Saturday 22 February 2014

የመከላከያ ተቋም ተግባር አገርን መጠበቅ ነዉ ወይስ አገርን መዝረፍ?



Ginbot 7 weekly editorialየአዉሮፓ ቅኝ ገዢዎች አፍሪካን ሲቀራመቱ ባህር ተሻግረዉ በመጡ የነጭ ባዕዳን ኃይሎች መገዛትን መርጦ የአዉሮፓን ወራሪዎች በሰላም በሩን ከፍቶ ወደ አገሩ ያስገባ እንድም የአፍሪካ አገር አልነበረም፤ የኋላ ኋላ ተሸንፈዉ በቅኝ አገዛዝ ቀንበር ስር ቢወድቁም ሁሉም የአፍሪካ አገሮች እንደ አቅማቸዉ ከወራሪ ኃይሎች ጋር ተፋልመዋል። በአንድ ወቅት የቅርብ ጎረቤቶቻችንን ጨምሮ ብዙዎቹ የአፍሪካ አገሮች በወራሪ ኃይሎች ተሸንፈዉ የቅኝ ገዢዎች ቀንበር ጀርባቸዉ ላይ ሲጫን አገራችን ኢትዮጵያ ብቻዋን የአለም ጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌት ሆና የኖረችዉ ጣሊያኖች፤ እንንግሊዞችና ፈረንሳዮች ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች ለይተዉ ስለወደዷት ወይም ስላከበሯት አይደለም። ይልቁንም ነፃነታችንና የግዛት አንድነታችን ተከብሮ የኖረዉ ኢትዮጵያ እናት አገሩ በጠላት ስትደፈር ከሚያይ ምትክ የሌላት ህይወቱ ብታልፍ ደስ የሚለዉ የኩሩና የጀግና ህዝብ አገር በመሆኗ ነዉ። የሚገርመዉ ይህ ኩሩና ጀግና ህዝብ ጣሊያንን የመሰለ በዘመናዊ መሳሪያ የታጀበ ኃይል ዉርደቱን ተከናንቦ ወደመጣበት እንዲመለስ ሲያስገድድ እንደ ዛሬዉ የተደራጀ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት አልነበረዉም። ዛሬ አራት ኪሎና ስድስት ኪሎ ላይ የተተከሉት ሁለቱ ታሪካዊ ሀዉልቶቻችን የሚነግሩንም ይሀንኑ የኢትዮጵያ ህዝብ በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ሠራዊት ሳይኖረዉ የጎበዝ አለቃ እየመረጠ በጣሊያን ፋሺስቶች ላይ የተጎናጸፈዉን አኩሪ ድል ነዉ።
ኢትዮጵያ ዉስጥ ዘመናዊና የተደራጀ መከላከያ ሠራዊት ጥንስስ የተጣለዉ በዳግማዊ ሚኒልክ ዘመነ መንግስት ሲሆን እሱም ቢሆን ከአድዋ ድል በኋላ ቆይቶ የመጣ ክስተት ነዉ። በአፄ ኃ/ሥላሤና በደርግ ዘመነ መንግስት ኢትዮጵያ ለአንድ ፓርቲና ይህ ፓርቲ እወክለዋለሁ ለሚለዉ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ሙያዊ ብቃት የነበረዉ፤ሙያዉን የሚያከብርና ለአገሩና ለወገኑ ታማኝ የሆነ የመከላከያ ሠራዊት ነበራት። የወያኔ ዘረኞች አዲስ አበባን ሲቆጣጠሩ የመጀመሪያ ኢላማቸዉ አድርገዉ ካወደሟቸዉ ዋና ዋና የአገራቸን ተቋሞች ዉስጥ የመጀመሪያዉ ይሄዉ የአገርና የህዝብ ደጀን የነበረዉ ተቋም ነበር። ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ የአገር መከላከያ ሠራዊት እየተባለ የሚጠራዉ ተቋም ለጎጠኞች ጥቅምና የስልጣን መራዘም የቆመ፤ በዘረኝነት የተካፋፈለ፤ ይህ ነዉ ተብሎ የሚጠቀስ ሙያዊ ብቃት የሌለዉና የወገንና የአገር ፍቅር እንዳይኖረዉ ተደርጎ የተደራጀ ሰራዊት ነዉ። ይህንን ሠራዊት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሳይሆን የወያኔ ሠራዊት እያልን የምንጠራዉም በዚሁ ምክንያት ነዉ።
ዛሬ ሙሉ በሙሉ በወያኔ ዘረኞች ቁጥጥር ስር የወደቀዉ የአገር መከላከያ ተቋም የሚታማዉ በዘረኝነት፤ በሙያ ብቃት ማነስና የአንድ ፓርቲ ጥቅም አስከባሪ በመሆኑ ብቻ አይደለም፤ ተቋሙ ከእነዚህ ዋና ዋና ጉድለቶቹ በተጨማሪ በቀድሞዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ተቋም ላይ በፍጹም ያልታዩ ሌሎች ትላልቅ ጉድለቶች አሉበት። ከእነዚህ ጉድለቶች ዉስጥ አንዱ የወያኔ የመከላከያ ተቋም ህገ መንግስቱ ከሰጠዉ ኃላፊነት ዉጭ በንግድና በንብረት ይዞታ ላይ ላይ መሰማራቱ ሲሆን ሁለተኛዉ ደግሞ ከዚህ ፀባዩ ጋር ተያይዞ በመከላከያ ሠራዊት ተቋም ዉስጥ ከላይ እስከታች የሰፈነዉ ቅጥ ያጣ ሙሰኝነት ነዉ። ዛሬ የወያኔን የመከላከያ ተቋም፤ የህወሀትን ፓርቲና ኤፎርት በሚል ምህጻረቃል የሚታወቀዉን የወያኔን የገንዝብ ማምረቻ ድርጅት ነጣጥለን ወይም አንዱን ከሌላዉ ለይተን ማየት የማንችልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል።
በላፈዉ አመት ወያኔ እራሱ ያቋቋመዉ ፀረ ሙስና ኮሚሺን የገንዘብ ዝርፊያን፤የንብረት መባከንንና መዝረክረክን አስመልክቶ ለፓርላማዉ ባቀረበዉ ሪፖርት ላይ ከጠቀሳቸዉ መንግስታዊ ተቋሞች ዉስጥ ቀዳሚዉን ደረጃ የያዘዉ የመከላከያ ተቋም ነዉ። ሆኖም ፓርላማዉም ሆነ የወያኔ አገዛዝ ለዚህ ሪፖርት የሰጡት ምላሽ የመከላከያና የደህንነት ተቋሞች ከአሁን በኋላ ያሻቸዉን ያክል ገንዝብ ቢዘርፉ የሂሳብ መዝገባቸዉ “ለአገር ደህንነት” ሲባል በኦዲት ኮሚሺን አይመረመርም የሚል ምላሽ ነበር። እንግዲህ ይህ በሙሰኝነት የተጨማለቀ፤ ለህግ የማይገዛና መጠበቅና መንከባከብ የሚገባዉን የአገር ኃብትና ንብረት የሚዘርፍ ተቋም ነዉ ባለፈዉ ሳምንት “የመከላከያ ቀን” ተብሎ አመታዊ በዐል የተከበረለት።
መናገሻ ከተማችን አዲስ አበባ ዉስጥ በየቦታዉ የሚታዩትን ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች ሰርተዉ የሚያከራዩት የወር ደሞዛቸዉ ከ2500 ብር የማይበልጥ መከላከያ ሠራዊት ዉስጥ የተሰገሰጉ የወያኔ ጄኔራሎች ናቸዉ፤ኢትዮጵያ ዉስጥ ትርፋማ በሆኑ ቦታዎች ሁሉ ትላልቅ ሆቴሎች፤ የአገልግሎት ተቋሞችና የንግድ ድርጅቶች ከፍተዉ ቁጥር ስፍር የሌለዉ ኃብት የሚያጋብሱት የወያኔ ጄኔራሎች ናቸዉ፤ ድሃዉና የወያኔ ዘረኝነት ሰለባ የሆነዉ ኢትዮጵያ ሰራዊት ለተመድ ተልዕኮ በተሰማራባቸዉ ቦታዎች ሁሉ ተመድ የሚከፍለዉን የቀን አበል ኪሳቸዉ ዉስጥ እየከተቱ ሚሊዮነሮች የሆኑትና በየዉጭ አገሩ ዉድ መኖሪያ ቤቶችንና የንግድ ተቋሞችን የሚገዙት የወያኔ ጄኔራሎች ናቸዉ። የወያኔ መከላከያ ተቋም ጉድ በዚህ ብቻ አያበቃም፤ ይህንን ወንጀለኛ ተቋም ቃላት እየደረደሩ ለመግለጽ ከመሞከር ይልቅ በጥቅሉ ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ኃብትና ንብረት እንዳሻዉ መዝረፍ እንዲችል የኃይል ሽፋን የሚሰጥ ተቋም ነዉ ማለት የሚበቃ ይመስለናል።
ወያኔና ስር የሰደደዉ ዘረኛ ስርዐቱ ከኢትዮጵያ ምድር ላይ እስካልተነቀሉ ድረስ ወያኔ ዝርፊያዉን የወያኔ መከላከያ ተቋምም የወያኔንና የደገፊዎቹን ዝርፊያ በመሳሪያ ማጀቡ አይቆምም። የወያኔን ዝርፊያ ለማስቆምና አገራችንን ከተጋረጠባት አሳሳቢ አደጋ ለመታደግ ብቸኛዉ መንገድ ወያኔን ከሥልጣን ማስወገድ ብቻ ነዉ። ግንቦት 7 የፍትህ፤የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የጀመረዉ ህዝባዊ ትግል እንደ አገር መከላያከያ አይነቶቹ ቁልፍ የአገር ተቋሞች በሚሰሯቸዉ ስራዎች ሁሉ የአገርንና የህዝብን ጥቅም እንዲያስጠብቁ ለማድረግ ነዉ። የግንቦት 7 ትግል አላማ የመከላከያ፤ የደህንነት፤ የፖሊስና የፍትህ ተቋሞች የአንድ ፓርቲ ጥቅም ማስከበሪያ መሳሪያዎች መሆናቸዉ አብቅቶ የአገርና የህዝብ አለኝታ እንዲሆኑ ነዉ፤ ሆኖም ይህንን ቅዱስ አላማ ወያኔ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ ተግባራዊ ማድረግ ስለማይቻል ነፃነት፤ ፍትህ፤ዲሞክራሲ፤ ሠላምና እኩልነት የናፈቀዉ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ወያኔን በፍጥነት እናስወግድ ከሚለዉ የአገር አድን አላማ ጎን እንዲሰለፍ ግንቦት 7 የትግል ጥሪዉን ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!http://ecadforum.com/Amharic/archives/11144/

Friday 21 February 2014

አንድነት እና መኢአድ፤ በባዶ እግራቸው በመሆን በባህርዳር ቅስቀሳ እያደረጉ ነው።

andent ena mead
አንድነት እና መኢአድ፤ በባዶ እግራቸው በመሆን በባህርዳር ቅስቀሳ እያደረጉ ነው።
የአማራ ክልሉ ባለስልጣን፤ “አማራው በባዶ እግሩ ነው የሚሄደው…” ብለው እጅግ የከፋ ዘለፋ ካሰሙ ብኋላ ህዝቡ በያለበት ስለ ሰውዬው ያፈረላቸው ቢሆንም እርሳቸው ግን ሳያፍሩ ትላንት በቴሌቪዥን መስኮት ተከስተው ሲያስቁን ነበር።
ዛሬ እንደሰማነው እና እንዳየነው፤ የመኢአድ እና አንድነት አባላት እሁድ ለጠሩት ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ፤ በባዶ እግራቸው በመሆን ባደረጉት ቅስቀሳ “እኛም ጫማ የለንም፤ እኛም በባዶ እግራችን ነው የምንሄደው ቢሆንም ግን የሞራል ለዕልና አለን” የሚል ቅስቀሳ ሲያሰሙ ውለዋል።
በቅስቅሳው ወቅት ፖሊስ ጉልቤውን ሊያሳያቸው ቢሞክርም ህዝቡ ከበባ እያደረገ ሲከላከላቸው አንድነት ዛሬ ከለቀቀው ቪዲዮ አይተናል።
ድረ ገጻችን፤
…የምር ግን ህዘብ እየተዘለፈም እየተዘረፈም እንዴት ይችለዋል…. ???ብላ በትልቁ እየጠየቀች፤ አንድነት ያሰራጨውን ቪዲዮ ላላዩት እንደሚከተለው ታሳያለች።

“የረዳት አብራሪ ኃይለመድን እህት ታስራለች፣ ቤተሰቦቹ በግዳጅ ሊናገሩ ነው”

Tensay Abera (Co-pilot Hailemedhin's sister)
Tensay Abera (Co-pilot Hailemedhin’s sister)
ቦይንግ 767-300 ጄኔቭ አርፎ፣ መንገደኞቹ ወደየመድረሻቸው ተጉዘው አውሮፕላኑም ወደ ሀገሩ ተመልሷል። ነገር ግን የወሬው በረራ ማረፊያ ቦታ እንዳጣ ነው። የኃይለመድን ጉዳይ በየቦታው የመወያያ ርዕስ እንደሆነ ነው፣ ይቀጥላልም። የግምት ወሬዎች እዚህም-እዚያም እየተረጩ ነው። በተለይ የመንግስት ካድሬዎችን “ቢዚ” አድርጓቸዋል። በምን መልኩ የድራማውን ድርሰት እንደሚጽፉ ግራ ግብት ብሏቸዋል የአዕምሮ ሕመምተኛ ሊሉት ፈለጉ …ከዚያ ትዝ ሲላቸው አዕምሮ ታማሚ ሆኖ አየር መንገዱ መንግስት እንዴት እንዲያበር ፈቀደ፣ ለአብራሪዎቹ ምርመራ አያደርግም ወይ የሚሉት ጥያቄዎች ሊከተሉ ሆነ። ቀጥለው አባትዬው እቁብ ሰብሳቢ፣ አራጣ አበዳሪ… ተደርገው ተሳሉ። እእ..ደራሲዎቹ የቤተሰብ ጣጣ መሪ ተዋናዩ ላይ የሚፈጥረው ተጽዕኖ አልታይ አላቸው። የኃይለመድን እህት ሆነው የተዋቀረ እና የተዋቃ ጽሑፍ በፌስቡክ ላይ አከታተለው ጻፉ…በርግጥ ይሄኛው የወጭ የዜና አውታሮች ዘንድ ደርሶላቸው ተራግቦላቸዋል። ተአማኒነት ባያገኝም።
በነዚህ መጨበጫ በሌላቸው ወሬዎቹ አንድ ሊገባን የሚችል ነገር ቢኖር ካድሬዎቹ ደራሲዎች የአበራሪው ስም እና ስብዕና በአሉታዊ ጎኑ ብቻ እንዲነሳ መፈለጋቸው ነው። ከአየር መንገዱ ይልቅ የመንግስታቸው ህልውና እንቅልፍ ነስቷቸዋል። ምክንያቱም ኃይለመድን የጠየቀው የፖለቲካ ጥገኝነት ነው፣ ዝርዝር ባይኖረውም ይቺ ቃል የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ስቧል። የHuman Rights Watch ዳይሬክተር ሌስሊ ሌፍኮው ስለክስተቱ ተጠይቀው የኢህአዴግ አምባገነናዊ እና ኢ-ሰብአዊነት የትኛውንም ዜጋ የሚያሰድድ እንደሆነ ሳያመነቱ ተናግረዋል። የእንግሊዙ Telegraphም በመረጃ አስደግፎ “ኢትዮጵያውን ያላማቋረጥ የሚፈልሱት በድኅነት እና በጭቆና ነው” ሲል ቁልጭ አደርጎ አስቀምጦታል። እና እንደዚህ ያሉ የኢህአዴግ መታወቂያዎች ከሀገሬው አልፈው ለተቀረው ዓለም እየደረሱ መሆናቸው ካድሬዎቹን አሰበርግጓቸዋል። አውሬ ደግሞ ሲበረግግ የሚያደርገውን አያውቅም።
አሁን የልጁን ቤተሰቦች አስገድደው እንደለመድነው ETV ላይ ድራማ ሊያሰሯቸው እንደሆነ መረጃዎች እየወጡ ነው። “ፌስቡኬ በሌሎች ሰዎች ጥቅም ላይ ውሏል” ያለችው እህቱም በእስር ላይ እንደምትገኝ ተሰምቷል።
እስኪ የሚያስብሏቸውን እንስማ መቼም ምንም ቢቧጥጡ እውነታዋ ያለችው ረዳት አብራሪ ኃይለመድን ጋ’ ስለሆነ ሊያጠፏት አይቻላቸውም። እኛም እሱ እስኪናገር ከይሆን-ይሆናል አሉባልታዎች ተቆጥበን በድርጊቱ መፈጸም በፊት ባንዲራችንን ተሸክሞ ከአድማስ አድማስ አውሮፕላናችንን እያበረረ ሀገሩን ሲያገለግል ለቆየው ኋይለመድን የምንሰጠው ክብር ይቀጥል።

የብአዴን ድንጋጤና የእሁዱ የተቃውሞ ሰልፍ

ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የብአዴን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አለምነው መኮንን በአማራ ህዝብ ላይ የሰነዘሩትን ዘለፋ ተከትሎ የተነሳውን ተቃውሞ ለማብረድ የብአዴን የወጣቶች ሊግ ለአባለቱ የስልጠና እና የግምግማ ስራ በባህር ዳር ፤ ደሴ እና ጎንደር እያከናወነ ነው።
የካቲት 16 አንድነትና መኢአድ በጋራ የጠሩትን ሰልፍ ተከትሎ በባህር ዳር ከተማ ባሉ ዘጠኝ ክፍለ ከተሞች 12 የገጠር ቀበሌዎች ብአዴን አባላቱ እና አባል ያልሆኑ ወጣቶችን በግዳጅ በማስጠራት ባቀረበው የውይይት ሃሳብ እና መመሪያ በማህበራዊ ድረ ገፆች በሚተላለፉ ሃሰተኛ መረጃዎች ማንም ተወናብዶ ሰልፉን መቀላቀል እንደሌለበት አሳስቧል።
የጥፋት ሃይሎች የሚያስወሩት ሴራ ነው የሚለው ብአዴን፣ ሰልፉን ለማጨናገፍ ና ማህበረሰቡ በሰልፉ ላይ እንዳይገኝ ወጣቶች አስፈላጊውን ስራ መስራት እንዳለባቸው መክሯል።
የባህር ዳር ከተማ ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት ሃላፊ ወጣት ጌታቸው ብርሃኑ ባቀረበው ጽሁፍ የተሳሳቱ መረጃዎችን በማምጣት ህዝብ እና መንግስትን የማለያየት ስራ እየሰሩ በማለት ለወጣቶች ተናግሯል፡፡
የብአዴን ጽ/ቤ ሃላፊ የሆኑት አቶ እሱባለው መሰለ በበኩላቸው “የማህበራዊ ድህረ ገጾችን አትመልከቱ ችግር አለባቸው የሚያስተምሩት ጥላቻ እና አመጽን ነው” በማለት ምክራቸውን ለግሰዋል።
“በማህበራዊ ድረ ገፆች በሚተላለፉ ሃሰተኛ መረጃዎች አንታለልም” የሚል መሪ ቃል ይዞ እየተከናወነ ያለው ይህ ስልጠና ፣ ኢሳትንና ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ማእከል አድርጎ የሚካሄድ ነው።
አንዳንድ ተሰብሳቢዎች ” በድምጽ የሰማነውን ጉዳይ አይን ባወጣ ውሸት እንዴት ይክዱናል” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የአቶ አለምነውን ንግግር ሳያስተባብሉ ” የብአዴን የወጣት ሊግ እና ታች ያሉ አመራሮች ወጣቱን ለማሳሳት መመኮራቸው ብዙ ተሰብሳቢዎችን አስደምሟል።”
አንዳንድ ወጣቶች ” መረጃውን ለምን ማህበራዊ ሚዲያ እና ኢሳት አቀረበው ብሎ ከመጥላት ለምን አቶ አለምነው ከ22 ሚልየን በላይ የሚሆነውን ህዝብ ተሳደበ ብሎ” ውይይት አይከፈትም ነበር ሲሉ ተደምጠዋል። ብአዴን ከህዝብ ይልቅ ግለሰብ ይበልጥብኛል በማለት ጉዳዩን እየሸፋፈነው ነው በማለት አንዳንድ አባሎቹ ለዘጋቢያችን ነግረዋታል። የጎንደር መሬት ለሱዳን ተቆርሶ መሰጠቱን በተመለከተም ኢህአዴግ ተቃዋሚዎችን በመሳደብ ስታራቴጅ ችግሩን ለማድበስበስ እየሞከረ መሆኑን ወታጦች መናገራቸውን ሪፖርተራችን ከባህርዳር ዘግባለች።
አቶ አለምነው የአማራው ህዝበ የትምክህት ለሃጩን ማራገፍ አለበት በማለት መናገራቸው ይታወቃል
አንድነትና መኢአድ እሁድ ለሚካሄደው ተቃውሞ በባህርዳር ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ሲሆኑ፣ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ተቃውሞውን እንዲገልጽም ጠይቀዋል።

ሰበር ዜና፤ ወያኔ በውጭ የሚገኙ ተቃዋሚዎችና ጋዜጠኞች ላይ የሚያደርገው የስለላ ወንጀል ስለተጋለጠ አሜሪካ ውስጥ ክስ ተመሠረተበት

ዜናውን በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ።   ወያኔ በስለላ ወንጀል አሜሪካ ውስጥ ተከሰሰ
የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ለ22 ዓመታት የግድያ፣ የማሰቃየት፣ የማፈንና ሌሎችም ዘግናኝ ወንጀሎችን ሲፈጽም የኖረው ወያኔ “ተሸሽጎ የሚኖር ነገር የለም” እንደሚባለው አሜሪካ ውስጥ በሚገኘው የኢሳት ጋዜጠኞች ላይ ያካሂድ የነበረው የስለላ መረብ በመበጣጠሱና እጅ ከፍንጅ በመያዙ በዛሬው ዕለት ዋሽንግተን ከተማ ውስጥ በሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውስጥ ክስ እንደተመሠረተበት ታላቁ የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ አስታውቋል።
ክሱን የመሠረተው አሜሪካ ውስጥ ላለፉት 22 ዓመታት የኖረው ኢትዮጵያዊ አሜሪካዊ ግለሰብ ሲሆን የወያኔ አገዛዝ የአሜሪካን ህግ በመጣስ የስለላ መረቦችን በግልኮምፒውሩ ላይ በማስጠመድ ግለሰቡ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ሲከታተል እንደነበር ተመልክቷል። ይህ የተመሠረተው ክስ የቅርብ የአሜሪካን መንግስት ወዳጅና ተመጽዋች የሆነው የወያኔ አገዛዝ ተቃዋሚዎችን፣ጋዜጠኞችንና የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችን፣ የማፈን ታሪክ ያለው ከመሆኑም በላይ የተራቀቁ የድረገጽ መሳሪያዎችን በመጠቀም ጠላቶቼ የሚላቸውን ሲሰልል መገኘቱን ምልክት የሚሰጥ መሆኑ በጋዜጣው ውስጥ ተጠቁሟል።
ክሱን ያቀረበው “Electronic Frontier Foundation” በመባል የሚጠራው የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ጠበቃ የሆኑት ሚ/ር ኔት ካርዶዞ እንደገለጹት “የኢትዮጵያ መንግሥት የሚቻለውን ሁሉ በማድረግ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በተለይም ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ግንኙነት አላቸው የሚላቸውን እንደሚሰልል መረጋገጡን አስታውቀዋል። የወያኔ ወኪሎች ስለቀረበባቸው ክስ ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠይቀው የሰጡት መልስ የተለመደ ክህደታቸውንና ቅጥፈታቸውን ነው። የኮምፒውተር ተመራማሪዎች እንዳረጋገጡት የወያኔ አገዛዝ የአፈናና የስለላ ወንጀሎችን ከሚፈጽሙ አገሮች ተርታ ውስጥ ይገኛል።
ከአራት ወራት በፊት ነጻ የሆነው የጥናትና ምርምር ተቋም የወያኔ አገዛዝ “ፊን እስፓይ” በመባል የሚጠራ የጆሮጠቢ መረብ እንደሚጠቀም መረጃዎች መገኘታቸውን የሚያሳይ ዝርዝር ዘገባ አቅርበው ነበር። ቶሮንቶ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በሚገኝው ዓለም-አቀፍ ጉዳዮች ትምህርት ቤት የወያኔ አገዛዝ የስለላውን መረብ ብቸኛ ተጠቃሚ መሆኑን አርጋግጠዋል። ይህ ሪፖርት ከወጣና ዜናው ከፍተኛ ሽፋን ከተሰጠው ከ5 ቀናቶች በኋላ የወያኔ አገዛዝ መጋለጡን በማወቅ ያካሂድ የነበረውን የስለላ መረብ ማቋረጡ ታውቋል። ሆኖም የወያኔ የስለላ  መረብ ባላሟሎች እንዳይያዙ መረጃዎችን ለማጥፋት ከፍተኛ ርብርቦሽ ቢያደርጉም ሙሉ በሙሉ አሻራቸውን ለማጥፋት ሳይችሉ በመቅረታቸው እጅ ከፍንጅ ሊያሲዝቸው የሚችል መረጃ ተገኝቶባቸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ወያኔ እንግሊዝ አገር ውስጥም በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የፖለቲካ ስደተኞች ላይ የሚያደርገው ስለላ ስለተደረሰበት ተጨማሪም ክስ ተመስርቶበታል። ከዚህ ለማጠቃለል የሚቻለው ወያኔ የአሜሪካን ህግ በመጣስ አማሪካ መሬት ላይ የፈጸመው ወንጀል ከአሜሪካ መንግስት ጋር ያለውን ግንኙነት በእጅጉ እንደሚያበላሽበት አይጠረጠርም። የዚህ ወንጀል መፈጸም መጋለጥና ክስ መመስረት ለወያኔ አገዛዝ ድጋፍ የሚሰጡ የአሜሪካን ባለሥልጣኖችንም ጭምር በወያኔ ድፍረትና ጥጋብ በአገራቸው ምድር ላይ ወንጀል መፈጸሙ በእጅጉ እንደሚያበሳጫቸውና እንደሚያስቆጫቸው እንዲሁም “ያሳደኩት ውሻ ነከሰኝ” እንደሚያስብላቸው ይገመታል። በአጠቃላይ ወያኔ ይህንን የስለላ ወንጀል ሲፈጽም እጅ ከፍንጅ መያዙ እንደ መንግስት ሳይሆን ወንበዴነቱን፣ሌብነቱን፣ማጅራት መቺነቱንና ኪስ አውላቂነቱን በዓለም-አቀፍ ደረጃ ያሳየና እርቃኑን ያስቀረው መሆኑን ለመገመት አያዳግትም። ከዚህም በተጨማሪ ወያኔ ከደደቢት ዋሻ ውንብድናውን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ በርካታ ደረቅ ወንጀሎችን ለምሳሌም ባንኮችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ የመንግስት መስሪያ ቤቶችን፣ ቤተክርስቲያኖችን፣ የግለሰቦችን መኖሪያ ቤቶችን፣ ሱቆችንና ሌሎች የኢትዮጵያውያንን ንብረቶችን መዝረፍ፣ ሀኪም ቤት የተኙ በሽተኞችን ከአልጋቸው አውርዶ መሬት ላይ በመጣል አልጋቸውን መዝረፍ፤ ሌሎችንም ወንጀሎች ሲፈጽም መኖሩና ብሔራዊ ባንክ የተቀመጠውን ወርቅ በምትሃት ወደ ቦንዳነት የለወጠ መሆኑና በርካታ ኩንታል ቡና ወደ አቧራነት የቀየረ መሆኑ አይዘነጋም።

Thursday 20 February 2014

''ካፒቴን ኃይለ መድህን በአጎቱ ሚስጥራዊ ሞት ይሰጋ የነበረ ሰው ነበር።'' 'ስካይ ኒውስ ''በክፍልም ውስጥ ሆነ በሥራ ላይ 'ስማርት'የሆነ ልጅ ነበር'' አብሮት የተማረ እና የስራ ባልደረባው የነበረው ረ/አብራሪ ምስጢር ታዬ


ዛሬ የካቲት 12/2006 ዓም 'ስካይ ኒውስ' ስለረዳት አብራሪ ኃይለ መድህን ጉዳይ አጎቱ አቶ ዓለሙ አስማማው ለአሶሼትድ ፕሬስ  በስልክ የሰጡትን ቃለ መጠይቅ መሰረት አድርጎ እንዲህ ብሏል።
''ኢትዮጵያዊው ፓይለት በአጎቱ አሟሟት ጉዳይ ጥርጣሬ (ስጋት ነበረበት)''
''የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ መምህር የነበሩት ዶ/ር እምሩ ስዩም ከቤታቸው ወደ ሚያስተምሩበት የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ሲሄዱ ሞተው ተገኝተዋል''
''የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ድረ-ገፅም ይህንንኑ አረጋግጦ ረዳት ፕሮፌሰር አለሙ አስማማው ጃንዋሪ 1 ቀን በድንገት ማለፋቸውን ፅፏል።''
''ሰኞ እለት የኢትዮጵያ መንግስት ቃል አቀባይ አቶ ሬድዋን ካፒቴን ኃይለ መድህን ከእዚህ በፊት ምንም አይነት የተመዘገበበት የወንጀል ሪከርድ የለም ብለዋል'' የስካይ ኒውስ ዜና መጨረሻ።

ከእዚሁ ጋር ተያይዞ ኢሳት በትናንትና ምሽት የራድዮ ዘገባው በአሜሪካ ከምትኖር የቤተሰቡ አባል ጋር እና አብሮት ከተማረ እና ከሰራ በኢንዶኔዥያ በሥራ ላይ ከሚገኘው ረዳት አብራሪ ምስጢር ታዬ ጋር ስለ ካፒቴን ኃይለ መድህን ቃለ መጠይቅ አድርጎ ነበር።
በቃለመጠይቁ ላይ የቤተሰብ አባሉም ሆኑ የትምህርት ቤት እና የስራ ባልደረባው ቃል አንድ ነው።በጣም ጎበዝ እና ሃገሩን የሚወድ ሰው የነበረ መሆኑን ሁሉም አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም የተለያዩ ዘገባዎች ሰሞኑን ስለ ወጣቱ ካፒቴን ሲገልፁ-ኃይለ መድህን ጎበዝ፣ሃገሩን የሚወድ፣በአስራሁለተኛ ክፍል  የመልቀቅያ ፈተና ላይ በሙሉ ''ኤ'' በማምጣት ወደ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ገብቶ የኢንጅነሪንግ ትምህርት መማሩን እና በመጨረሻ ላይ የአብራሪነት ስልጠና ለመውሰድ ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደገባ፣ከሀገሩ ውጭ የመኖር አንዳች ፍላጎት እንደሌለው፣በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚፈፀመው ጭቆና ግን እረፍት የነሳው ኢትዮጵያዊ መሆኑ ተነግሯል።በኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሞዝ እስኬል መሰረት የአንድ ረዳት አብራሪ ደሞዝ ከ 27 ሺህ እስከ 30 ሺህ ብር እንደሚደርስ ዘገባዎች ያሳያሉ።

የዘገባው ምንጮች -

     ስካይ ኒውስ February 19/2014 እ ኤ አቆጣጠር  http://www.skynews.com.au/world/article.aspx?id=951493

    ኢሳት ራድዮ የካቲት 11/2006 ዓም  (February 18/2014)

ESAT Breaking News Feb 20, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Breaking News Feb 20, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

“ድምፁ የእኔ ነው ስድቡ ግን የእኔ አይደለም” አቶ አለምነው መኮንን

አቶ አልምነው“ድምፁ የእኔ ነው ስድቡ ግን የእኔ አይደለም” አቶ አለምነው መኮንን
አንድነት እና መኢአድ የተሳዳቢው ባለስልጣን አቶ አለምነው መኮንን እንጀራ እናት የሆነችውን ብአዴንን ለመቃውም እሁድ በባህር ዳር ሰልፍ መጥራታቸው እንደተስማ፤
እኒያ የአማራ ህዝብ ምንትስ ነው… ቅብርጥስ ነው… ብለው በሞቅታ ውስጥ ያለ ሰው እንኳ የማይሞክረውን የስድብ ውርጂብኝ “በመረጣቸው” ህዝብ ላይ ያወረዱት ሰውዬ፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ቀርበው። “ድምፁ የእኔ ነው ስድቡ ግን የእኔ አይደለም… ይህ የተደረገው በኮምፒውተር ቆርጦ ቀጥል ቴክኖሎጂ ነው…” ብለው መግለጫ ሰጥተዋል መባሉን ስሰማ ሮጬ ወደ ኢቲቪ ድረ ገጥ ሄጄ ያሉትን ለመስማት ሞከርኩ።
“ድምጹ የእኔ ነው…” የሚለው ከንግግራቸው ውስጥ ተቆርጦ ውጥቷል። “ተሳደበ ይሉኛል… እንዴት እሳደባለሁ… መራጮቼን… ወላጆቼን… ዘመዶቼን… ወገኖቼን… ምን በወጣኝ እና ምን ቆርጦኝ እሳደባለሁ…???” ብለው እኛኑ ሲጠይቁ የሚያሳየው ንግግራቸውን ግን ሰማሁት።
እንግዲያስ አቶ አለምነህ፤
አንደኛ የብዙሃኑም ጥያቄ ይሄው ነው… ይሄ ህዝብ ቅጥ ባጣ ድህነት እንዲኖር የተፈረደበት አንሶ ምን በድሎ ምን አጥፍቶ ይብጠለጠላል… ምን በወጣውስ ይሰደባል…???
ሁለትኛ አዩት አይደል መቁረጫ እና መቀጠያ ቴክኖሎጂው ያለው ኢቲቪ ቤት ነው…! በአደባባይ ተናግረው ዞር ከማለትዎ “ድምጹ የእኔ ነው” የሚለው የእምነት ቃልዎ ተስረዘልዎ!
ሶሰት… አራት…አምስት…. መቶ፤  ይሄንን ለሁሉም ኢህአዴጎች ንገሩልኝ፤
ወይ ልቦና ግዙ! ንስሃም ግቡ እና ተንበርከካችሁ ይሄን ህዝብ ይቅርታ ጠይቁ፤ ወይ ደግሞ “ማስተዳደሩን” ርግፍ አድርጋችሁ ትታችሁ ማደሪያችሁን ፈልጉ!

Tuesday 18 February 2014

ረዳት ፓይለቱ ለኢትዮጵያ ተላልፎ የማይሰጥባቸው 6 ምክንያቶች

ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)
ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን ተላልፎ ይሰጣል የሚል እምነት የለኝም።
አንደኛ፣ ኢትዮጵያ የሞት ቅጣትን ተግባራዊ የምታደርግ አገር ናት።
ሁለተኛ፣ ኢትዮጵያ በሰብአዊ መብት ጥሰት በአለም የምትታወቅ ናት።
ሶስተኛ፣ ኢትዮጵያና ስዊዘርላንድ ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ የመስጠት ስምምነት ( extradition treaty) የላቸውም::
አራተኛ፣አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶችና በአውሮፓ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዝም ብለው አይቀመጡም።
አምስተኛ፣ እንደሚባለው ጭንቀት ኖሮበት ድርጊቱን ከፈጸመም የበለጠ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመለስ ያደርገዋል። ምክንያቱም በስደተኝነት ህግ የአእምሮ ጭንቀት ያለባቸው ሰዎች ጥገኝነት ለማግኘት ከፍተኛ እድል አላቸውና።
ስድስት፣ የአእምሮ ጭንቀቱ መንስኤ የቅርብና ከአጎቱ ሞት ጋር በተያያዘ ከሆነ ደግሞ ጥገኝነት ለመጠየቅ ጉዳዩን ይበልጥ ያከብድለታል ምክንያቱም የአጎቱ ሞት መንስኤ እስካሁን እንቆቅልሽ እንደሆነ አለና። እህቱ የጻፈችውም ደብዳቤ የሃይለመድህንን ችግር ይበልጥ የሚያሳይ ነው ። “ጠላቶች እንዳሉ እንደሚያምን ፣ ስልኩን እንደጠለፉት እንደሚያስብ፤ በላፕቶፑ ካሜራ ሳይቀር ያዩኛል ብሎ ስለሚሰጋ ካሜራውን ሳይሸፍን እንደማይከፍት እንዲሁም፤ ወጥቶ እስኪገባ ቤቱን ሲበረብሩ የቆዩ ስለሚመስለው ካሜራ ጠምዶ መሄድ ” መጀመሩን መግለጿ፣ የሃይለመድህ መሰረታዊ ችግር የደህንነት ዋስትና ማጣት መሆኑ በአገሪቱ ውስጥ ያለውን የደህንነት እጦት (insecurity) የሚያሳይ ነው። በቤተሰቡ በተለይም በአባቱ ላይ ተከፍቶ የነበረው የማጥፋት ዘመቻም ለጭንቀቱ መንስኤ ሊሆን ይችላል።
የሃይለመድህን ድርጊት ባለሁለት ሰይፍ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት በሁለቱም ሰይፍ መቆረጡ አይቀርም። ፓይለቱን የአእምሮ በሽተኛ አድርጎ ቢያቀርበው፣ ለአየር መንገዱ ትልቅ ኪሳራ ነው። መንገደኞች ከእንግዲህ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመጓዝ ድፍረቱ አይኖራቸውም፣ ለዚህም ይመስለኛል አቶ ሬድዋን ፓይለቱ ሙሉ ጤነኛ ነው ሲሉ መግለጫ የሰጡት። ወጣቱ ለስደት መጠየቂያ በማሰብ የወሰደው እርምጃ ነው ቢሉም፣ ” በደህና የኑሮ ሁኔታ ላይ የሚገኝ ሰው እንዴት ስደትን ሊመርጥ ቻለ?”፣ ከስደት የከፋ ችግር ቢያጋጥመው ነው ተብሎ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች አያያዝ መነሳቱ አይቀሬ ነው። መንግስት ግራ ሲጋባ ይታየኛል

የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ዕልቂት

ያዩ እንደሚሉት በርግጥም ዘግናኝ ነዉ።የሰዉ አንገት በገጀራ ይቀነጠሳል።እጅ፥ እግር፥ በጎራዴ ይቆረጣል።ሌላ አካል በጩቤ ይጨቀጨቃል። መንገዶች በደም አበላ ጨቅይተዋል-እየጨቀዩም ነዉ።አስከሬን በየጉርጓዱ ይከመራል።ከተንቀሳቃሽ ሥልክ እስከ ምግብ፥ ከሐብል እስከ ብስክሌት ያሉ ቁሳቁሶች ይመዘበራሉ። ቤቶች፥ መደብሮች፥ ቁሳቁሶች፥ መሳጂዶች ይነዳሉ።
ያዩ እንደሚሉት በርግጥም ዘግናኝ ነዉ።የሰዉ አንገት በገጀራ ይቀነጠሳል።እጅ፥ እግር፥ በጎራዴ ይቆረጣል።ሌላ አካል በጩቤ ይጨቀጨቃል። መንገዶች በደም አበላ ጨቅይተዋል-እየጨቀዩም ነዉ።አስከሬን በየጉርጓዱ ይከመራል።ከተንቀሳቃሽ ሥልክ እስከ ምግብ፥ ከሐብል እስከ ብስክሌት ያሉ ቁሳቁሶች ይመዘበራሉ። ቤቶች፥ መደብሮች፥ ቁሳቁሶች፥ መሳጂዶች ይነዳሉ።
የዋሽግተን-ሞስኮ፣ የለንደን-ቤጂንግ ሐያላን ከቁብ አልቆጠሯትም።ፓሪሶች እንዳይረሷት የድሮ ቅኝ ተገዢ ናት።እንደ ሊቢያ እንደ ኮትዲቯር፥ ወይም እንደ ማሊ ሐያል ተባባሪዎችን አስተባብረዉ እንዳያዘመቱባት ነዳጅ፣ ሥልታዊነት፣ መጥፋት ያለበት ገዢ ጠላት የለባትም።ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ።አፍሪቃዉያን የደቡብ ሱዳንን ያክል እንዳይጨነቁላት ነዳጅ፥ አዲስ ገበያ የላትም።ፈረንሳዮችም፣ አፍሪቃዎችም የሉም እንዳይባሉ በጥቂት ጦር አለን ሲሉ፣ የአዉሮጳ ሕብረት አለሁ ለማለት እያዘገመ ነዉ።የደሐይቱ ሐገር ሕዝብ ግን ይረገፋል።የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ እልቂት መነሻ፥ የዓለም ትኩረት ያልሳበበት ምክንያት መድረሻችን ነዉ። ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ፓን ጊ ሙን እንደ ብዙዉ ዓለም ፖለቲከኛ ዲፕሎማት ሁሉ ዘግይተዋል።ግን ቢያንስ በቀደም የግጭት፥ እልቂት ጥፋቱን አሳሳቢነት ተናገሩ።
«ለትዉልዶች ተሳስሮ የኖረዉ ማሕበረሰብ ተከፋፋል እየተጫረሰ ነዉ።ማሕበረሰቡን ደም ያቃባዉ ግጭትን ለማቆም እርምጃ ካልተወሰደ ለአስርታት የሚዘልቅ ግጭት ያስከትላል።»
እልቂቱ፥ ያዩ እንደሚሉት በርግጥም ዘግናኝ ነዉ።የሰዉ አንገት በገጀራ ይቀነጠሳል።እጅ፥ እግር፥ በጎራዴ ይቆረጣል።ሌላ አካል በጩቤ ይጨቀጨቃል።ሴቶች ይደፈራሉ። መንገዶች በደም አበላ ጨቅይተዋል-እየጨቀዩም ነዉ።አስከሬን በየጉርጓዱ ይከመራል።ከተንቀሳቃሽ ሥልክ እስከ ምግብ፥ ከሐብል እስከ ብስክሌት ያሉ ቁሳቁሶች ይመዘበራሉ። ቤቶች፥ መደብሮች፥ ቁሳቁሶች፥ መሳጂዶች ይነዳሉ።
ዋና ፀሐፊ ፓን ጊ ሙን ከኒዮርክ የእልቂት ፍጅቱን አስጊነት ሲናገሩ ፖላንዳዊዉ የካቶሊክ ቄስ ንዛኮን የተባለችዉ መንደር የምታስነግደዉን ግፍ ይታዘቡ ነበር።ስማቸዉ መጠቀሱን ያልፈለጉት ቄስ እንደሚሉት ከመንደሪቱ ሲደርሱ ጣራ-ግርግዳቸዉ የጋዩ ቤቶች፥ በደም የራሰ ዓመድ፥ ከሰል፥ ዝንቦች የወረሩት አስከሬን—-አዩ።የንዛኮን አስደንጋጭ ትርዒት ቄሱ እንደሚሉት በዚሕ አላበቃም።
«እዚያ እንደደረስን ሃያ-ሁለት ሰዎች ተገደሉ።ወደዚያዉ ሃያ-አምስት ቤቶች ጋዩ።ወደ መንደሪቱ መሐል ስንደርስ የተቃጠሉ ሞተር ብስክሌቶች፥ ብስክሌቶች፣የጋየ መድሐኒት ቤት አየን።ሰዎቹ በጣም መጥፎ ነገር ነዉ የፈፀሙት።»
ሙስሊሞች የሚበዙበት የሳሌካ አማፂያን ሕብረት የቀድሞዉን ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ አምባገነን ገዢ ፍራንሷ ቦዚዜን አስወግዶ ሥልጣን ከያዘበት ካለፈዉ ዓመት መጋቢት ወዲሕ ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ሠላም ኖሯት አያዉቅም።በቀድሞዉቹ አማፂያን እና አማፂያኑን በሚቃወሙት በቦዚዜ ታማኞች፥ ቦዚዜ ባስታጠቋቸዉ ወጣቶች መካካል ለወራት የተደረገዉ ዉጊያ ግጭት ሐገሪቱን ለዘራፊ ወሮበሎች አጋልጧቷል።
ወዲያዉ ግጭት ዉጊያዉ ፖለቲካዊ መልክ ባሕሪዉን ለዉጦ ሐይማኖታዊ ሆነ።ሙስሊሞች የሚበዙበትን አማፂያን የሚቃወሙት የክርስቲያኒያን ሚሊሺዎች የታጠቀዉንም፥ ያልታጠቀዉንም፥ ሴቱኑም ወንዱኑም፣ ልጁንም አዋቂዉንም ሙስሊም ሲያሰኛቸዉ በጥይት፥ ሲፈልጋቸዉ በቆንጨራ ይረሽኑት፥ ያርዱ፥ ይቆራርጡ፥ ያሰደዱት ገቡ።
ቻናል ፎር የተሰኘዉ የብሪታንያ ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኛ ባለፈዉ ሳምንት እንደዘገበችዉ ደግሞ ሰዎች እንደበግ እየታረዱ ነዉ።
«ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ዉስጥ የዘር ማጥፋት ዘር እየተዘራ ነዉ።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስጠንቅቋል።የአይን ምስክሮች እንደሚሉት ደግሞ ሙስሊሞች እንደገበግ እየታረዱ ነዉ።»
የቀድሞዋ የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ቅኝ ገዢ ፈረንሳይ የሠላማዊዉን ሰዉ እልቂት ፍጅት ያስቆማል ያለችዉን አንድ ሺሕ ስድስት መቶ ጦር ባለፈዉ ታሕሳስ አዝምታለች።ተጨማሪ አራት መቶ ወታደሮች ለማዝመት እየተዘጋጀችም ነዉ።የአፍሪቃ ሕብረት አባል ሐገራት በበኩላቸዉ አምስት ሺሕ ወታደሮች አዝምተዋል።
የፈረንሳዩ ጦር አዛዥ ጄኔራል ፍራንሲስኮ ሶሪያኖ ባለፈዉ ሳምንት እንዳሉት ሰሞኑን በሕዝብ ላይ ለሚፈፀመዉ ጭፍጨፋ ፀረ-ባላካ በሚል ቡድን የተደራጁት የክርስቲያን ሚሊሺያ አብዛኞቹ አባላት ወንጀለኛ እና ወሮበሎች ናቸዉ።ወንጀለኛና ሽፍቶቹ የሚፈፅሙትን ጥቃት ለመከላከል ግን የሐያሊቱ ሐገር ጠንካራ ጦር ቢያንስ እስካሁን የተከረዉ የለም።
አምና መጋቢት የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክን የመሪነት ሥልጣን ይዘዉ የነበሩት የቀድሞዉ የሳሌካ አማፂ ቡድን መሪ ሚሼል ጆቶዲያ እና ጠቅላይ ሚንስትራቸዉ በፈረንሳይ ፍቃድ፥ በቻድ ግፊት ሥልጣን ለቀዉ በምትካቸዉ ሌሎች ከተሾሙ ወር አለፈ። እልቂቱ ግን ባሰ እንጂ አልቆመም። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዘር ማጥፋቱ ጭፍጨፋ እየተዘራ መሆኑን ሲናገር ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት አምንስቲ ኢንተርናሽናል በበኩሉ የዘር ማጥፋት ወንጀል መፈፀሙን ይዘግባል።
የዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች መዳኛ ፍርድ ቤት ICC ጠቅላይ አቃቢት ሕግ ፋቶ ቤን ሶዳ በበኩላቸዉ የሳሌካ አማፂያንም፥ የፀረ-ሳሌካ ሚሊሻዎችም በሰላማዊ ሕዝብ ላይ የፈፀሙትን ወንጀል ለማጣራት ማቀዳቸዉን አስታዉቀዋል።በፈረንሳይ ድጋፍ በቅርቡ ሥልጣን የያዙት የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ጊዚያዊ ጠቅላይ ሚንስትር አንድሬ ንዛፓዬከ ግን እኒያኑ የፈረንሳዩ ጀኔራል ወንጀለኛ እና ወሮበላ ያሏቸዉን የክርስቲያን ሚሊሺያ አዛዦች ሰብስበዉ ጥቃቱን እንዲያቆሙ መማፀናቸዉን ዛሬ አስታዉቀዋል።
ሕዝብ ግን ፖላንዳዊዉ የካቶሊክ ቄስ እንዳሉት ከቻለ ይሰደዳል፥ ካልቻለ ግን ዕለት በዕለት እየተጨፈጨፈ ነዉ።የጠቅላይ ሚንስትር ንዛፓዬከ መንግሥት፥ የፈረንሳይ እና የአፍሪቃ ሕብረት ጦር ጭፍጨፋዉን ለማስቆም ሁነኛ እርምጃ እንዲወስዱ ፖለንዳዊዉ ቄስና ብጤዎቻቸዉ የሚያሰሙት ጩኸት ሰሚ አላገኘም።
«ርዕሠ ከተማ ባንጉይ የሚገኙት የመንግሥት ባለሥልጣናት እና የፈረንሳይ ጦር (እልቂቱን) እንዲያስቆሙ በተደጋጋሚ ጠይቄ ነበር።ማንም የተቀበለኝ የለም።አሁን ያለሁት የሴሌካ አማፂያን ከማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ እየለቀቁ በሚሸሹበት በካሜሩን እና በቻድ አዋሳኝ ድንበር ነዉ።እንደ ፀረ-ባላካ ሚሊሻዎች ሁሉ የሴላካ አማፅያንም ሲሸሹ የሚያደርሱት ጥፋት ከባድ ነዉ።»
ሱዳናዊዉ እዉቅ የጦር አበጋዝ ሱልጣን ረቢሕ ዓል ዙቤር ኢብን ፈድል አላሕ የዛሬዋን ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክን ከቻድ ጋር ቀይጠዉ መግዛት ከጀመሩበት ከ1875 (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎሮጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) ጀምሮ የዚያች ሐገር ሕዝብ የራሱን ጉዳይ በራሱ ፍላጎትና ፍቃድ ወስኖ አያዉቅም።
ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ፥ ቻድንና ሌሎች የአካባቢዉ ሐገራትን ከሱልጣን ረቢሕ አል ዙቤር ሐይላት የቀማችዉ ፈረንሳይ በ1960 ለማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ የነፃ ሐገር እዉቅና ብትሰጣትም የዚያች ሐገር ፖለቲካዊ ሒደት አንድም በቀጥታ ከፓሪስ አለያም ለፓሪስ ባደሩት በእንጃሚና፥ በያዉንዴ፥ በኪንሻሳ ገዢዎች ያልተዘወረበት ዘመን የለም።
ማዕከላዊ አፍሪቃ ነፃ ከወጣችበት ጊዜ ጀምሮ በተቆጠሩት 53 ዓመታት በመፈንቅለ መንግሥት፥ እራሳቸዉን ወደ ንጉስነት እስከመቀየር በደረሱ የጦር መኮንኖች አገዛዝ፥በርስ በርስና በዉጪ ጣልቃ ገብ ጦር ግጭት ያልታበጠችበት ጊዜ ትንሽ ነዉ።በዚሕ ሁሉ ዘመን የዚያች ሐገር ደሐ ሕዝብ እኩል መጨቆን፥ መረገጥ መሰቃየቱ እንጂ ክርስቲያንና ሙስሊም በሚል ሐይማኖት ለይቶ የተጨፋጨፈበት ዘመን ግን የለም።
ዋና ፀሐፊ ፓን ጊ ሙን «ለበርካታ ትዉልድ ተሳስሮ የኖረ» ያሉት ማሕበረሰብ አንድነትን የበጠሰዉ እልቂት ፍጅትን ለማስቆም ፈረንሳይ እንደ ማሊ ያየር የምድር ጦሯን ማዝመት አልፈለገችም።የራስዋ የፓሪስ፥ የዋሽግተን፥ ለንደን መሪዎች እንደ ሊቢያ ሐያል ፈርጣማ ጦራቸዉን ለማዝመት ምክንያት የላቸዉም።ወደብ አልባ ደሐይቱ ሐገር የሐያሉን ዓለም ትኩረት ለመሳብ እንደ ማሊ ሥልታዊ ጠቀሜታ፥ እንደ ሊቢያ ነዳጅ ዘይት፥ የረጅም ጊዜ የምዕራባዉያን ጠላት ገዢ ሊኖታት ይገባል።የላትም።
የአዉሮጳ ሕብረት እልቂት ፍጅቱ በዓለም መገናኛ ዘዴዎች ወደ ዘር ማጥፋት ወይም የሐይማኖት ተከታዮችን ማፅዳት ከተሸጋገረ በሕዋላ እንኳን ለማዝመት ያቀደዉ ከስድስት መቶ የማይበልጥ ወታደር ነዉ።ሌላዉ ቀርቶ የአፍሪቃ መሪዎች እንኳን የደቡብ ሱዳንን ያክል ሙሉ ትኩረት ሊሰጧት አልፈቀዱም ወይም አልቻሉም።
እንደ ፈረንሳይ ሁሉ እልቂት ፍጅቱን በገሚስ ልብ የሚከታተሉት የአፍሪቃ መሪዎች ያዘመቱት ጦር እስካሁን እልቂቱን ለማስቆም እንደ ፈረንሳይ ጦር ሁሉ የተከረዉ ነገር የለም።እንዲያዉም MISCA በሚል ምሕፃረ-ቃል የሚጠራዉ የአፍሪቃ ሕብረት ጦር አዛዥ ጄኔራል ማርቲን ቱሜንታ ቹሙዋ እንደሚሉት ጦራቸዉ የሚተኩሰዉ በራሱ በጦሩ አባላት ላይ ከተተኮሰበት ብቻ ነዉ።
ጦሩ ሚሊሺያዎቹ ወይም አማፂያኑ በሰላማዊ ሕዝብ ላይ የሚያደርሱትን ጭጨፋ ለማስቆም እርምጃ ካልወሰደ ቦንጊ ድረስ የዘመተበት ዓላማ ምክንያት በርግጥ ግራ አጋቢ ነዉ።ካለፈዉ ታሕሳስ ወዲሕ መረን በለቀቀዉ ጭፍጨፋ ርዕሠ-ከተማ ቦንጊ እና አካባቢዋ ብቻ ከሁለት ሺሕ በላይ ሕዝብ መገደሉ ተዘግቧል።በየመንደሩ በየዕለቱ የሚያልቀዉን ሰዉ በትክክል የቆጠረዉ የለም።ዕልቂቱን ሽሽት የተሰደደ ወይም የተፈናቀለዉን ሕዝብ ከሚረዱት አንዱ ፖለንዳዊዉ ቄስ እንደሚሉት ግድያዉ ባሁን ይዘቱ ከቀጠለ እሳቸዉን ለመሰሉ የዉጪ ሰዎችም ማስጋቱ አይቀርም።ግን ጠመንጃ የታጠቀዉ ጦር የማያደርገዉን ለማድረግ የቆረጡ ይመስላሉ ቄሱ።
«የለም ከዚሕ አንወጣም።ከሕዝቡ ጋር መቆየት እንፈልጋለን።ሕዝቡ ይፈልገናል።በያለንበት በአሸዋ የተሞሉ ጆንያዎችን ደርድረን በምንሰራዉ ምሽግ እንጠለላለን።ጥቃቱ በኛ ላይ በጣም ከከፋ ግን እንወጣ ይሆናል።»
ጄኔራሎቹ ይፎክራሉ።ፖለቲከኞቹ ገና ያቅዳሉ።ዲፕሎማቶቹ ያወራሉ።ሕዝብ ያልቃል።ይሰደዳል።ሐብት ንብረት ይወድማል። ቄሶቹ፥ ርዳታ አቀባዮቹ እልቂት፥ ፍጅት ስደት ስቃዩን ይጋፈጣሉ።ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ።እስከ መቼ ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰማን።
ነጋሽ መሐመድ ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ፓን ጊ ሙን እንደ ብዙዉ ዓለም ፖለቲከኛ ዲፕሎማት ሁሉ ዘግይተዋል።ግን ቢያንስ በቀደም የግጭት፥ እልቂት ጥፋቱን አሳሳቢነት ተናገሩ።
«ለትዉልዶች ተሳስሮ የኖረዉ ማሕበረሰብ ተከፋፋል እየተጫረሰ ነዉ።ማሕበረሰቡን ደም ያቃባዉ ግጭትን ለማቆም እርምጃ ካልተወሰደ ለአስርታት የሚዘልቅ ግጭት ያስከትላል።»
እልቂቱ፥ ያዩ እንደሚሉት በርግጥም ዘግናኝ ነዉ።የሰዉ አንገት በገጀራ ይቀነጠሳል።እጅ፥ እግር፥ በጎራዴ ይቆረጣል።ሌላ አካል በጩቤ ይጨቀጨቃል።ሴቶች ይደፈራሉ። መንገዶች በደም አበላ ጨቅይተዋል-እየጨቀዩም ነዉ።አስከሬን በየጉርጓዱ ይከመራል።ከተንቀሳቃሽ ሥልክ እስከ ምግብ፥ ከሐብል እስከ ብስክሌት ያሉ ቁሳቁሶች ይመዘበራሉ። ቤቶች፥ መደብሮች፥ ቁሳቁሶች፥ መሳጂዶች ይነዳሉ።
ዋና ፀሐፊ ፓን ጊ ሙን ከኒዮርክ የእልቂት ፍጅቱን አስጊነት ሲናገሩ ፖላንዳዊዉ የካቶሊክ ቄስ ንዛኮን የተባለችዉ መንደር የምታስነግደዉን ግፍ ይታዘቡ ነበር።ስማቸዉ መጠቀሱን ያልፈለጉት ቄስ እንደሚሉት ከመንደሪቱ ሲደርሱ ጣራ-ግርግዳቸዉ የጋዩ ቤቶች፥ በደም የራሰ ዓመድ፥ ከሰል፥ ዝንቦች የወረሩት አስከሬን—-አዩ።የንዛኮን አስደንጋጭ ትርዒት ቄሱ እንደሚሉት በዚሕ አላበቃም።
«እዚያ እንደደረስን ሃያ-ሁለት ሰዎች ተገደሉ።ወደዚያዉ ሃያ-አምስት ቤቶች ጋዩ።ወደ መንደሪቱ መሐል ስንደርስ የተቃጠሉ ሞተር ብስክሌቶች፥ ብስክሌቶች፣የጋየ መድሐኒት ቤት አየን።ሰዎቹ በጣም መጥፎ ነገር ነዉ የፈፀሙት።»
ሙስሊሞች የሚበዙበት የሳሌካ አማፂያን ሕብረት የቀድሞዉን ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ አምባገነን ገዢ ፍራንሷ ቦዚዜን አስወግዶ ሥልጣን ከያዘበት ካለፈዉ ዓመት መጋቢት ወዲሕ ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ሠላም ኖሯት አያዉቅም።በቀድሞዉቹ አማፂያን እና አማፂያኑን በሚቃወሙት በቦዚዜ ታማኞች፥ ቦዚዜ ባስታጠቋቸዉ ወጣቶች መካካል ለወራት የተደረገዉ ዉጊያ ግጭት ሐገሪቱን ለዘራፊ ወሮበሎች አጋልጧቷል።
ወዲያዉ ግጭት ዉጊያዉ ፖለቲካዊ መልክ ባሕሪዉን ለዉጦ ሐይማኖታዊ ሆነ።ሙስሊሞች የሚበዙበትን አማፂያን የሚቃወሙት የክርስቲያኒያን ሚሊሺዎች የታጠቀዉንም፥ ያልታጠቀዉንም፥ ሴቱኑም ወንዱኑም፣ ልጁንም አዋቂዉንም ሙስሊም ሲያሰኛቸዉ በጥይት፥ ሲፈልጋቸዉ በቆንጨራ ይረሽኑት፥ ያርዱ፥ ይቆራርጡ፥ ያሰደዱት ገቡ።
ቻናል ፎር የተሰኘዉ የብሪታንያ ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኛ ባለፈዉ ሳምንት እንደዘገበችዉ ደግሞ ሰዎች እንደበግ እየታረዱ ነዉ።
«ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ዉስጥ የዘር ማጥፋት ዘር እየተዘራ ነዉ።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስጠንቅቋል።የአይን ምስክሮች እንደሚሉት ደግሞ ሙስሊሞች እንደገበግ እየታረዱ ነዉ።»
የቀድሞዋ የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ቅኝ ገዢ ፈረንሳይ የሠላማዊዉን ሰዉ እልቂት ፍጅት ያስቆማል ያለችዉን አንድ ሺሕ ስድስት መቶ ጦር ባለፈዉ ታሕሳስ አዝምታለች።ተጨማሪ አራት መቶ ወታደሮች ለማዝመት እየተዘጋጀችም ነዉ።የአፍሪቃ ሕብረት አባል ሐገራት በበኩላቸዉ አምስት ሺሕ ወታደሮች አዝምተዋል።
የፈረንሳዩ ጦር አዛዥ ጄኔራል ፍራንሲስኮ ሶሪያኖ ባለፈዉ ሳምንት እንዳሉት ሰሞኑን በሕዝብ ላይ ለሚፈፀመዉ ጭፍጨፋ ፀረ-ባላካ በሚል ቡድን የተደራጁት የክርስቲያን ሚሊሺያ አብዛኞቹ አባላት ወንጀለኛ እና ወሮበሎች ናቸዉ።ወንጀለኛና ሽፍቶቹ የሚፈፅሙትን ጥቃት ለመከላከል ግን የሐያሊቱ ሐገር ጠንካራ ጦር ቢያንስ እስካሁን የተከረዉ የለም።
አምና መጋቢት የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክን የመሪነት ሥልጣን ይዘዉ የነበሩት የቀድሞዉ የሳሌካ አማፂ ቡድን መሪ ሚሼል ጆቶዲያ እና ጠቅላይ ሚንስትራቸዉ በፈረንሳይ ፍቃድ፥ በቻድ ግፊት ሥልጣን ለቀዉ በምትካቸዉ ሌሎች ከተሾሙ ወር አለፈ። እልቂቱ ግን ባሰ እንጂ አልቆመም። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዘር ማጥፋቱ ጭፍጨፋ እየተዘራ መሆኑን ሲናገር ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት አምንስቲ ኢንተርናሽናል በበኩሉ የዘር ማጥፋት ወንጀል መፈፀሙን ይዘግባል።
የዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች መዳኛ ፍርድ ቤት ICC ጠቅላይ አቃቢት ሕግ ፋቶ ቤን ሶዳ በበኩላቸዉ የሳሌካ አማፂያንም፥ የፀረ-ሳሌካ ሚሊሻዎችም በሰላማዊ ሕዝብ ላይ የፈፀሙትን ወንጀል ለማጣራት ማቀዳቸዉን አስታዉቀዋል።በፈረንሳይ ድጋፍ በቅርቡ ሥልጣን የያዙት የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ጊዚያዊ ጠቅላይ ሚንስትር አንድሬ ንዛፓዬከ ግን እኒያኑ የፈረንሳዩ ጀኔራል ወንጀለኛ እና ወሮበላ ያሏቸዉን የክርስቲያን ሚሊሺያ አዛዦች ሰብስበዉ ጥቃቱን እንዲያቆሙ መማፀናቸዉን ዛሬ አስታዉቀዋል።
ሕዝብ ግን ፖላንዳዊዉ የካቶሊክ ቄስ እንዳሉት ከቻለ ይሰደዳል፥ ካልቻለ ግን ዕለት በዕለት እየተጨፈጨፈ ነዉ።የጠቅላይ ሚንስትር ንዛፓዬከ መንግሥት፥ የፈረንሳይ እና የአፍሪቃ ሕብረት ጦር ጭፍጨፋዉን ለማስቆም ሁነኛ እርምጃ እንዲወስዱ ፖለንዳዊዉ ቄስና ብጤዎቻቸዉ የሚያሰሙት ጩኸት ሰሚ አላገኘም።
«ርዕሠ ከተማ ባንጉይ የሚገኙት የመንግሥት ባለሥልጣናት እና የፈረንሳይ ጦር (እልቂቱን) እንዲያስቆሙ በተደጋጋሚ ጠይቄ ነበር።ማንም የተቀበለኝ የለም።አሁን ያለሁት የሴሌካ አማፂያን ከማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ እየለቀቁ በሚሸሹበት በካሜሩን እና በቻድ አዋሳኝ ድንበር ነዉ።እንደ ፀረ-ባላካ ሚሊሻዎች ሁሉ የሴላካ አማፅያንም ሲሸሹ የሚያደርሱት ጥፋት ከባድ ነዉ።»
ሱዳናዊዉ እዉቅ የጦር አበጋዝ ሱልጣን ረቢሕ ዓል ዙቤር ኢብን ፈድል አላሕ የዛሬዋን ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክን ከቻድ ጋር ቀይጠዉ መግዛት ከጀመሩበት ከ1875 (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎሮጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) ጀምሮ የዚያች ሐገር ሕዝብ የራሱን ጉዳይ በራሱ ፍላጎትና ፍቃድ ወስኖ አያዉቅም።
ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ፥ ቻድንና ሌሎች የአካባቢዉ ሐገራትን ከሱልጣን ረቢሕ አል ዙቤር ሐይላት የቀማችዉ ፈረንሳይ በ1960 ለማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ የነፃ ሐገር እዉቅና ብትሰጣትም የዚያች ሐገር ፖለቲካዊ ሒደት አንድም በቀጥታ ከፓሪስ አለያም ለፓሪስ ባደሩት በእንጃሚና፥ በያዉንዴ፥ በኪንሻሳ ገዢዎች ያልተዘወረበት ዘመን የለም።
ማዕከላዊ አፍሪቃ ነፃ ከወጣችበት ጊዜ ጀምሮ በተቆጠሩት 53 ዓመታት በመፈንቅለ መንግሥት፥ እራሳቸዉን ወደ ንጉስነት እስከመቀየር በደረሱ የጦር መኮንኖች አገዛዝ፥በርስ በርስና በዉጪ ጣልቃ ገብ ጦር ግጭት ያልታበጠችበት ጊዜ ትንሽ ነዉ።በዚሕ ሁሉ ዘመን የዚያች ሐገር ደሐ ሕዝብ እኩል መጨቆን፥ መረገጥ መሰቃየቱ እንጂ ክርስቲያንና ሙስሊም በሚል ሐይማኖት ለይቶ የተጨፋጨፈበት ዘመን ግን የለም።
ዋና ፀሐፊ ፓን ጊ ሙን «ለበርካታ ትዉልድ ተሳስሮ የኖረ» ያሉት ማሕበረሰብ አንድነትን የበጠሰዉ እልቂት ፍጅትን ለማስቆም ፈረንሳይ እንደ ማሊ ያየር የምድር ጦሯን ማዝመት አልፈለገችም።የራስዋ የፓሪስ፥ የዋሽግተን፥ ለንደን መሪዎች እንደ ሊቢያ ሐያል ፈርጣማ ጦራቸዉን ለማዝመት ምክንያት የላቸዉም።ወደብ አልባ ደሐይቱ ሐገር የሐያሉን ዓለም ትኩረት ለመሳብ እንደ ማሊ ሥልታዊ ጠቀሜታ፥ እንደ ሊቢያ ነዳጅ ዘይት፥ የረጅም ጊዜ የምዕራባዉያን ጠላት ገዢ ሊኖታት ይገባል።የላትም።
የአዉሮጳ ሕብረት እልቂት ፍጅቱ በዓለም መገናኛ ዘዴዎች ወደ ዘር ማጥፋት ወይም የሐይማኖት ተከታዮችን ማፅዳት ከተሸጋገረ በሕዋላ እንኳን ለማዝመት ያቀደዉ ከስድስት መቶ የማይበልጥ ወታደር ነዉ።ሌላዉ ቀርቶ የአፍሪቃ መሪዎች እንኳን የደቡብ ሱዳንን ያክል ሙሉ ትኩረት ሊሰጧት አልፈቀዱም ወይም አልቻሉም።
እንደ ፈረንሳይ ሁሉ እልቂት ፍጅቱን በገሚስ ልብ የሚከታተሉት የአፍሪቃ መሪዎች ያዘመቱት ጦር እስካሁን እልቂቱን ለማስቆም እንደ ፈረንሳይ ጦር ሁሉ የተከረዉ ነገር የለም።እንዲያዉም MISCA በሚል ምሕፃረ-ቃል የሚጠራዉ የአፍሪቃ ሕብረት ጦር አዛዥ ጄኔራል ማርቲን ቱሜንታ ቹሙዋ እንደሚሉት ጦራቸዉ የሚተኩሰዉ በራሱ በጦሩ አባላት ላይ ከተተኮሰበት ብቻ ነዉ።
ጦሩ ሚሊሺያዎቹ ወይም አማፂያኑ በሰላማዊ ሕዝብ ላይ የሚያደርሱትን ጭጨፋ ለማስቆም እርምጃ ካልወሰደ ቦንጊ ድረስ የዘመተበት ዓላማ ምክንያት በርግጥ ግራ አጋቢ ነዉ።ካለፈዉ ታሕሳስ ወዲሕ መረን በለቀቀዉ ጭፍጨፋ ርዕሠ-ከተማ ቦንጊ እና አካባቢዋ ብቻ ከሁለት ሺሕ በላይ ሕዝብ መገደሉ ተዘግቧል።በየመንደሩ በየዕለቱ የሚያልቀዉን ሰዉ በትክክል የቆጠረዉ የለም።ዕልቂቱን ሽሽት የተሰደደ ወይም የተፈናቀለዉን ሕዝብ ከሚረዱት አንዱ ፖለንዳዊዉ ቄስ እንደሚሉት ግድያዉ ባሁን ይዘቱ ከቀጠለ እሳቸዉን ለመሰሉ የዉጪ ሰዎችም ማስጋቱ አይቀርም።ግን ጠመንጃ የታጠቀዉ ጦር የማያደርገዉን ለማድረግ የቆረጡ ይመስላሉ ቄሱ።
«የለም ከዚሕ አንወጣም።ከሕዝቡ ጋር መቆየት እንፈልጋለን።ሕዝቡ ይፈልገናል።በያለንበት በአሸዋ የተሞሉ ጆንያዎችን ደርድረን በምንሰራዉ ምሽግ እንጠለላለን።ጥቃቱ በኛ ላይ በጣም ከከፋ ግን እንወጣ ይሆናል።»
ጄኔራሎቹ ይፎክራሉ።ፖለቲከኞቹ ገና ያቅዳሉ።ዲፕሎማቶቹ ያወራሉ።ሕዝብ ያልቃል።ይሰደዳል።ሐብት ንብረት ይወድማል። ቄሶቹ፥ ርዳታ አቀባዮቹ እልቂት፥ ፍጅት ስደት ስቃዩን ይጋፈጣሉ።ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ።እስከ መቼ ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰማን።
ነጋሽ መሐመድ

ማየት ማመን ነው በሚል የኢትዮጵያውያንን የስደት ስቃይ የሚያሳይ የፎቶ ኤግዚብሽን እና የቪዲዮ ቅንብር በኖርዌ ኦስሎ ከተማ ተካሄደ

ፌብሩዋሪ 17, 2014
ሄለን ንጉሤ/ኖርዌ/

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ የሴቶችና ወጣቶች ክፍል በሐገራችን ኢትዮጵያ የሰዎች የህገወጥ ዝውውርን በተመለከተና ሰዎች ከሃገራቸው ለምን እንደሚሰደዱ እንዲሁም የስደትን አስከፊነት የሚያሳይ የፎቶ ኤግዚብሽንና ቪዲዮ በDiakonhjemmet university college Oslo February 14, 2014 ለኖርዌጅያንና የተለያየ ሐገር ዜግነት ላላቸው ተማሪዎች አቀረቡ።

ይህ የፎቶ ኤግዚብሽን ዋና አላማው በሐገራችን ኢትዮጵያ በወያኔ የአገዛዝ ዘመን የህገወጥ የሰዎች ዝውውር ቁጥሩ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ በመምጣቱና ዜጎች በሐገራቸው ለመኖር የሚያስችላቸው መልካም አስተዳደር ስለሌለ የሰብአዊ መብት ጥሰቱ ከእለት ወደ እለት እየጨመረ በመምጣቱ ዜጎች የወያኔ አባል ካልሆኑ በስተቀር ተምረው የስራ እድል ስለማያገኙ፤ የመናገርና የመፃፍ መብታቸው በመገደቡ፤ ዜጎች ያለምንም ቅድመ ሁኔት መሬታቸውን እየተነጠቁ ለውጭ ሐገር ባለሃብቶች በመሸጡ ተለዋጭ ነገር ሳያገኙ ለጎዳና ህይወት በመዳረጋቸው፤ በዘራቸው ምንክያት በሚደርስባቸው ተፅኖ እንዲሁም በፖለቲካ አመለካከታቸው በሚደርስባቸው ከፍተኛ እስር፤ ግርፋትና እንግልት ሳቢያ ሐገራቸውን ለቀው ለመሰደድ ይገደዳሉ። ገዢው መንግስት ህጋዊ የሚላቸው ነገር ግን ህጋዊ ያልሆኑ 250 ኤጀንሲዎችን አቋቁሞ ፍቃድ በመስጠት የዜጎች ሽያጭ በስፋት እንዲያከናውኑ እያደረገ ይገኛል። እነኚህ ኤጀንሲ ተብዬዎች በአብዛኛው እድሜያቸው ለስራ ያልደረሱ ህፃናት ልጆችን ሳይቀር በገጠሪቱ የሃገራችን ክፍል የሚገኙ ወገኖቻችንን በመመልመል የራሳቸውን ኪስ ለማደለብ ለሽያጭ ያቀርባሉ።

ሰዎች ከሐገራቸው እንዲሰደዱ ዋናውን ሚና እየተጫወተ ያለው አምባገነኑ የወያኔ መንግስት ሲሆን እነዚህ ስደተኞች በመንገድ ላይ የሰውነት ብልታቸው ከውስጣቸው እየተወሰደ ሲሽጥ፤ በየመንገዱ ሲሞቱ፤ ሴቶች እህቶቻችን ተገደው ሲደፈሩ፤ ሲደበደቡ፤ የፈላ ውሃና ዘይት በላያቸው ሲደፋ፤ ከፎቅ ተወርውረው ሲሞቱ፤ በየኢምባሲው ደጃፍ ሲጎተቱ፤ አእምሮአቸውን ስተው በየጎዳናው እራቁታቸውን እየሄዱ መሳለቂያ ሲሆኑ በየሃገሩ አምባሳደር ተብለው የተወከሉት ግን ምንም አይነት ወገናዊ ስሜት የሌላቸው በመሆኑ ለወከሉት ህዝብ ከለላ መስጠት ሳይችሉ በተቃራኒው ለአረቦቹ ወግነው ሲናገሩ ይታያሉ። ሐገር ውስጥም ለሚደረገው ህገወጥ ዝውውር ገዢው ፓርቲ ትኩረት ሰጥቶ ባለመከታተሉ ወይም እያየ ዝም በማለቱ ሰዎች በኮንቴነር እንደ እቃ እየታጨቁ የብዙዎች ህይወት ማለፉ ይታወቃል። እነኚህ ከላይ የጠቀስናቸው ችግሮች በሙሉ እየተፈፀመብን ያለው በአምባገነኑ የወያኔ መንግስት መሆኑን ለአለም ለማጋለጥ ማየት ማመን ነው በሚል የወገኖቻችንን ስቃይ ከሐገር ሲወጡ ጀምሮ በመንገድና በደረሱበት ቦታ ሁሉ የሚደርስባቸውን ስቃይና እንግልት የሚያሳየውን የፎቶ ኤግዚብሽን እና ቪዲዮ ፕሮግራም ለማቅረብ የወሰነው።

ዝግጅቱ በኖርዌጅያን የሰአት አቆጣጠር ከጠዋቱ 08፤45 በትምህርት ቤቱ መምህር እና በእኛ በኩል በዶ/ር ሙሉአለም አዳም የመክፈቻ  ንግግር ሲሆን፤ በመቀጠል ተማሪዎቹ ፎቶዎቹን እየተዘዋወሩ የተመለከቱ ሲሆን አዘጋጆቹም ስለፎቶዎቹ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከ15 ደቂቃ እረፍት በኋላ የቪዲዮ ፕሮግራም የቀረበ ሲሆን ይህ ቪዲዮ መምህራኑን ጨምሮ ተማሪዎቹን ያስለቀሰ ሲሆን አንዳንዶቹ ለማየት አቅም በማጣታቸው አዳራሹን ለቀው የወጡም ነበሩ ከቪዲዮ በኋላ ተማሪዎቹ የተሰማቸውን ስሜት ሲገልፁ መንግስታችን በዚህ የሰዎች ንግድ ውስጥ መሳተፉ ያሳዘናት መሆኑን አንዲት ተማሪ ገልፃለች። አዘጋጅ ወጣቶችም የኖርዌጂያን መንግስት ለኢትዮጵያ  የሚሰጠውን ገንዘብ ማቆም እንዳለበትና የወያኔ መንግስት የሚያገኘውን የእርዳታ ገንዘብ መሳሪያ ለመግዛት እና ህዝቦችን ለመጨቆን እየተጠቀመበት በመሆኑ በስልጣን ላይ እንዲቆይ እገዛ እያደረጉ በመሆኑ እኛ በሃገራችን ዲሞክራሲያዊ ለውጥ ለማምጣት እና ይህንን ጨቋኝ   አገዛዝ ለመጣል በምናደርገው ትግል እንቅፋት ሆኖ ያስቸገረን በመሆኑ የኖርዌጂያን ሰዎች የሚለግሱት ገንዘባቸው ለምን ተግባር እንደሚውል እንዲያውቁና ተማሪዎቹም መንግስታቸውን እንዲጠይቁ እንዲሁም ለሚያውቋቸው ሁሉ ያዩት እንዲያስረዱላቸው ጠይቀዋል።

በመጨረሻም መምህራኑ ለአዘጋጆቹ ምስጋና አቅርበው ፕሮግራሙ በኖርዌጅያን የሰአት አቆጣጠር 11፡00
ተጠናቋ። እኛም አዘጋጆቹ ለወደፊት ሐገራችን ከአምባገነኖች ነፃ እስከምትወጣ ድረስ የወያኔን ትውልድ የማጥፋት ሴራ በማጋለጥ እስከመጨረሻው እንደምንሰራ ለመግለፅ እወዳለሁ። ዝግጅቱን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ። 
        https://www.youtube.com/watch?v=4oEyoA3WrU8

ኢህአዴግ ራሱ ባወጣው አፋኝ ሕግ ታፈነ

ለተፈጥሮ ሃብት የጠየቀው ዓለምዓቀፋዊ እውቅና ውድቅ ሆነ
eiti
ኢህአዴግ የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) ለተሰኘ ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ያቀረበው የእውቅና ጥያቄ ማመልከቻ ከተገመገመ በኋላ መመዘኛዎቹን ማሟላት ባለመቻሉ መውደቁ ተሰማ። ኢህአዴግ የእውቅና ማመልከቻ በድጋሚ ማስገባቱን አስቀድሞ ያወቀው ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅት (Human Rights Watch) ጉዳዩን ከሚከታተሉ ጋር ባገኘው መረጃ ኢህአዴግ የEITI መስፈርት የማያሟላና በሰብአዊ መብት ጥሰት የተወነጀለ ድርጅት መሆኑንን ማስረጃ አስደግፎ በመጥቀስ መሟገቻ ደብዳቤ ለድርጅቱ አስገብቶ ነበር።
EITI የዛሬ 11ዓመት አካባቢ የተቋቋመ በተፈጥሮ ሃብት ዙሪያ ዕውቅና የሚሰጥ ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱ የተፈጥሮ ሃብት የህዝብ መሆኑን የሚያምን ሲሆን ማንኛውም የተፈጥሮ ሃብት – ማዕድን፣ ዘይት፣ ብረታብረትና ጋዝ – ከመሬት በሚወጣበት ጊዜ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የሚኖረውን ያህል ግልጽነትና ተጠያቂነት በሌለባቸው አገራት ድርጊቱ ለሙስና እና ግጭት በር እንደሚከፍት ይናገራል፡፡ በመሆኑንም ድርጅቱ አገራት ለሚያቀርቡት የዕውቅና ጥያቄ ማሟላት ያለባቸውን መስፈርት በዝርዝር አስቀምጧል፡፡ ልማትና እድገት በሚል ሰበብ የሕዝብ ሃብት የሆነውን የተፈጥሮ ሃብት በማውጣት የህዝባቸውን መብት ለሚረግጡ አገራት የሚያቀርቡትን የዕውቅና ማመልከቻ ውድቅ ያደርጋል፡፡
የጎልጉል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ምንጭ እንደጠቆሙት ኢህአዴግ ያቀረበው የእውቅና ጥያቄ ውድቅ መደረጉ እውነት ነው። ምንጩ እንዳሉት ኢህአዴግ በውሳኔው በመበሳጨት ይግባኝ ለመጠየቅ በዝግጅት ላይ ነው። ድርጅቱ (EITI) አንድ አገር ለሚያቀርበው የእውቅና ማመልከቻ በመስፈርቱ መሰረት ግምገማ ካካሄደ በኋላ እውቅና እንዲሰጥ ሲያምን በራሱ ድረገጽ ላይ የዚያን አገር ስም በመመዝገብ ተጠቃሹ አገር ከተፈጥሮ ሃብት ጋር በተያያዙ ኢንቨስትመንቶች የሚገኘው ትርፍ ለህዝብ ጥቅም እንዲውል ያደርጋል የሚል እውቅና በመስጠት ምስክርነቱን ያሰፍራል፡፡
ኢህአዴግ የመጀመሪያው የማመልከቻ ጥያቄ ያቀረበው በአውሮጳውያኑ አቆጣጠር በ2009 አካባቢ ነበር፡፡ ከEITI አምስት መስፈርቶች መካከል አንዱ፤ ማመልከቻ የሚያቀርቡ አገራት ከመያዶች (መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች) ጋር ለመስራት ያላቸው ፍላጎት ተጠቃሽ ነው፡፡ በወቅቱ ኢህአዴግ በመያዶች ላይ አፋኝ ሕግ አውጥቶ የነበረ በመሆኑ እውቅና ሰጪው ድርጅት – EITI – የኢህአዴግን ማመልከቻ ውድቅ አድርጎታል፡፡ የEITI ቦርድ ይህን ዓይነት ውሳኔ ሲያስተላልፍ ያሰፈረው ነገር ኢትዮጵያ በእጩ አባልነት ለመመዝገብ በመጀመሪያ በመያዶች ላይ ያወጣችውን ሕግ ማስወገድ አለባት የሚል እንደነበር የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅት በድረገጹ ላይ አስቀምጦታል፡፡ በወቅቱ የተሰጠው ይህ ብያኔ በEITI እውቅና አሰጣጥ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያ እንደሆነ ተጠቁሞም ነበር፡፡
የEITI ዕውቅናን ለማግኘት ቋምጦ የነበረው ኢህአዴግ በድርጅቱ ውሳኔ ባለመደሰት ጥቂት ዓመታትን ቆጥሮ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ በአቶ ሃይለማርያም በመመራት በድጋሚ ዕውቅና የማግኘት ዘመቻውን ማጠናከር ጀመረ፤ በይፋም እንቅስቃሴውን ቀጠለ፡፡ የማዕድን ሚ/ር መ/ቤትም ዕውቅና ማግኘቱ በጣም የሚያስፈልግ እንደሆነ በይፋ በመናገር ዘመቻውን አጧጡፎ ነበር፡፡ ከዚህም አልፎ ለዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን አሠራር በዓለምአቀፉ ድርጅት ላይ ተግባራዊ በማድረግ ኢህአዴግ Ethiopia Revenue Transparency Initiative (ERTI) የሚባል “ተለጣፊ” ተቋም በመመሥረት እንቅስቃሴ ሲያደርግ እንደቆየ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ለEITI በጻፈው ደብዳቤ ላይ ገልጾዋል፡፡
ጉዳዩን በቅርብ ይከታተሉ የነበሩ የዲፕሎማቲክ ምንጮች ኢህአዴግ በአውሮጳውያኑ አቆጣጠር 2013ዓም በድጋሚ ማመልከቻ የማቅረብ ዓላማ እንዳለው ለዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት አሳወቁ፡፡ በወቅቱ ኢህአዴግ ማሻሻያ እያደረጉ ነኝ የሚል ማስመሰያ ለማቅረብ የሞከረ ቢሆንም የመያዶችና የጸረ አሻባሪነት አፋኝ ሕጎቹ በተጨማሪ በቴሌኮሙኒኬሽን በኩል በስልክና ኢንተርኔት የሚያደርውን ህዝብን የመሰለል ተግባር አጠናክሮ የቀጠለበት እንደሆነ በመጥቀስ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ክፍሎች EITI ዕውቅና እንዳይሰጥ መወትወታቸውን ተያያዙ፡፡
እነዚሁ ወገኖች በተደጋጋሚ ያደረጉት “የወረቀትና የፔቲሽን ትግል” እየተባለ የሚቃለለው ትግል ውጤት በማምጣት ኢህአዴግ በደጋሚ ያስገባው የአባልነት ማመልከቻ ሰሞኑን ውድቅ መደረጉ ተሰምቷል፡፡ እንደ መረጃው ከሆነ EITI ማመልከቻ በሚመዝንበት በሁሉም መስፈርቶች ኢህአዴግ ወድቋል፡፡
አነስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙና ኢህአዴግ “ልማታዊ” የሚላቸው ኢንቨስተሮች ሳይሆኑ በከፍተኛ ደረጃ የሚመደብ መዋዕለ ንዋይ የሚያፈሱ ባለሃብቶች ኢንቨስት የሚያደርጉበትን አገር ለመምረጥ የመጀመሪያው መለያቸው የEITI ድረገጽ የአባል አገራት ዝርዝር እንደሆነ ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ኢህአዴግም አስፈላጊውን የምዝገባና የማመልከቻ መስፈርት በማሟላት የተቋሙን እውቅና የጠየቀው በድርጅቱ ድረገጽ ላይ ለመመዝገብ ነበር። የሁለት ጊዜ ሙከራው መክሸፉ ኢህአዴግ ራሱ ባወጣው አፋኝ ህግ መታፈኑ የሚያመላክት እንደሆነ የሚጠቅሱ ክፍሎች፤ ከኢህአዴግ ከፍተኛ ፍላጎት አኳያና ሰሞኑን በተለያየ አቅጣጫ እየተወጠረ ከመምጣቱ አንጻር ሁኔታው አጣዳፊና ፋታ የማይሰጥ በሽታ ምልክት እንደሆነ በምጸት ይናገራሉ፡፡
ስለEITI ውሳኔ ባጭሩ እንዲያብራሩልን የጠየቅናቸው ባለሙያ እንዳሉት “አንድ ዩኒቨርሲቲ ህንጻ በማስገንባቱና አስተማሪዎችን በመቅጠሩ ብቻ ዩኒቨርስቲ ተብሎ ሊጠራ አይችልም። ዩኒቨርስቲው ዓለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስለመሆኑ በዓለም አቀፍ መስፈርት መሰረት ተገምግሞ እውቅና የሚሰጠው መስፈርቶቹን በሙሉ አሟልቶ ስለመገኘቱ ምርመራ ተደርጎበት ፈተናውን ሲያልፍ ብቻ ነው። በዚሁ መሰረት አልፎ እውቅና ያላገኘ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ገብቶ መማር የተሳትፎ ያህል ነው። መስፈርቱን አሟልተው እውቅና ካገኙት ጋር መወዳደር ስለማይችል ተመራጭ አይሆንም። በተመሳሳይ Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የተባለው ድርጅትም ከየአገራቱ እውቅና እንዲሰጥ የሚቀርብለትን ጥያቄ /ማመልከቻ/ የሚመዝንበት መስፈርቶች አሉት። ኢህአዴግ የተፈተነው በዚሁ አቅልጦና አንጥሮ በሚያወጣው መመዘኛ ነው ብለዋል፡፡”
ስለጉዳዩ የተጠየቀው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ የህዝብ ግንኙነት ግብረ ኃይል ጉዳዩን በጥልቀት የሚያውቀውና ገና ከጅምሩ ሲከታተል የቆየው መሆኑን በመግለጽ በበርካታ ፈርጆች ከሚያካሂደው ትግል አንጻር በዕቅድ ሲያከናውነው የቆየ መሆኑን አመልክቷል። የህዝብ ግንኙነት ክፍሉ ለጎልጉል እንዳለው ከሆነ “የEITI ውሳኔ ኢትዮጵያን እንደ አገር የሚጎዳ መሆኑ ግልጽ ነው፤ ሆኖም ውሳኔው ኢህአዴግ በራሱ ግትረኝነትና እብሪት ያመጣው ጣጣ በመሆኑ የራሱን ተግባር ተከትሎ የተወሰነው ውሳኔ በአገሪቱ ላይ በማንኛውም መልኩ ለሚያደርሰው ኪሳራ ተጠያቂው ኢህአዴግና ህወሃት ናቸው” ብሏል። በማያያዝም የጋራ ንቅናቄው ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ መግለጫ በማውጣት አስፈላጊ ናቸው ለሚላቸው ወገኖች እንደሚበትንና ተቋሙ በውሳኔው እንዲጸና የሚቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ ለተሰማሩ መልዕክት እንደሚያስተላልፍ አመልክቷል።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ረዳት ፓይለቱ ሀይለመድህን በእህቱ አንደበት…

በመጀመሪያ ይህን ጽሁፍ የምታነቡ ሰዎች በሙሉ የተዝረከረከ ከሆነባችሁ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ከትናንት ከሰዐት በኋላ ጀምሮ እስካሁን ኢንተርኔትና ቴለቪዥን ላይ ያለማቋረጥ ተተክየ ስለቆየሁና በጥልቅ ሃዘን ስለተመታሁ አይምሮየ ትክክል ላይሆን ይችላል።
‘የኢትዮጵያ አየር መንገድን ወደ ሮም ይጓዝ የነበረ አውሮፕላን ጠልፎ ጄነቫ ላይ ያሳረፈው ረዳት አብራሪ እጁን ለስዊዝ ስጠ። ምክንያቱም ስዊዘርላንድ ውስጥ ጥገኝነት ለመጠየቅ ነው ብሏል።’ የሚለውን ዜና በርካታ የዜና ማሰራጫዎች ከየፊናቸው አስተያየት ጋር አቅርበውታል። የዜና ማሰራጫዎች ብቻ ሳይሆኑ የተለያዩ ወገኖች ያሻቸውን ብለዋል። የፖለቲካ ድርጅቶች የሰብዐዊ መብት ተሟጋቾችና እንደ አቤ ቶኪቻው ያሉ ቀልደኞች የየራሳቸውን ሃሳብ ለማስተላለፍ ተጠቅመውበታል። በጣም አሳዝኝ ነገር ነው። ሁሉም የየራሱን እምነት ለማስተላለፍ እንጂ እሱስ ምን ሆኖ ይሆን ብሎ አለማሰቡ ልብ ይሰብራል።
ወንድሜ ሃይለመድህን አበራ የሰዎችን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል አይደለም እንስሳትን ለመጉዳት የሚፈልግ ሰው አይደልም። ደግሞም ያንን የጨነቀውን ያክል ከፈራው ነገር ለመሸሽ ሞከረ እንጂ ማንንም ባለመጉዳቱና ሃሳብ እንኳ እንዳልነበረው ምንም አይነት ማጥቂያ መሳርያ ባለመታጠቁ አሳይቷል። በሁሉም ዘንድ የሚታወቀው ለተቸገሩ በመድረስና ባዛኝነቱ ነው። ካገር ውጪ ሄዶ ለመኖር የሚፈልግ ሰው ቢሆን ለሱ በጣም ቀላል ነገር ነው። ከጥቂት ወራት በፊትንኳ ዩኤስ ኤ ሄዶ ነበር። ከ አስር ቀናት በላይንኳ መቆየት አልፈለገም። ዝም ብሎ ካገር መውጣት ቢፈልግ ከዛ የተሻለ አጋጣሚ አልነበረም። ደግሞም በኑሮ ደረጃ ውጪ ቢኖር ያን ያክል የሚያሻሽለው ነገር አይደለም። ምክንያቱም የገንዘብ ችግር የለበትም። ከራሱም አልፎ ለብዙ ሰዎች የሚተርፍ ገቢ ነበረው።
ከልጅነቱ ጀምሮ ጎበዝ ሳይሆን እጅግ በጣም ጎበዝ ጭንቅላት ያለው ወጣት ነው። አብዛኛዎቹን ክፍሎች ሁለት ሁለት እያለፈ አስራ ሰባት አመት ሳይሞላው ሀይስኩል ሲያጠናቅቅ የ አስራሁለተኛ መልቀቂያ ውጤቱ ሁሉም ኤ ነበር። የጀመረውን የ አርክቴክቸር ትምህርት ትቶ ወደ ፓይለትነት የገባው ለሙያው ካለው ፍቅር የተነሳ ነው። ለኢትዮጵያ አየር መንገድም የተለየ ክብር አለው።
ሃይለመድህን ሁሉንም አስታዋሽ ቤተሰቡን የሚወድና ተጫዋች ሰው ነበር እስከ ቅርብ ጊዜ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ለኛ ያለውን ፍቅር ደህነታችንን በማረጋገጥና የሚያስፈልገንን ሁሉ በመታዘዝ ቢገልጽም ከዘመድ ወዳጆቹ ጋር መገናኘትና አቆመ። የወትሮው ጨዋታና ደስተኝነቱ ቀርቶ ብቸኝነትን የሚወድ ዝምተኛ ሆነ። ህይወቱ ደስታ የራቀው መሰለ። በሁኔታው ተደናግጠን ደጋግመን በመጠየቅ ያወቅነው ሊያጠቁት የሚከታተሉት ጠላቶች እንዳሉ እንደሚያምን ነው። ስልኩን እንደጠለፉት ያስባል፤ በላፕቶፑ ካሜራ ሳይቀር ያዩኛል ብሎ ስለሚሰጋ ካሜራውን ሳይሸፍን አይከፍተውም፤ ወጥቶ እስኪገባ ቤቱን ሲበረብሩ የቆዩ ስለሚመስለው ካሜራ ጠምዶ መሄድ ሁሉ ጀምሮ ነበር። ባጠቃላይ በታላቅ የመንፈስ ጭንቀት እየተሰቃየ ነው። የሚያሳዝነው ደግሞ ይህንን ጉዳቱን ለኛ ለቤተሰቡንኳ አብራርቶ አለመናገሩ ነው። ወንድሜ ለሰዎች እርዳታ ለመድረስና የሌሎች አዳኝ ለመሆን የማይታክት ሰውንጂ እንዲህ በሚያንገበግብ ስቃይ ውስጥንኳ ለራሱ አስቦ እርዳታን የሚጠይቅ ሰው አይደለም። ሁኔታውን በደበስባሳው በታወቀበት ጊዜንኳ የሚያስፈልገውን የህክምና በማቅረብ ስላልረዳነው ቤተሰቡ ሁሉ እንደግር ሳት ይከነክነዋል።እሱ ግን እንዲህ ባለ ጥልቅ የመንፈስ ጭንቀት ውስጥንኳ ለኛ አንድም ቀን ሳያስብ ቀርቶ አያውቅም።
ይህን የምታነቡ ወገኖች ሁሉ ዛሬ እኔ ይሄን ከምጽፍ እግዚአብሄር ምስክሬ ነው እሱ ወደነበረበት ጤናና ሁኔታ ተመልሶ እኔ ሞቼ ቢሆን እመርጣለሁ። ውሸት ከሆነ ይህንን በማድረግ የውሸቴን መልስ እንዲያሳየኝ አምላኬን እለምነዋለሁ። በኛ አገር መስሪያ ቤቶች የሰዎችን እውቀት ብቃትና ቁመና ሳይቀር ሲመዝኑ የዐይምሮ ጤንነት ሁኔታን አለመከታተላቸው እጅግ የሚያሳዝን ነገር ነው።
ወንድሜ ትናንት አውሮፕላኑ ውስጥ ከመግባቱ በፊት ምን አጋጥሞት ይሆን እነዛ የሚላቸው ሰዎች ሲመለስ ጠብቀው እንደሚገሉት ዝተውበት ያንን ፈርቶ ይሆን ወይም ፓይለቱ ከጠላቶቹ ጋር በመተባበር ሊይጠቃው እንደሚችል ብማመን ሰግቶ ይሆን ሲወጣ ራሱን ለመከላከል በሩን የዘጋው ከሁለቱ አንዱ ወይም ሁለቱም እንደሆነ አምናለሁ። አስቡት በዛች ቅጽበት አለሙን በሙሉ ሊያናጋ የሚችል ምንም አይነት ራሱን ሊከላከልበት የሚችል መሳርያ ሳይዝ ይህንን ድርጊት የሚያስፈጽም ምን ነገር ሊኖር ይችላል ስዊዘርላንድ ገነት አይደለችም። የዐይምሮ ህመም ሰለባ የሆኑ ሰዎችን ለዚያውም በማንም ላይ ምንም ጉዳት ባልፈጸሙበትና ሊፈጽሙም ባላሰቡበት ሁኔታ ወደስር ቤት እንዲወረወሩ ህግ የሚፈቅድ አይመስለኝም። ሃይለመድህን ለህይወቱ ሰግቶ ነበር። የሰው ልጅ ሊቋቋመው በማይችል የመንፈስ ጭንቀት ገሃዱና ሃሳባዊው አለም በተዘበራረቀበት የስቃይ አለም ውስጥ ብቻውን ሲሰቃይ ነው የቆየው። በተስተካከለ የዐይምሮ ጤንነት ላይ የሚገኝ ሰው ላይገባው ይችላል። እኔ ግን የሱን ግማሽ ባያክልም የተወሰነ ይህንን መሰል ችግር ስላለብኝ ህመሙን አውቀዋለሁ። ሁሌም በሳት እየተጠበሱ መኖር ማለት ነው
ወገኖች መልዕክቴን አንብባችሁ በምትችሉት ሁሉ ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ ፍትህ አግኝቶ ወደ ነበረበት እንዲመለስ በመጣር እንድትተባበሩን መላ ቤተሰቡ በምታምኑት ሁሉ እንለምናችኋለን! እኛም የሚያስፈልገውን የህክምና እርዳታ አግኝቶ ወደ ቀድሞው ጤናው ከተመለሰ በኋላ ለዚች አገር ባለው አቅም ሁሉ እንዲያገለግል በማድረግ እንክሳለን!
እባካችሁ ይህን መልእክት በማስተላለፍ ተባበሩን!

Tuesday 11 February 2014

ሰው ለሆኑ ሰዎች በሙሉ!


በጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፤ ከዝዋይ ማረሚያ ቤት
(ከኢትዮ-ምኅዳር ጋዜጣ የተወሰደ)
‹‹ይህንን ስለመሳሰሉ ጉዳዮች መወያየት ክልክል ነው፡፡›› በማለት በተንጎላጀጀ ድምፅ ጠባቂው ተናገረ፡፡ ቀጠል አደረገናም ‹‹መነጋገር የምትችሉት ስለቤተሰብ ጉዳዮች ብቻ ነው›› በማለት ተናገረ፡፡ ይህን ከላይ ያለውን ሐሳብ የሚመለከት ማንኛውም አንባቢ፣ ጉዳይ የተፈፀመው እዚህችው እማማ ኢትዮጵያ ሰማይ ስር ባሉ አጃኢበኛ እስር ቤቶች፣ ቤተሰብ መጠየቂያው እንደሆነ መጣራቱ አይቀርም፡፡
ይሁንና በመግቢያው ላይ ያለው ጽሑፍ ተቀንጭቦ የተወሰደ ‹እናት› ከተሰኘውና እ.ኤ.አ. በ1906 ከታተመው የስመ ጥሩው ሩስያዊ ደራሲ ማክሲም ጎርኪይ ታሪካዊ ልቦለድ ገፅ 102 ላይ ነው፡፡ የዛሬ 108 ዓመት አካባቢ ማለት ነው፡፡ አቤት ርቀቱ!… ይህ ርቀት ግን ለእኛ ምንም ማለት ያልሆነ ይመስላል፤ ለምን? ቢሉ ዛሬም ይህንንና ይህን የመሳሰለውን አስፍተን እየሠራን እንገኛለን፡፡ እንዲያውም በአንዳንድ ሁኔታዎች እየተጓዝን ያለነው የቁልቁለት ሩጫ በእጅጉ አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል፡፡
የነገሮች ሁሉ መድረሻ እስር ቤቶች እየሆኑ መጥተዋል፡፡ ‹ጠበቅ ያለ እርምጃ፣ የማያዳግም እርምጃ፣ የማስወገድ እርምጃ፣…› ወዘተ የሞሉ ከሕግ መርሕዎች ሳይሆን ከጥላቻ ፖለቲካ የሚመነጩ ፀያፍ አነጋገሮችን በሕዝብ የመገናኛ ዘዴዎች ሲተላለፉ እየሰማን እየታዘብን ነው፡፡ ቃል በቃል ‹ቀይ ሽብር ይፋፋም› ብሎ ማወጅ የቀራቸው የሕግም የግብረገብም ሚዛን ያልወጣላቸው ቀረርቶች በተለይ በእስር ቤት የምንገኝ ኢትዮጵያውያንን እየሰበሰቡን ይገኛሉ፡፡
በኢ.ቴ.ቪ. የአብዮታዊ እርምጃ ፕሮግራሞች በቀረቡ ማግስት አሁን በዝርዝር ብለው የብዙ ቤተሰቦችን ስሜት ሊያሸማቅቁ የሚችሉ ሰቆቃና እንግልቶች በአስደማሚ ስልት ተቀናብረው ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡ እስኪ የተወሰኑትን እንይ፡፡ ማንኛውም ታሳሪ ቤተሰብ በቅርብ ሊጎበኘው በሚችለው እስር ቤት ይታሰር የሚለው ሕግ የተሻረው በእኛ ላይ ነው፡፡ ዝዋይ የአገራችን ‹ሳይቤሪያ ግዞት› ማለት ናት፡፡ ቤተሰብ ያን ያህል የበርሃ ጉዞ አቋርጦ የእኛዋ ሳይቤሪያ ሲደርስ በአድካሚና ግብረ-ገብ በጎደለው ፍተሻ መከራውን ማየቱ አንሶ ጆሮ ግንዱ ላይ በቆሙ የቤተሰብ አገናኞች ቤተሰባዊ ገመናውን አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ሕፃናት ልጆች ወላጆቻቸው አንድ ላይ ሆነው ናፍቆታቸውን መወጣት አይችሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፖሊሶቹ ሲዘናጉልን ልጆቻችንን አቅፈን እንስማለን፡፡ ይህ ከሆነ ቁጣና ዘለፋው ምንም አይደለም፡፡ ግን በሁኔታው ሕፃናቱ ክፉኛ ይበረግጋሉ፣ የእኛ ስጋት ይጋባባቸዋል፤ በዚህም መንፈሳቸው እርብሽብሽ ብሎ ወደቤታቸው ይመለሳሉ፡፡
ሁኔታው በዚህ አያበቃም፡፡ ምንም እንኳን የመጠየቂያ ሰዓቱ በግልፅ የተቀመጠ ቢሆን ከቤተሰቦቻችን ጋር ገና መነጋገር ስንጀምር ‹‹በቃ… ቶሎ ጨርሱ›› የሚባልባቸው ጊዜዎች ብዙ ናቸው፡፡ ቀጥሎ የሚመጣው የእስር ቤት ማኅበራዊ ጉዳዮችን ማለትም ለሳሙና፣ ለምግብ ማጣፈጫ፣ ለሻይ ለቡና፣ ለውስጥ አልባሳት፣ ለውኃ ማከሚያ/ውኃ አጋር/ ወዘተ፤ ገንዘብ የሚያስፈልገን ቢሆንም እና እንደሚያስፈልጉ ቢታወቅም ጉዳዩ ለይቶለት የማሰቃየት፣ ማንገላታት፣ መበቀል ሆኗልና ለአንድ ወር ከአንድ መቶ ብር በላይ መጠቀም እንዳንችል የተከለከልን የመሆኑ አሳፋሪ ሐቅ ነው፡፡ ይህ እየተፈፀመ ያለው ደግሞ ዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ብቻ ነው፡፡ በዚህ የተነሳም ለመግለጽ በሚከብድ ሁኔታ ሰብኣዊ ክብራችንን የማዋረድ ሙከራዎች እየተፈፀሙ ነው፡፡
በአገራችን ላይ እኔ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን የጨረስኩት ዝዋይ በመሆኑ ብዙ ወዳጅ ዘመዶቼ በእዚህ ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ለአካባቢው ነዋሪዎች በሳምንት እንዲጠይቁን የተፈቀደላቸው አንድ ቀን /ረቡዕ/ ብቻ ሲሆን ‹‹የት ነው የምታውቁት? እንዴት አወቃችሁት? ምንድን ነው የሚያመላልሳችሁ?›› በሚሉትና በሌሎችም ጥያቄዎች ተደናግጠው መምጣቱን እርግፍ አድርገው ትተውታል፡፡
ሀገሩ ሞቃታማ ነውና በዚያ ላይ በእያንዳንዱ ቤት እስከ 150 ሰው ይታሰርበታል፡፡ ይህ ሁሉ ተደማምሮ እስረኛው የቱንም ያህል ፅዳቱን ለመጠበቅ ቢሞክርም የተባዩ መርመስመስ የእነ ትኋን እንዲህ መራባት፤ ለማሰብ እንኳን ይዘገንናል፡፡ ሌሊቱን ሙሉ ገላን ሲቆፍሩ ማደር ነው፡፡ ሊናገሩት ይከብዳል፣ አንባቢንም ቅር ያሰኛል፤ ግን ይህ የፊልም ትረካ ሳይሆን በእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ላይ ሆን ተብሎ እየተፈፀመ ያለ ደባ ነው፡፡ […] ግን የባሰ አታምጣ ማለት ነው!
ግን የባሰ ነገር አለ፡፡ አፈር ቅጠል የማይል ምግብ ይቀርብናል፡፡ ‹በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ› ከፍተኛ የውኃ እጥረት /ዝዋይ ሀይቅ አናት ላይ ተቀምጠን/ አለ፡፡ የእስር እስር እንዲሉ ጄኔራል መኮንኖቹን ጨምሮ አብዛኛዎቹ አባሪዎቻቸውና ሌሎች ሌሎች የተወሰንን እስረኞች የምንገኘው በልዩ ቅጣት ጭለማ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ይህንን ሁሉ እንደምንም ለመቋቋም ጥረት ማድረግ ይቻል ይሆናል፡፡ አዲሱ ስልት ግን መዘዙ በጣም አደገኛ በመሆኑ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ፣ እያንዳንዱ ሃይማኖት ያለው፣ ፈርሐ እግዚአብሔር ያለው፣ እያንዳንዱ የመሠረታዊ ሰብኣዊ መብቶችና ነጻነቶች መከበር የሚያሳስበው እያንዳንዱ ሰው የሆነ ሰው ሁሉ ሊያውቀው ይገባል ስንል ድምፃችንን እናሰማለን፤ በሕክምና ንፍገት ወደሞት እየተገፋን ነው፡፡
ከወር በፊት ገደማ ወጣቱ የአንድነት ፓርቲ አባል ናትናኤል መኮንን ለሕክምና በሪፈር ወደ ቃሊቲ ተልኮ የነበረ ቢሆንም፣ የዛኑ ዕለት ሕክምናውን ተነፍጎ ከሌሊቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ እስካሁን በሕመሙ እየተሰቃየ ይገኛል፡፡ የኢብአፓ ሊቀመንበር የነበረው ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር እንደዚሁ ለተጨማሪ ሕክምና ሪፈር ተብሎ ሲጠባበቅ ከቆየ በኋላ ዘዴው ተፈፃሚ ሆነበት እጁን አጣጥፎ ተቀምጧል፡፡ ከሕመሙ ጋር በተያያዘ በአካሉ ላይ አሳሳቢ ሁኔታ እየታየበት ይገኛል፡፡ ከዚህ ቀደም ገልጬው የነበረው የእኔ የኩላሊት ሕመም አሁን ለመቀመጥም፣ ለመንቀሳቀስ እያወከኝ የሚገኝ ሲሆን፣ እኔን ከቃሊቲ ዝዋይ ለማምጣት የተደረገው የተቀናጀ መረብ ሩብ ያህሉን ለሰብኣዊነት አውለውት ቢሆን ኖሮ እኔም ፋታ፣ እነሱም እርካታ ባገኙ ነበር፡፡ ሕመም ካልታከመ መጨረሻው ሞት ነው፡፡ የሞቱም ሰዎች አሉ!
የጄኔራል መኮንኖቹ አባሪዎች የነበሩት ኮረኔል ተስፋዬ ኃይሉ እና ኢንጂነር ክፍሌ ስንሻው፣ በዶክተር መረራ በሚመራው ኦሕኮ ፓርቲ አባል የነበሩት አሕመድ ነጃሺ፣ በጭለማ ቤት የከረመው ተስፋሀን ጨመዳ፣ የቤንሻንጉሉ አዛውንት ወዘተ ተገቢውን ሕክምና በማጣት ሕይወታቸውን ያጡ የእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ እንዴት ሕክምና ይከለከላል!? ግፍና ጭቆና ተቃውመው ደማቸውን ያፈሰሱና አጥንታቸውን የከሰከሱ ታጋዮችን በሥልጣን ማግስት ከፍርድ በመለስ በየእስር ቤቱ ያሉ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻቸው በሕክምና እጦት ሲረግፉ በእርካታ ማርመምን ከየት ተማሩት!? የኢትዮጵያ ሕዝብስ ምን ይላል!? ሰው የሆኑ ሰዎች ሁሉ ከቶ ምን ይላሉ!?
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ