የነበረ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 42 ሺህ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን/ት ናቸው፡፡ በመንግስት መረጃ መሰረት በመካከለኛው ምስራቅ ከሚገኙት ኢትዮጵያዊ የቤት ሰራተኞች ውስጥ 91 በመቶ የሚሆኑት ብቻቸውን ያሉ ሴቶች ሲሆኑ 83 በመቶ የሚሆኑት ከ20- 30 ባሉት የእድሜ ጣሪያ ውስጥ የሚገኙት ናቸው፡፡ ወደ 63 በመቶ የሚሆኑት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያላቸው ሲሆኑ 26 በመቶ የሚሆኑት ምንም ዓይነት ማንበብ እና መጻፍ የማይችሉ ማይሞች ናቸው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ደግሞ 71 በመቶ የሚሆኑት ሙስሊሞች ሲሆኑ 93 በመቶ የሚሆኑት በየወሩ ከ100 – 150 ዶላር የኪስ ግንዘብ ይሰጣል፡፡ እነዚህ ጥቂት ሴቶች ከመንግስት ጋር በስደተኛ ሰራተኝነት በመንግስት ምዝገባ ያደርጋል፡፡ ሌሎቹ ህገወጥ ደላላዎች እና ላባቸውን ያላፈሰሱበትን መውሰድ የሚፈልጉ በዝባዦች ደግሞ የሴቶችን ገንዘብ ቀምተው ይወስዱ እና ሶማሌ እንኳ ሳይደርሱ በበረሀ ላይ ጥለዋቸው ይሄዳሉ፡፡
ህወሀት እና ህገወጥ የሰዎች ዝውውር፣
እ.ኤ.አ ከ1998 ጀምሮ የመለስ ዜናዊ አገዛዝ በአዋጅ ቁጥር 104/1998 የግል ስራ ቀጣሪ ኤጀንሲን በማቋቋም ለግል ስራ ቀጣሪ ኤጀንሲዎች እና ህገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎችን እና ደላላዎችን በህግ ሊያስጠይቅ የሚችል አዋጅ አወጣ፡፡ እ.ኤ.አ በ2009 ይኸ አዋጅ ተሻረ እና “የስራ አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 632/2009“ በሚል ሌላ አዋጅ ተተካ፡፡ ይህ አዲሱ አዋጅ የግል የስራ ቀጣሪ ኤጀንሲዎች እድሚያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ሰዎችን መቅጠር እንደማይቻል፣ ከተቀጣሪው ሰው ጋር በጽሁፍ ስምምነት እስካልተደረሰ በስተቀር ማንንም ሰራተኛ ተነስቶ ከስራው ማባረር እንደማይቻል፣ ስራ ለመቀጠር እና አዲስ ስምምነት ለመፈራረም ወይም የቆዬ ስምምነትን ለማደስ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽ/ቤት ፈቃድ ማግኘት እንደሚያስፈልግ፣ ወደ ውጭ ሀገር የሄደ ስራ ፈላጊ በ15 ቀናት ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽ/ቤት ቀርቦ መመዝገብ እንዳለበት በግልጽ አስቀምጧል፡፡  
ስራ ፈላጊዎችን ወደ ውጭ ሀገር የሚልክ የግል ስራ ቀጣሪ ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ዜጎች ለስራ ፍለጋ የሄዱበት ሀገር የስራ ሁኔታ የሌሎች ሀገሮች ስራ ፈላጊዎች ሄደው ከሚሰሩት የስራ ሁኔታ እና ያነሰ ጥቀም እንዳይኖረው የማረጋገጥ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ የውጭ ሀገር ቀጣሪ ሰራተኛው ለተንቀሳቀሰበት ሀገር የቪዛ ክፍያ፣ የደርሶ መልስ ቲኬት፣ የኗሪነት፣ የስራ ፈቃድ እና የኢንሹራንስ ክፍያዎችን ለሰራተኛው እንዲከፍል ይጠበቅበታል፡፡ ከዚህም በላይ ስራ ፈላጊዎችን ወደ ውጭ ሀገር ልኮ ስራ ለማስቀጠር ፈቃድ የተሰጠው ማንኛውም የግል ስራ ቀጣሪ ኤጅንሲ የሰራተኛውን መብት ለማስጠበቅ እና በመብቱ ሊያገኛቸው የሚፈለጉትን ጥቅሞች ተግባራዊ ለማስደረግ እስከ 500 ለሚሆኑ ሰራተኞች ቢያንስ 30,000 ዶላር በባንክ ሂሳብ ማስቀመጥ ወይም ደግሞ ቦንድ መግዛት እንዳለበት ግዴታ ተጥሎበታል፡፡
አዋጅ ቁጥር 632ን ተላልፎ የተገኘ ማንኛውም የግል ስራ ቀጣሪ ኤጀንሲ ስራው ለተወሰነ ጊዜ እዲቋረጥ፣ ህገወጥ ስለሆነ ወደ ተግባር መሸጋገር እንደማይችል ወይም ደግሞ የስራ ፈቃዱ እንደሚሰረዝ በግልጽ ያስቀምጣል፡፡ በዚያ አዋጅ በአንቀጽ 40 ስር በርካታ የሆኑ አሳሪ የወንጀለኛነት ቅጣቶች ተዘርዝረው የተቀመጡ ቢሆንም ቅሉ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስፈጻሚዎችን ወደ ህግ ሊያቀርብ የሚያስችል ተግባራዊ እንቅስቃሴ ግን በጣም አናሳ መሆኑን ሊያስረዱ የሚችሉ ማስረጃዎች አሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2010 የወጣው የዩኤስ የመንግስት መምሪያ ዘገባ ከሆነ እ.ኤ.አ በመጋቢት እና ጥቅምት 2009 መካከል የፌዴራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት 11ኛ የወንጀል ችሎት ስለድንበር ተሻጋሪ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ጋር የተያያዙ 15 ጉዳዮች ቀርበውለት ከእነዚህ ውስጥ 5ቱ የጥፋተኝነት ብይን የተሰጠባቸው፣ 9ኙ ጥፋተኝነት የሌለባቸው እና አንዱ ደግሞ ምስክር ባለመገኘቱ ምክንያት እንዲቋረጥ የተደረገ ሆኗል፡፡ 5ቱ የጥፋተኝነት ብይን ከተሰጠባቸው መካከል 3ቱ ተከላካዮች የ5 ዓመት እስራት በመጣል ስራቸውም እንዲቆም ሲደረግ፣ ሁለቱ ተከላካዮች ደግሞ በገንዘብ እንዲቀጡ የተደረገ ሲሆን አንዱ ተከላካይ ደግሞ የ5 ዓመት እስራት ተበይኖበታል፡፡
በተመሳሳይ መልኩ የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን/United Nations Higher Commission for Refugees (UNHCR) እ.ኤ.አ በ2011 እንዲህ የሚል ዘገባ አውጥቷል፣ “የኢትዮጵያ መንግስት የእራሱ ዜጎች ለስራ ጉዳይ ከሚሄዱባቸው ሀገሮች መንግስታት ጋር የኢትዮጵያ ሰራተኞችን የስራ ሁኔታ ለማሻሻል እና የጥቃት ሰለባ የሚሆኑትን ዜጎቹን ደህንነት ለመጠበቅ ሲል ብዙ ርቀት ያልተጓዘ እና ገና በጅምር ላይ ነው፡፡ ከዚህም በላይ ፈቃድ ያላቸው የሰራተኛ ቀጣሪ ኤጀንሲዎች የሰራተኞች የውል/ኮንትራት ስምምነት ቢቋረጥ ለመያዣነት በሚል ከሰራተኞች እየተቆረጠ ገንዘብ በባንክ እንዲቀመጥ የሚደረግ ቢሆንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህንን የተከማቸውን ገንዘብ የጥቃት ሰለባ ሆነው ወደ ሀገራቸው ወደ ኢትዮጵያ በሚመለሱበት ጊዜ ለእነዚህ የጥቃት ሰለባ ለሆኑት ሰራተኞች ምንም ዓይነት የትራንስፖርት መጓጓዣ አይከፍልም፡፡“
ሆኖም ግን የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ሌሎች የህገወጥ የሰዎች ዝውውር ሰለባዎችን ከአደጋ ለመከላከል ሲታትር ይታያል፡፡ ለምሳሌ ያህልም እንዲህ የሚለውን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽንን ዘገባ ማየቱ ለዚህ ታላቅ ማስረጃ ነው፣ “እ.ኤ.አ በ2010 ኢትዮጵያ በሲናይ በረሀ በራሻዳ የኮንትሮባንድ ህገወጦች የሚዘረፉትን፣ የሚሰቃዩትን፣ በግዴታ በግንባታ ስራ ላይ እየተመደቡ ጉልበታቸውን የሚበዘበዙትን እንደዚሁም ደግሞ ከብሄራዊ ውትድርና አገልግሎት ፕሮግራም ጋር በተያያዘ መልኩ ከኤርትራ እየኮበለሉ ወደ ጎረቤት ሀገር የሚሰደዱትን የኤርትራ ዜጎች እና ከግብጽ ለተጋዙት 1,383 የኤርትራ ስደተኞች ጥገኝነት ሰጥታለች፡፡“ እንደዚህ ዓይነቱ ከህገወጥ የሰዎች ዝውውር ጋር በተያያዘ መልኩ የጥቃት ሰለባ ለሚሆኑት እና የሰብአዊ መብታቸውን ተነፍገው ለሚሰቃዩት ዜጎች ከለላ መሆን እና መጠለያ መስጠት ከመልካም ስራ እና ከሞራል ስብዕና አንጻር በጎ ምግባር ቢሆንም ቅሉ ደግነት ከቤት መጀመር እንዳለበትም እውነት ነው፡፡
ለችግሩ መፍትሄ ለመፈለግ ቃል የተገባው .. 2013 ነበር፡፡
እ.ኤ.አ. ጥቅምት 2013 የኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞች እና ጥገኝነት የጠየቁ ወገኖች በሳውዲ አረቢያ ስቃይ እና መከራን እየተቀበሉ በነበረበት ወቅት አድኃኖም እንዲህ ብሎ ነበር፡ “በእርግጥ ከብዙ ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ የሚደርሰውን ችግር ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስወገድ እና መፍትሄ ለመስጠት የአጭር እና የረዥም ጊዜ ዕቅድ በመንደፍ ያላሰለሰ ጥረት ስናደርግ ቆይተናል፡፡ እናም እንደምታውቁት ሁሉ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሆነ መሻሻል እያሳየች እና ባለሁለት አሀዝ ዕድገት (ይህንን ባለሁለት አሀዝ የምጣኔ ሀብት ዕድገት እየተባለ በየዕለቱ የሚደሰኮርለትን ተራ ፕሮፓጋንዳ ተጨባጭ መረጃ በማቅረብ በማጋለጥ ከምንም ጥርጣሬ በላይ ቅጥፈት፣ ነጭ ውሸት እና የቁጥር ጨዋታ ነው በማለት ቀደም ሲል ማስተባበሌን ልብ ይሏል) እያስመዘገበች ነው፡፡ ከዋሻው መጨረሻ ብርሀን ይታያል፣ እናም ማድረግ እንደምንችል እናውቃለን፡፡ ድህነትን ማጥፋት እንደምንችል እናውቃለን፡፡ ጉዟችን በትክክለኛው ጎዳና ላይ ነው፡፡ ሆኖም ግን እስከ አሁንም ድረስ በዓለም አቀፋዊ ትብብር ማመን አለብን፡፡ ቢሆንም ግን እንደዚህ ያለ ሁኔታ ይፈጸማል ብለን አልጠረጠርንም፡፡“ አጽንኦ ተጨምሯል፡፡)
አድኃኖም ከተናገራቸው ንግግሮች ውስጥ በኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ በሳውዲ አረቢያ “እንደዚህ ያለ ሁኔታ ይፈጸማል ብለን አልጠረጠርንም ነበር” ወይም ደግሞ ለእርሱ ሁሉም ነገር “ፍጹም አስገራሚ ነበር“ በሚሉት አባባሎች ላይ ለማመን እስከ አሁንም ድረስ ይከብደኛል፡፡ በእርግጥ በዚያን ወቅት አዘጋጅቸው በነበረው ትችቴ ላይ በግልጽ እንዳስቀመጥኩት ሁሉም ነገር “ፍጹም አስገራሚ ነበር“ የሚለው አባባል ለሁሉም አስገራሚ ሊሆን እንደማይችል አስገንዝቤ ነበር፡፡ እ.ኤ.አ ጥቅምት 2013 ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረቢያ እንደዚያ ያለ የሰብአዊ ቀውስ አደጋ ይድረስባቸዋል በማለት አድኃኖም የወደፊቱን በትክክል ይተነብያል ለማለት የሚያስደፍር ምንም ዓይነት ተጨባጭ ሁኔታ የለም፡፡
ያም ሆነ ይህ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን እየተው በገፍ ወደ ሌሎች ሀገሮች የሚጎርፉበትን ጉዳይ እና እንደ ጥገኝነት ጠያቂነታቻው በሄዱባቸው ሀገሮች ሁሉ መብቶቻቸው ተጠብቀው እና የሰራተኞች የውል/ኮንትራት ስምምነትም በተለይም ደግሞ በመካከለኛው ምስራቅ በሚደረጉት ላይ መፍትሄ ለማምጣት አድኃኖም “ለብዙ ጊዜ ስንሰራው የቆየነው የአጭር እና የረዥም ጊዜ ዕቅድ መፍትሄ” እያለ የሚጠራው ምን እንደሆነ ለማወቅ በመጠባበቅ ላይ ነኝ፡፡
እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2015 ሆነን የተባለውን እና ቃል የተገባለትን ነገር ሁሉ ስንቃኘው ምንም የተለወጠ ነገር የለም፡፡ ወጣት ኢትዮጵያውያን/ት ወንዶች እና ሴቶች እግሮቻቸው ወደመሯቸው በመጓዝ ላይ ናቸው (በእጆቻቸው ሊመሩ ባለመቻላቸው፡፡) በመካከለኛው ምስራቅ ለመናገር በሚያዳግት ሁኔታ የጥቃት ሰለባ የመሆናቸው ጉዳይ ቀጥሎ ይገኛል፡፡ እነዚህ ወገኖቻችን ድብደባ ይፈጸምባቸዋል፣ ይሰቃያሉ፣ በረሀብ እንዲጠቁ ይደረጋሉ፣ ይሰቀላሉ፣ አሁን ደግሞ አንገታቸውን ይቀላሉ፡፡
እነዚህ ወንጀሎች አድኃኖም “ለብዙ ጊዜ ስንሰራው የቆየነው የአጭር እና የረዥም ጊዜ ዕቅድ መፍትሄ” በአገዛዙ በኩል በመደረግ ላይ ነው ብሎ በድፍረት ከተናገረ ከሁለት ድፍን ዓመታት በኋላም ሁኔታዎች ሁሉ ይዘታቸውን፣ የመፈጸም የጊዜ ፍጥነታቸውን እና መጠናቸውን በመጨመር በተጠናከረ መልኩ በመፈጸም ላይ ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም የአድኃኖምን እና የኃይለማርያምን ተወዳጅ ሀረጎች በመዋስ በመካከለኛው ምስራቅ እንዲሁም በደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ “የዘር አደን/race hunted” እና “የኃይማኖት አደን/religious hunted” ይፈጸማል ልበል ይሆን! እነዚህን ወገኖቻችንን ለመርዳት እና ለመናገር ከሚዘገንኑ ወንጀሎች ለመጠበቅ እስከ አሁን ድረስ ምንም ዓይነት ነገር አልተሰራም!
እንደ አካደሚክ፣ የህግ እና የሰብአዊ መብት ጥበቃ ወትዋች ባለሙያ ኢትዮጵያውያን/ት በአሸባሪዎች፣ በወሮበሎች፣ በዘራፊዎች እና ሰብአዊ መብታቸውን በሚደፈጥጡ የሰራተኛ ቀጣሪዎች የጥቃት ሰለባ መሆናቸው ብቻ ላይ አይደለም ብዙ መሰራት ያለበት፡፡ ሆኖም ግን በህግ ጥላ ከለላ ስም ህጉን እየጣሱ እና እየደረመሱ ከህግ ውጭ እየተራመዱ በወገኖቻችን መብቶች እና ህይወት ላይ ቁማር በሚጫወቱ ኃላፊ ተብዬዎች ላይ ነው ብዙ ነገር መሰራት ያለበት፡፡ ለምንድን ነው በአሁኑ ጊዜ ለኢትዮጵያውያን/ት ጥገኝነት ጠያቂዎች እና በሀገር ውስጥ መብታቸውን ለሚያጡ ሰራተኞች መፍትሄ ሊፈልግ የሚችል ቋሚ እና ልዩ ግብረ ኃይል የማይቋቋመው? ለምንድን ነው የሲቪል ማህበረሰብ ቡድኖች ዜጎች ወደ ውጭ እንዳይሰደዱ የማይከላከሉት እና ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚመለሱት ስደተኛ እና ጥገኝነት ጠያቂ ወገኖቻችን በሀገራቸው ላይ ስራ አግኝተው በሰላም እንዲኖሩ የማያግዙት? ለመሆኑ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ስለኢትዮጵያውያን/ት ጥገኝነት ጠያቂዎች፣ የኮንትራት ሰራተኞች እና ሌሎች ምንም ዓይነት ጥሩ አያያዝ ለማይደረግላቸው፣ ሰብአዊ መብቶቻቸው ለሚደፈጠጡባቸው እና ለሚሰቃዩት ወገኖቻችን ደንታ አለውን? እንዴት ሆኖ! (በእርግጥ ይኸ የድስኩር እንጅ የተግባር ጥያቄ አይደለም፡፡)
ኢትዮጵያውያንን/ትን በሳውዲ አረቢያው እንደደረሰው ያለ ቀውስ በሚያጋጥምበት ጊዜ ለዜጎቹ የሚያስብ ማንም አገዛዝ ቢሆን የአስቸኳይ ጊዜ ግብረ ኃይል በማቋቋም በተቀነባበረ መልኩ እገዛ እያደረገ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችን እየቀረበ እርዳታ እና ድጋፍ ማሰባሰብ ይኖርበታል፡፡ (ዓለም አቀፍ ድርጅቶችን እየቀረበ ስል ከእነርሱ ገንዘብን እየለመነ ወደ ኪሱ ያጭቅ ማለቴ እንዳልሆነ ልብ ይባልልኝ፡፡) አድኃኖም እና አገዛዙ በመካከለኛው ምስራቅ እና በሌሎች ሀገሮች በኢትዮጵያውያን/ት የቤት ሰራተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ላይ የደረሰው የአደጋ ሁኔታ ሲያልፍ የትርፍ ስሌታቸውን በመስራት እንደተለመደው የንግድ ጥባ ጥቤ የቁማር ጨዋታቸውን ይቀጥላሉ፡፡
ስለሆነም እነዚህን ሊመለሱ የማይችሉ ጥያቄዎችን ለእራሴ በመጠየቅ እንዲህ የሚሉትን የብቸኝነት የግጥም ስንኞችን እነሆ… 
ምንድን ነው ነገሩ? 
ምንድን ነው ነገሩ እስቲ ተናገሩ፣
ከቶ ምንድን ይሆን ይህ ሁሉ እሽሩሩ፣
ዕልቂት ዕጣ ፈንታ የሆነ ተግባሩ፣
ሰው መኖር አይችልም በገዛ ሀገሩ?
የኢትዮጵያውያን ነብስ እንዴት ረከሰ፣
በሊቢያ በሳውዲ ደም እየታፈሰ፣
በሲናይ በረሀ አሸዋ እየላሰ፣
ባሸባሪ ቡድን ሰው እየታመሰ፣
ደሙ ተግተልትሎ እንባውም ፈሰሰ፡፡
በሰይጣን ምግባራት ወገን ተላቀሰ፡፡
ጉልበቴን መንዝሬ ልኑር ልስራ ባለ፣
ለሌላው ሰው ድሎት ጉልበቱን ባዋለ፣
ከሀገር ተሰዶ በተንቀዋለለ ነብሱን ባቃጠለ፣
ከሰማይ ጠቀስ ፎቅ ተገፍቶ ተጣለ?
በጥይት እሩምታ በግፍ ተገደለ?
 ስራ ልስራ ብሎ ካገር በነጎደ፣
ለህይወት መሻሻል ሀሳብ ባራመደ፣
እንደ ፋሲካ በግ በካራ ታረደ?
ለመስራት አቅዶ ከሄደ በኋላ፣
ለደኃ ወገኑ ሊሆን ጋሻ ባላ፣
ችጋርን በማጥፋት በጥረት በመላ፣
ሊመለስ ላገሩ ነገሩ ሲብላላ፣
እንደ ሀገር ጠላት በጥይት ተቆላ?
 ሀገር እንደሌለው እንደ ባዕዳ ሰው፣
ከሀገር ተገፍቶ ሀገር እያለው፣
መኖር አልችል ያለ መብት የሌለው፣
በበረሀ ቀልጦ ጫካ የቀረው፣
የአራዊት መፈንጫ ነብሱ የሆነው፣
በባዕድ ሀገር ባከኖ ውኃ የበላው፣
እሱን ማን ልበለው ኢትዮጵያዊ ነው፡፡
አንች የሀገር ቆንጆ ተስፋው የራቀሽ፣
በሀገርሽ መኖር ፍጹም ተስኖሽ፣
በባዕድ ሀገር ሆነሽ ኑሮን የቀመስሽ፣
ከስብዕና በታች ሆኖ ህይወትሽ፣
ያልፍልኛል ብለሽ ውጥንቅጥ ኑሮሽ፣
ዘመድ ወገኖችሽ እንደናፈቁሽ፣
በሰው ሀገር ሄደሽ ባክነሽ የቀረሽ፣
ሀዘናችን ከፍቷል እስቲ ተመለሽ፡፡
አዕምሮ የሰጠን ለማመዛዘን ነው፣
ደግ እና ክፉውን ለማነጻጸር ነው፣
ግና ምን ያደርጋል ሁሉ አይተገብረው፣
ወያኔ ያዋለው ተንኮል ለማድራት ነው፣
ህዝብን ከህዝብ ጋር ለማተራመስ ነው፡፡
የኢትዮጵያውያን ደም ቢፈስ ቢንዠቀዠቅ፣
በጥይት ቢቆላ በገመድ ቢታነቅ፣
ቢጣል በውቅያኖስ በወንዝ እና በሐይቅ፣
ወያኔ ከጥቅሙ መች ይል እና ንቅንቅ፡፡
ምንድን ነው ነገሩ እስቲ ተናገሩ?
ማንንም ሳትፈሩ ሳትደናገሩ፣
አንድም ነገር የለ በባህር ባየሩ፣
በየብስ በጫካው ባፈሩ በዱሩ፣
የኢትዮጵያ ደም ነው ዶፉ ውሽንፍሩ ፡፡
ምንም የሚያሳስብ የለም አንድ ነገር፣
በባህር በወንዙ ባየሩም በምድር፣
በሰማይ በጫካ በሐይቁ በባህር፡፡
 በመሬት ቢዞሩ ባየር ላይ ቢበሩ፣
የማያሳስበው ምንድን ነው ነገሩ?
የኢትዮጵያ ደም ነው ጎርፉ ስንክሳሩ?
የወጣቶቸ  ደም ነው ዘዋሪው አኪሩ?
ያሳስባል እንጅ በውንም በህልምም፣
በግፈኞች ድርጊት ህይወት ስትጨልም፣
ራዕይ ሲኮላሽ ሃሳቦች ሲመክኑም፣
ጭራቃዊ ድርጊት ባለም ሲለመልም፡፡
 ምንድን ያሳስባል በዚህች ምድር ላይ?
ደኃውን ሀብታሙን ሁሉንም ስናይ፣
ሀቀኛ ሲያዳምጥ ሲናገር አባይ፣
ዓለም ስትናውዝ በሌት በጸሐይ፡፡
የኢትየጵያውያን ህይወት ያሳስባል፣
ሁሉም የሰው ልጆች ህይወት ያሳስባል!
እውነት ተናገሩ ምንድን ነው ነገሩ?
እስቲማ ንገሩኝ ምንድን ነው ነገሩ?
ወገኖቼ አኩርፈው ጠፍተዋል ካገሩ፣
የእውነትን መድኃኒት ሄደው ሊቀምሩ፣
ተመልሰው መጥተው ሀገርን ሊያኮሩ፡፡
ወያኔ ጨካኝ ነው የሞራል ኪሳራ፣
እሱ በመደንገጥ ህዝብን የሚያስፈራ፣
ቀኙን ያዘው ሲሉት የሚመርጥ ግራ፣
ብዕርን ሲያሳዩት የሚመዝ ካራ፣
ጣፋጩን ሲያሳዩት የሚመኝ መራራ፣
የጽድቅ በር ትቶ ጋነም የሚያጓራ፡፡
አሸባሪ አውሬነት ስብዕና የሌለው፣
ኃላፊነት የለሽ ምግባር የጎደለው፣
የደቡብ አፍሪካው ወሮበላው ሌባው፣
የሊቢያው አጋንንት በደም ላይ የዋኘው
የሳውዲው መናጢ ውቃቢ የራቀው፣
እንዴት ሆኖ ይሆን ከህሊና እሚያድረው?
የዲያስፖራው አቅምየለሽነት፣
በኢትዮጵያዊነት ትብበር እጦት፣
በሰው ልጆች ጭራቅነት፣
በሰው ልጆች ኢሰብአዊነት፣
ይንጸባረቃል በዋናነት፣
ሁሌም ያሳስባል የኢትዮጵያዊ ህይወት፡፡
ወያኔ ወገኑን ኬሬዳሽ ብሎታል፣
ቢፈለጥ ቢቆረጥ ዓይኑን ሸፍኖታል፣
ቢሰደድ ቢሰቀል አላይም ብሎታል፣
የኢትዮጵያውያን ህይወት አልሰምር ብሎታል፡፡
ለምንወዳት ሀገራችን ለኢትዮጵያችን እጮሃለሁ፣ ሆኖም ግን ከዋሻው መጨረሻ ብርሀን አለ
የኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች በሳውዲ አረቢያ ስቃይ እና መከራ እየደረሰባቸው በነበረበት ጊዜ አድኃኖም እንዲህ ብሎ ነበር፣ “ከዋሻው መጨረሻ ብርሀን አለ፣ እናም ድህነትን ማጥፋት እንደምንችል እንደምናጠፋ እናውቃለን፡፡“
እኔም እንደዚሁ በኢትዮጵያ በስልጣን እርካብ ላይ ከህዝብ ፈቃድ ውጭ ተፈናጥጠው ከሚገኙት ጨካኞች እና አምባገነኖች መጨረሻ ብርሀን አለ እላለሁ፡፡ ከአድማሱ ባሻገር አዲስ ቀን አለ፡፡ አንድ መሆን አለብን፣ ክርስቲያን እና ሙስሊም ሳንል ሁላችንም በሀገሪቱ ውስጥ ያለን ሁላችንም ኢትዮጵያውያን/ት ሁሉ እጅ ለእጅ ተያይዘን በአንድነት መጓዝ አለብን፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን በዋሻው ውስጥ በቀጥታ በመጓዝ ለሁለት አስርት ዓመታት እና ከዚያ በላይ በጭቆና እና መሰረታዊ የሰብአዊ መብቶችን ተነጥቀን ከቆየንበት ዋሻ ውስጥ በጥሰን እና በጣጥሰን በድል አድራጊነት ብርሀን ከሚታይበት ጫፍ ብቅ ማለት አለብን፡፡
እውነታውን መናገር አለብኝ፡፡ በጣም አስቸጋሪ ነገር ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ተስፋ እቆርጣለሁ፣ እናም ለምንወዳት ኢትዮጵያችን አለቅሳለሁ፡፡ ይህንን በጽናት አደርጋለሁ፡፡ ምን ያህል እንደማደርግ ብታውቁልኝ? እ.ኤ.አ. በ1948 በዚያው ዓመት አፓርታይድ በደቡብ አፍሪካ እራሱ ህግ መሆኑን በማስመልከት አላን ፓቶን እንዲህ በማለት ጻፉ፣ “ለውዲቷ ሀገራችን እንጩህ“ በማለት በደቡብ አፍሪካ ዕጣ ፈንታ ላይ ጥልቅ የሆነ የተስፋ ማጣት ስሜታቸውን ገልጸው ነበር፡፡ የእኔ የግሌ በኢትዮጵያ ላይ ተስፋ የማጣት ስሜቴ ከፓቶን ስሜት ጋር ጎን ለጎን በመሄድ እንዲህ በማለት ያስተጋባል፡
…የኮሶ መታሪ እንደገባው የኮሶ ትል ስለተበጣጠሰው የጎሳ ክፍፍል፣ መቅኖውን ስላጣው የህግ ስርዓት እና እንደ አሮጌ ቁና ወደ ጎን ስለተሽቀነጠረው ብርቅዬ ባህላችን እና ልማዳችን እጮሀለሁ፡፡ አዎ፣ ስለሞተው ወንድ፣ ስለሞተችዋ ሴት እና በሞት ስለተነጠቁት ልጆች እጮሀለሁ፡፡ ስለውዲቱ ሀገሬ እጮሃለሁ፡፡ እነዚህ ነገሮች ሁሉ በመጨረሻው የውድቀት ምዕራፍ ላይ አይደሉም፡፡ ጸሐይ ሁሉም ሰው ተደስቶ ሊኖርባት ባልቻለባት በመሬት ላይ መሀለቋን ላይ ትጥላለች፡፡ ሰው የሚያውቀው የልቡን ፍርሀት ብቻ ነው፡፡
እኔም እንደ ፓቶን ሁሉ በኢትዮጵያ የጎሳ ክልል እየተባሉ ተበጣጥሰው ላሉት ጎሳዎች እጮሀለሁ፡፡
ለዚህ መቅኖውን አጥቶ ለበከተው እና ለተዋረደው የፍትህ ስርዓት እና እንደ አሮጌ ቁና ለተሽቀነጠረው አኩሪ ባህላችን እና ልማዳችን ድምጼን ከፍ አድርጌ እጮሀለሁ፡፡ ጨርቅ ነው እያሉ በአደባባይ ላዋረዱት ለኢትዮጵያ ባንዲራ ድምጼን ከፍ አድርጌ እጮሀለሁ፡፡ የኢትዮጵያ ታሪክ የመቶ ዓመት እድሜ ብቻ ነው በማለት በድንቁርናቸው ለገደቡት እና በህዝብ በተሳለቁት ደምጼን ጮክ አድርጌ እጮሀለሁ፡፡ ኢትዮጵያ የ100 ዓመት ገደማ ያህል ህልውና ያላት ሀገር ናት ብለው ለተዘባበቱት ድምጼን ከፍ አድርጌ እጮሀላሁ፡፡
ለወንዞች እና ድምጻቸው ለተገደበው ድምጽ የለሾች ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡ ለተራሮች፣ ለሸለቆዎች እና ለበረሀዎች ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡ ወርቋን እና የከርሰ ምድር ማዕድኗን ተነጥቃ ለምትደማው ሀገሬ ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡
በጭራቃዊ አሸባሪ ቡድን አንገታቸውን እየተቀሉ በግፍ እንዲያልቁ ለተደረጉት ለ30 የኢትዮጵያ ወጣት ክርስቲያን ወንዶች ወገኖቼ ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡ ለእነዚህ ወጣቶች አባቶች እናቶች፣ ለእህቶቻቸው እና ለወንድሞቻቸው ለአጎቶቻቸው እና ለአክስቶቻቸው እንዲሁም ለአያቶቻቸው ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡ ለጓደኞቻቸው እና ለጎረቤቶቻቸው፣ ለከተሞቻቸው እና ለመናገሻ መዲናቸው ድምጼን ከፍ በማድረግ እጨሀለሁ፡፡ ለውዲቱ ሀገራቸው እና ለኢትዮጵያ አለቅሳለሁ፡፡ እነዚህ ነገሮች እስከመጨረሻው ለመውደም በመጨረሻው እረድፍ ላይ አይደሉም፡፡ ጸሐይ በአሁኑ ጊዜ በጣም ጥቂቶች ብቻ እየተደሰቱ በሚኖሩባት መሬት ላይ ለ13 ወራት ያህል የሚዘልቀውን መሀለቋን በኢትዮጵያ ምድር ላይ ትጥላለች፡፡ ፍርሀታቸውን በልባቸው ውስጥ ብቻ ለሚያውቁት ወገኖቼ ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡ የወገኖቼን ስቃይ እና መከራ እንዲሁም የሚደርስባቸውን መንገላታት እና መሪር ሀዘን ሁሉ እጋራለሁ፡፡
እንደ በግ ጠቦት ጸጥ ያሉትን እና በሊቢያ አረመኔ ጨካኝ እና ገዳይ ወሮበሎች ለታረዱት ወጣት ወንድሞቼ ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡ ከእግዚአብሔር በቀር ምንም ዓይነት ሊረዳቸው የሚችል ኃይል በሌለበት በሊቢያ ምድር ላይ በወጥመድ ውስጥ ተይዘው በመቁለጭለጭ ላይ ላሉት ወገኖቼ ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡ በመካከለኛው ምስራቅ አስገድዶ መድፈር በሚፈጸምባቸው፣ በሚደበደቡት እና ከታላቅ ህንጻ ላይ በመስኮት እየተወረወሩ ለሚሞቱት፣ ከጣራ እና ከዛፍ ላይ ለሚሰቀሉት፣ የፈላ ውኃ በላያቸው ላይ ለሚደፋባቸው ወጣት እህቶቻችን ድምጻችንን ከፍ አድርገን እንጮሀለን፡፡ ተወልደው ያደጉበትን እና እትብታቸው የተቀበረበትን ሀገራቸውን በግዳጅ እንዲለቁ እና ለስደት በመዳረግ ነጻነት እንዳይሰማቸው፣ መብት ያላቸው ለመሆናቸው ምንም ዓይነት ስሜት እንዳይኖራቸው በገዛ ሀገራቸው ምንም ዓይነት የሰብአዊ ፍጡር ስሜትነት እንዳይሰማቸው በማድረግ ለከፍተኛ አደጋ እንዲጋለጡ ለሚደረጉ ወጣት ወንዶች እና ሴቶች ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡ በገዛ ሀገራቸው 3ኛ እና 4ኛ ደረጃ ዜግነት እንዳለ ያውቃሉ፡፡ ኑሯቸውን እና ህይወታቸውን ለማሻሻል በማሰብ የየመንን፣ የሊቢያን እና የሳውዲ አረቢያን በረሀዎች ሲያቋርጡ በሞት ለተነጠቁት እና አሁንም በመሞት ላይ ለሚገኙት ኢትዮጵያውያን/ት ወገኖች ድምጻችንን ከፍ በማድረግ እንጮሀለን፡፡ እ.ኤ.አ የ2005 ሀገር አቀፍ ምርጫ ከተጠናቀቀ በኋላ በመለስ ዜናዊ እና በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ጭካኔ እና አረመኒያዊነትን በተላበሰ መልኩ   በአዲስ አበባ መንገዶች በጠራራ ጸሐይ በአደባባይ ህይወታቸውን ላጡ ወጣት ወንዶች፣ ወጣት ሴቶች፣ አባቶች እና አባቶች ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡
ለእህቴ ለርዕዮት ዓለሙ፣ ለወንድሞቼ ለእስክንድር ነጋ፣ ለአንዷለም አራጌ፣ ለውብሸት ታዬ፣ ለበቀለ ገርባ፣ ለአቡባከር አህመድ እና ለሌሎችም በሺዎች ለሚቆጠሩት ለኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኞች ሁሉ ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮሀለሁ፡፡ ለኢትዮጵያውያን እና ለኢትዮጵያ ድምጼን ከፍ በማድረግ እጮለሁ፡፡
ተስፋ በማጣት በማሰማው ጩኸት እንዲህ የሚሉትን የሸክስፒርን የግጥም ስንኞች አረፍ በማለት አንጸባርቃለሁ፡
ዕድል እጣ ፈንታ በጨለመ ጊዜ፣
አላንቀሳቅስ ሲል የያዘን አባዜ፣
ከወንዶች ዓይን ላይ በተነነ ጊዜ፣
ሁሉም አይሳካም አይኖርም ኑዛዜ፡፡
በተተፋው መንግስት ሁልጊዜ እጮሀለሁ፣
ግራ ተጋብቼ ቀኙን አጥቻለሁ፣
ወደላይ ከመሄድ ቁልቁል እወርዳለሁ፣
አንድነቱን ትቼ ነጠላ ሆኛለሁ፣
ፍቅርን በመተው ጥላቻን ይዣለሁ፣
በህይወት ከመኖር ሞትን መርጫለሁ፣
በሀገር ከመኖር ባድን አምልኪያለሁ፣
ዘረኛን ከማጥፋት ሀሜት ለምጃለሁ፣
በዚሁ ከቀጠልኩ ጋነም እገባለሁ፡፡
የጻዲቁን መንገድ ተረተሩን ስቼ፣
እውነትን በመፍራት ለሀሰት ሞግቼ፣
ቀረሁ ባደባባይ ለፍቼ ለፍቼ፣
ባልተሳካው ጩኸት ከጋነም ገብቼ፡፡
ጆሮው በማይሰማ በዲያብሎሱ ቤት፣
በጠራራ ጸሐይ ስመላለስበት፣
እዩኝ ተመልከቱኝ ለዚህ ብኩንነት፣
ወገን አንድ በሉ ወገን ላለቀበት፡፡
 ቃል ኪዳን ግቡልኝ ለመልካም ዕድል፣
ፈዋሽ አቅርቡልኝ አምጡልኝ ጸበል፣
አማልዱኝ ካምላኬ ከኃያሉ ገድል፣
ተስፋዬ ለምልሞ እንድኖር በድል…
አዎ፣ ደግሜ ደጋግሜ በመጮህ ይህንን የማይሰማ መንግስተ ሰማያት ስኬታማ ባልሆኑት ጩኸቶቼ መግቢያ ቀዳዳ በማሳጣት አስቸግረዋለሁ፡፡ አዎ፣ በእኔ ተስፋ መቁረጥ አንድ ተጨማሪ ተስፋ እቋጥራለሁ፡፡ ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ከወሮበሎች አገዛዝ ነጻ ትሆናለች፡፡ ህዝቧ የእነዚህን የአጭበርባሪዎች እና ሸፍጠኞችን ተንኮል በመገንዘብ በአንድ ላይ እጅ ለእጅ በመያያዝ አንድ ላይ ሆኖ በመቻቻል፣ በስምምነት እና በፍቅር ላይ የተመሰረተች ኢትዮጵያን እንደሚገነባ ሙሉ ተስፋ አለኝ፡፡ ተስፋ አደርጋለሁ ምክንያቱም ተስፋየለሽነትን አስወግጃለሁ፡፡
ለውዲቷ ሀገራችን እጮሃለሁ፡፡ በደስታ እና በተስፋ እጮሀለሁ፡፡ ጩኸታችን ይሰማል የሚል ቃል ኪዳን እገባለሁ፡፡ ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ የጭካኔ አምባገነናዊ የዘረኝነት አገዛዝ ዋሻ ውስጥ አልወጣችምን? ማንዴላ እንዲህ ሲሉ አንድ ሌላ ተጨማሪ ተስፋን አልሰነቁምን?፡ “በፍጹም በፍጹም ከእንግዲህ ወዲያ በዚህ ቆንጆ መሬት አንዱ በአንዱ ላይ የሚጨቆንበት እና የሚሰቃይበት የተዋረደች ዓለም አትኖርም፡፡“
በፍጹም አትጠራጠሩ፡፡ እኔ የበለጠ በተስፋ የተሞላሁ፣ ከምንጊዜውም በላይ በደስታ የፈነጠዝሁ እንደሆንኩ እዘልቃለሁ፡፡ ኢትዮጵያውያን/ት በቅርብ ጊዜ ውስጥ የነበራቸውን ክብር እና ሞገስ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ እንደገና እንደሚቀዳጁ ምንም ዓይነት ጥርጥር የለኝም፡፡
ኢትዮጵያውያን/ት በክልል አገዛዝ እንደ ደቡብ አፍሪካውያን የአፓርታይድ የዘረኝነት አገዛዝ የዓለም የውርደት ቋት ውስጥ በፍጹም አትገባም፣ እናም ይህንን ከልብ በሆነ መልኩ አምናለሁ፡፡ ኢትዮጵያ እጆቿን በቅርብ ጊዜ ውሰጥ ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች፣ እናም በደስታ ምንም ዓይነት ጩኸት እና ጫጫታ ሳይኖር በደስታ እና በፈንጠዝያ እንኖራለን የሚል እምነት አለኝ!
የማየሳነው እና ዘላለማዊው አምላክ እግዚአብሔር በሊቢያ የወደቁትን የወንድሞቻችንን እና የልጆቻችንን ነብስ ይማርልን፣ በገነት ያኑርልን!
አላህ ምህረት ሰጭው እና መልካም አድራጊው ለእኛ ወንድሞች እና ልጆች ምንም ዓይነት ምህረት ላላደረጉት ወገኖች ምህረቱን እና ጽናቱን ስጣቸው!
ተከብረሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም
እናት ኢትዮጵያያ ያስደፈረሽ ይውደም!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ሚያዝያ 26 ቀን 2007 .