Wednesday, 17 April 2013

የቀድሞ የህወሃት ታጋይ ወ/ት አረጋሽ አዳነ አዜብ መስፍንን ክፉኛ ተቹ


የቀድሞ የህወሃት ታጋይ ወ/ት አረጋሽ አዳነ አዜብ መስፍንን ክፉኛ ተቹ

ኢሳት ዜና:-ወ/ሮ አዜብ መስፍን የባለቤታቸው ወርሃዊ ደመወዝ አነስተኛ እንደነበር በመጥቀስ በኢህአዴግ ጉባዔ ላይ ያደረጉትን
ስሜታዊ ንግግር የሕዝብን የማመዛዘን ችሎታ ግምት ውስጥ ያላስገባ ነበር ሲሉ የቀድሞ የህወሃት ታጋይ ወ/ት
አረጋሽ አዳነ ተቹ፡፡
ወ/ት አረጋሽ በዛሬው ዕለት በአዲስአበባ ለንባብ በበቃው “ኢትዮ ምህዳር” ጋዜጣ በሰጡት ሰፊ ቃለምልልስ ላይ
የወ/ሮ አዜብን ንግግር አስመልክቶ ጠንከር ያለ ትችት ሰንዝረዋል፡፡አቶ መለስ በፔሮል 6ሺ500 ብር ደመወዝ
የሚከፈላቸው ብቸኛው መሪ እንደነበሩ ወ/ሮ አዜብ መናገራቸውን በመጥቀስ ጋዜጣው ላቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ
“የኢትዮጽያን ሕዝብ መቼም የማመዛዘን ችሎታ ያለው ነው፡፡የማስተዋል ችሎታ አለው፡፡ያውቃል፡፡የወ/ሮ አዜብ
አባባል ግን የሕዝብን የማመዛዘን ችሎታ በትክክል የሚመዝን አድርጌ አልወሰድኩትም፡፡ምክንያቱም ሕዝቡ እውነታው
ይህ እንዳልነበር ያውቃልና” ብለዋል፡፡
አያይዘውም ጠ/ሚ/መለስ ቤተመንግስት ውስጥ ነው የሚኖሩት፡፡ቤተመንግስት ደግሞ የራሱ አስተዳደር ያለው ትልቅ
ተቋም ነው፡፡ራሱን የቻለ ባጀት አለው፡፡ይህ ባጀት የት እንደሚውል የማይታወቅ አይደለም፡፡ቤተመንግስት ውስጥ
የሚኖሩ ሰዎች የሚተዳደሩበት፣የሚኖሩበት ነው፡፡እንግዶች የሚያስተናግዱበትና የሚጠሩበት በጀት አላቸው፡፡ይህ አሁን
የተፈጠረ ሳይሆን በፊትም የሚታወቅ ነገር ነው፡፡በየስብሰባው በሚሄዱበት ጊዜ ውጪ አገር ከሆነ በውጪ ምንዛሪ
ይከፈላቸዋል፡፡የአገር መሪ ስለሆነ የአልጋና የምግብ ሊከፍሉ አይችሉም፡፡ስለዚህ ምን ያህል የውጪ ገንዘብ
መሰብሰብ እንደሚቻል መገመት ይቻላል” በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
እነአቶ መለስ ልጆቻቸውን ውድ የተባለ ት/ቤት እንደሚያስተምሩ ያስታወሱት ወ/ት አረጋሽ አዳነ ከዛሬ 12 እና
13 ኣመት በፊት ለአንዱ ልጃቸው ብቻ በዓመት 35 ሺ ብር ይከፍሉ እንደነበር አውቃለሁ ብለዋል፡፡ሶስቱም
ልጆቻቸው በዚህ ሁኔታ እንደተማሩ ቢታሰብ ገንዘቡ በዓመት 100ሺ ብር ይከፍሉ ነበር ማለት ነው ካሉ በኃላ ይህን
በስድስት ሺ ብር ደመወዝ ሊያደርጉት አይችሉም ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ኢንዶውመንት የሚባለው ግዙፉ የኤፈርት ሐብት በወ/ሮ አዜብ ቁጥጥር ስር መሆኑም ወ/ት አረጋሽ
በማስታወስ በ6 ሺ ብር ገቢ ብቻ ኖረዋል የተባለውን አጣጥለውታል፡፡

ከፍንጂ ማምከኛ ድርጅት በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ሀብት ተዘረፈ


ከፍንጂ ማምከኛ ድርጅት በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ሀብት ተዘረፈ

ሚያዚያ ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በአፍሪካ ውስጥ ካሉ ሶስት የፈንጅ አምካኝ ድርጅቶች መካከል በአገልግሎት ዘመኑም ሆነ በተግባሩ በግንባር ቀደምነት ስሙ የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ፈንጅ አምካኝ ድርጅት ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ እንደፈርስ መደረጉን ተከትሎ፣ ከተለያዩ የውጭ አገራት በእርዳታ ከተሰጠው በመቶ ሚሊዮኖች ከሚቆጠር ገንዘብ በተጨማሪ፣ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶቹ በወታደራዊ መኮንኖች እንዲዘረፍ መደረጉን የውስጥ ምንጮች ገለጹ።
አብዛኞቹ የድርጅቱ ከባድ መኪናዎች እና ሌሎች ንብረቶች በወታደራዊ አዛዦች መወሰዳቸውን የገለጡት ምንጮች ጉዳዩ ያሳሳበው የጸረ ሙስና ኮሚሽን ምርመራ ቢጀምርም ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ምርመራውን አቋርጣል።
ከ100 እስከ 150 ሚሊዮን የሚጠጋ ገንዘብ መዘረፉን የገለጡት ምንጮች፣ ከዝርፊያው ጋር እጃቸው አለበት የተባሉት መኮንኖች በዘረፉት ገንዘብ ከፍተኛ ህንጻዎችን እያስገነቡበት መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአንድ የመምሪያ ሀላፊነት ቦታ ላይ የነበሩ ሰው ድርጅቱ  ከአውሮፓ እና ከአሜሪካ መንግስት ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እየተደረገለት በጥሩ ሁኔታ ሲሰራ ከቆየ በሁዋላ፣ በድንገት የተወሰኑ ወታደራዊ አዛዦች በድንገት ተመካክረውና በቂ ጥናት ሳይደረግበት ከ7 መቶ በላይ ሰራተኞችን በማባረር እንዲፈርስ አድርገውታል ብለዋል። ወታደራዊ አዛዦቹ የተወሰኑ ቁሳቁሶችን ለፌደራል ፖሊስ ያስረከቡ ቢሆንም፣ አብዛኛውን ንብረት ያለጠያቂ በመከፋፈል መውሰዳቸውን እኝሁ ባለስልጣን ገልጸዋል።
ከ3 ወራት በፊት ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው የነበሩት የድርጅቱ ሰራተኞች ሰሚ አጥተው ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውንም እኝህ ባለስልጣን ገልጸዋል።
ድርጊቱ በህወሀት ታማኝ ጀኔራሎች መካከል የጥቅም አለመግባባት ፈጥሮ እንደነበርም ታውቋል።
በኦሮሚያ ክልል ፍቼ ከተማ  የነበረው  ጽህፈት ቤት ፈርሶ በአሁኑ ጊዜ ሌላ ጽህፈት ቤት መቀሌ ውስጥ እንዲከፈት መደረጉንም እኝሁ ባለስልጣን ገልጸዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስት ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
በኢትዮጵያ ውስጥ ከላይ እስከታች የሚገኙ ባለስልጣናት የሚፈጽሙት ሙስና በአገሪቱ ውስጥ የሚታየውን የኑሮ ውድነት ከማባባስ በተጨማሪ በህብረተሰቡ ውስጥ ያለው የኑሮ ልዩነት እንዲሰፋ እያደረገው ነው።
ለገዢው ፓርቲ ቅርብ የሆኑ ሰዎች በአንድ ጀምበር ሚሊየነር የሚሆኑበት አሰራር በመጨረሻ አገሪቱን እንደሚጎዳ ብዙዎች አስተያየት ይሰጣሉ።
ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ የተባለው ተቋም ባለፉት ስምንት አመታት ከኢትዮጵያ ከ 180 ቢሊዮን ብር በላይ ተዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች መከማቸቱን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሌላ በኩል ግን አገሪቱ ከቻይናና ከህንድ የተበደረችውን ገንዘብ ሳይጨምር 150 በሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ የውጭ እዳ አለባት።
ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች እና የመንግስት ባለስልጣናት በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች የሚገነቡዋቸውን አንዳንድ ህንጻዎች በፎቶ ግራፍ በማስደገፍ ማቅረባችን ይታወሳል።
ኢህአዴግ በ9ኛው ጉባኤ ሙስናን ለመዋጋት ቃል መግባቱ ይታወሳል።

Tuesday, 16 April 2013

A message to Awramba Times editor Dawit Kebede


A message to Awramba Times editor Dawit Kebede

A message to the “professional Journalist” turned into “a TPLF Camelion” otherwise known as Dawit Kebede

by Kirubeal Bekele
We are going through a very depressing time in our whole existence as a society and as Ethiopians. TPLF is throwing outA message to Dawit Kebede of Awramba Times innocent people of ours that include children and women into the wild, making them victims of hunger, disease and dinners for wild animals. TPLF is working hard to destroy the concept of “Ethiopianism” by targeting the Amhara ethnic group in its quest to establish the dream of “Greater Tigray”. I have no doubt within fiver years, the size of Tigray’s territory would probably be twice as much as it is now. And the dream of “Greater Tigray” may become a reality right in front of our eyes. In the meantime. we continue to carry our enemies in our bosom. We are stuck in the habit of appeasing them wallowing in confusion, with lack of determination and devoid of a heroic action.
As we are witnessing this horrible human suffering of an unprecedented level in our history, a paid agent of TPLF by the name Dawit Kebede, who has been installed among our ranks, has finally come out of his hiding. And he is laboring day and night throwing peppers into our eyes. He is going after ESAT pursuing a relentless campaign to distract, defame and discredit this great media outlet of ours at every turn and opportunity he gets.
As ESAT’s outreach in Ethiopia as well as around the world is spreading like wild fire, TPLF has learned that Jamming ESAT in not enough. And they are right. It is not working. So, TPLF has to do something. Buy someone with a media experience, however feeble, green and stupid he is, among us. Boom! Dawit Kebede of Awramba Times showed up in their radar screen. Hence the beginning of an infamous adventure of Dawit Kebede’s injection into the Diaspora as a TPLF agent declaring war on ESAT and by extension on those patriots who uphold ESAT’s cause for freedom and democracy in Ethiopia.
First of all, I am honored for being labelled as “the G7 propagandist” by this greenish and sheepish TPLF mole. Am I that good to deserve such an honor? No, I am not that good to be given such an honor. Rather, I am good at something else that I can proudly announce to the whole wide world. Do you know what it is? You guessed it. I am excellent at sniffing a TPLF rat a mile away. I can snif and flash out a TPLF little dog such as Dawit Kebede. I am a bull dog fighter that can bark and bite at the same time. Others can’t bite while they are barking. Or they have the opposite problem. They can’t bark while they are biting, if they can bite at all. I can do both.
Let alone a TPLF chuwawa like Dawit Kebede, with a combination of brain and bravado, I can handle his TPLF masters who installed Dawit Kebede in the Diaspora. There is a good reason why I and my friends have become sleepless and penniless in Seattle pursuing the enemy day and night. It sounds like bluffing until Dawit and all the TPLF dogs that are mushrooming in the Diaspora get a taste of our bite. Let me put it this way. TPLF has found its match in me. Not only I have the brain power to slice a TPLF camelion like Dawit into pieces, I can turn from a “G7 propagandist” into a bone-crashing and arm twisting bulldog fighter with a speed of light.
I am not in the business of civility and appeasing the enemy within. I leave that to the naive crew. I am dying inside day and night as great men and women like Andualem Arage, Eskinder Nega, and Reeyot Alemu and others are being tortured and tormented in TPLF prisons. My heart is bleeding for those little Amhara children who are dying of hunger after being thrown out into the wild by TPLF as we speak. For most of us, this is just bad news and numbers. That is all. But it should outrage us and compel us into an outrageous action including going after TPLF agents and moles like Dawit who are happily and comfortably doing their evil thing among us. We should have the brain to know the difference between intolerance, democracy, and going after an enemy. We should not confuse one with the other. After 20 years of engaging TPLF, we should be able to know an enemy right away when we see one.
Appeasing the enemy in the name of intolerance and “professional journalism” is out right naivete in the face such an alarming horror our people are subjected to even as we speak. I can see them in my mind if not with my eyes. I am not a disciple of naive democracy where I unrealistically fantasize about a democracy that does not exist. Freedom is burning in my heart. I want my freedom back before anything else. The rest of you can slice, dice, and analyze democracy. Good that you have time for that. I don’t. I am desperate and hungry for freedom. I don’t have time like you do. It looks like you are planning to live on earth forever. You don’t sound and look like you are in a hurry. I don’t know about you. For me,I want the simple freedom of going back to my country and sit with friends and have a cup of coffee in Arat Kilo. Don’t you? I don’t know about you. But I need to be free. And be free now.
Dawit first came to Seattle after he took his new mission of targeting ESAT. We all received him with respect and warm friendship. We invited him into a Chinese restaurant and fed him until his tummy got red and hot. We said cheers for our health while we clicked our glasses. Little that we know, this mole was cheering for our death. We were hugging and welcoming our killer. Can you imagine embracing and hugging your killer? This is how we greeted this mole who finally has stabbed us on our backs. What a bad dream!
Fast forward one year since then, we are looking at a mole that has successfully penetrated us. Fortunately, we have succeeded in flashing him out, thank God. There is a saying in our country that sounds perfect when expressed in Amharic that applies to Dawit. ‘አር ላይ ተቀምጦ ፈስ ሸተተኝ ብሎ ያወራል ወይም ያማርራል”. After being hired as a mole by an ethno-fascist and racist mafia group like TPLF, this traitor,Dawit, has the audacity to complain about ESAT and is working hard to discredit it, if he can.
What if we turn the tables on Dawit this time. This mole is not about “professional Journalism” as he has claimed so many times. He frequently uses the CPJ Award he received by mistake as a hammer to hit hard on ESAT. He also claims “professional journalism” which he uses to launch his campaign of slash and burn the democratic opposition and their leaders in the Diaspora. How professional is this TPLF mole himself? Can he tell us what he did with the $36, 000 he got from National Endowment for Democracy? May be this will tell us something about his “professional Journalism”? What did he do with all this money?
I hope this mole won’t deny it because we have the information. Here is the link:http://www.ned.org/where-we-work/africa/ethiopia
Last but not least, I ask all of you patriots to drop your naivete, use your God given brains, put some steel in your backs and stop the rise of TPLF agents and moles in the Diaspora. The responsibility is totally on us. We have permitted TPLF and its agents to roam freely in our neighborhoods by our inaction and passivity. Do something about TPLF on a day to day bases. If you have money to spare, give it. If you have a brain, use it to dig TPLF’s grave. If you have time, go and throw an egg, the real I egg, at TPLF’s agents around you. If you shop in a TPLF store, stop it even it is cheaper. Boycott against all TPLF businesses including the money exchange businesses in your area. Go out and lobby to your senators and congressmen. Raise money generously to support our people who have been evicted and suffering on the streets in Bene Shangul and Gura Ferda. Women and children have nothing to eat. Go on a demonstration targeting TPLF spies wherever we live. Let us show them crime does not pay.
Forget a little mole like Dawit Kebede. Stop appeasing him. Get some respect for yourself to get some respect from the enemy. May be that is why they call us “Hadgi” and “Hodam”. If we had respect for ourselves, we wouldn’t have the stamina to let TPLF dogs roam freely among us. When TPLF moles and agents are boldly functioning and mushrooming among us, they will have more contempt and incentive to take even bolder steps against us.
This is not a time to sleep and slumber. It is time to act. Not in words but in deeds. Be impatient. Be restless. Be sleepless. Your people are suffering. Our comrades are being tortured and killed. Our country is being torn apart never to be the same. In the face of this kind of daunting horror, quit hugging and appeasing the enemy within. Go to work. You don’t live forever. Rise and save your country.

መንግስታዊ ተቋማት በሕዝብ ላይ የሚያደርሱት አስተዳደራዊ በደሎች ከዓመት ዓመት እያደገ ነው


መንግስታዊ ተቋማት በሕዝብ ላይ የሚያደርሱት አስተዳደራዊ በደሎች ከዓመት ዓመት እያደገ ነው

ሚያዚያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- የሕዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ከሕዝብ ከሚቀርቡለት አስተዳደራዊ በደሎች መካከል በመንግስት ላይ በተለይ በፍትህ
ተቋማት ላይ የሚቀርበው የአስተዳደራዊ ቅሬታ ብዛት ከፍተኛ መሆኑን አንድ ጥናት አመለከተ፡፡
ላለፉት አምስት ዓመታት ወደተቋሙ የመጡ ቅሬታዎች መካከል አንድ ሶስተኛ ወይም 31 በመቶ ያህል ከፍተኛ ድርሻ
የያዙት የመንግስት ተቋማት ላይ የሚቀርቡ ቅሬታዎች ማለትም ከቀበሌ መዋቅር አንስቶ አስከ ፌዴራል ባሉ እርከኖች
የሚመለከቱ ሲሆኑ ከነዚህ ተቋማት መካከል የፍትህ ዘርፍ ላይ የሚቀርቡት አቤቱታዎች በመጀመሪያው ረድፍ ላይ
እንደሚገኙ ጥናቱ ይጠቁማል፡፡
ጥናቱ አቤቱታዎቹ በየዓመቱ በአማካይ በሴክተር መ/ቤቶች በ160 በመቶ እያደጉ ናቸው ያለ ሲሆን
ከፍትሕ ተቋማት ጋር በተያያዘ የሚቀርቡት አቤቱታዎች ብዛት በ138 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን
ጠቁሟል፡፡
ለትምህርት ሚኒስቴር እና ለሌሎች የመንግስት ተቋማት የሚቀርቡ አቤቱታዎች ብዛት በ221 በመቶ፣ከመሬት
አስተዳደር መስሪያ ቤቶች ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ አቤቱታዎች ብዛት በየዓመቱ በአማካይ በ409 በመቶ ከፍተኛ
ዕድገት እያሳዩ መምጣታቸውን ጥናቱ ይጠቁማል፡፡
ከክልሎች ጋር ሲነጻጸር በአዲስአበባ አቤቱታ አቅራቢ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ጥናቱ ያመለክታል፡፡“ ከአገሪቱ ሕዝብ ብዛት አምስት በመቶ የማይደርሰውን የሕዝብ ብዛት የያዘችው አዲስአበባ ለተቋሙ ከሚቀርቡ የአስተዳደር በደል አቤቱታዎች አስከ 60 በመቶ ያህሉን ትሽፍናለች፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት የተቋሙ አገልግሎቶች በከተሞች አካባቢ ብቻ በመወሰኑ ነው ብሏል፡፡
ከሕዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም የተገኘው ይህው ጥናት ለአቤቱታዎቹ በየኣመቱ መጨመር ምክንያት ናቸው ያላቸውን ጉዳዮች
ዘርዝሯል፡፡
ለሕዝቡ አቤቱታ መጨመር አንዱና ዋንኛው ምክንያት የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም እንደነዚህ ዓይነት
ጉዳዮችን እንደሚመለከት በሕዝብ ዘንድ ግንዛቤ አለመኖሩና ተቋሙ መኖሩን የተገነዘቡ ሰዎች በየዓመቱ በመጨመራቸው
መሆኑን ይጠቅሳል፡፡
ጥናቱ ይህን ይበል እንጂ የእምባ ጠባቂ ተቋም ምንጮቻችን እንዳሉት አቤቱታዎቹ እየጨመሩ የመጡት በአገሪትዋ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በየጊዜው መባባስ ምክንያት አስተዳደራዊ በደሎች ከመብዛታቸው ጋር በተያያዘ መሆኑን በመጥቀስ የጥናቱን ግኝት የመንግስትን ገመና ለመሸፈን የተቀመጠ ነው ሲሉ ያጣጥሉታል፡፡
በአዋጅ ቁጥር 211/1992 የተቋቋመው የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ዋንኛ ተግባሩ ሕዝቡ ለሚያጋጥመውን
አስተዳደራዊ በደሎች ቅሬታ ሲቀርብለት ተከታትሎ እርማት እንዲያገኝ በማድረግ የዜጎች መብትና ጥቅሞች በአስፈጻሚው
አካል መከበራቸውን ማረጋገጥ ቢሆንም፣  ተቋሙ አቤቱታዎችን መቅረፍ ባለመቻሉ “ጥርስ የሌለው አንበሳ፣የህዝብ እምባ
አባባሽ ተቋም” የሚሉ ቅጽል ስሞችን አትርፏል፡

ምርጫ እናካሂዳለን ሲሉ ሰማሁ ልበል? (አቡ ዘኪያ)


ምርጫ እናካሂዳለን ሲሉ ሰማሁ ልበል? (አቡ ዘኪያ)

አቡ ዘኪያ
ከምድረ-አናቶሊያ
ምርጫማ ጥሩ ነው!
ምርጫማ ጥሩ ነው ጥሩ ነው ምርጫማ
“ድምፃችን ተሰርቋል” ካላላችሁማ!
ከቶ የት ይገኛል ምርጫን የመሰለ
ከውስጥም ከውጭም ታዛቢ ከሌለ
ተቃዋሚ ፓርቲ ጠፍቶልን ከአገሩ
ቢሆን “ጽቡቅ” ነበር ምርጫ በየወሩ!
ምርጫኮ ጥሩ ነው ክብሩ የገነነ
የምርጫ አስፈፃሚው የራስ ሰው ከሆነ!
እንደ ምርጫ አስደሳች የት ይገኛል እስቲ
በተለይ ከሌለ ተቃዋሚ ፓርቲ!!
“ከፀሐይ በታች” ከተሰኘው የሰለሞን ሞገስ የግጥም መድብል የተወሰደ
“ከሰው መርጦ ለሹመት ከእንጨት መርጦ ለታቦት”እንዲሉ ይሆነኛል ያሉትን ግለሰብ መርጦ ለሹመት ማብቃት በአፍሪካ የፖለቲካ ሕይወት ዉስጥ ነባር ባህል ነው::”አንድ ሰው አይፈርድም አንድ እንጨት አይነድም”የምትለዋ ብሒለ አበውም ዘመናትን ያስረጀች ነባሩንና አባት አደሩን የጋራ አመራር ላይ የተመሰረተ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ባህላችንን ጠቋሚ አፍሪካዊ የፖለቲካ ፍልስፍና ነች::ለአብነት የአምሐራዎችን ሸንጎ የትግሬዎችን ባይቶ የኦሮሞ ጌድኦና ኮንሶዎችን የገዳ ስርዓት ያስታውሷል::
ሃያኛው ክፍለ ዘመን አፍሪካ ስር-ነቀል ታሪካዊ ክስተቶችን ያስተናገደችበት ዘመን ነበር::መሰረታዊ የፖለቲካ ባህል ለውጥ አንዱና ቀንደኛው ስር-ነቀል ታሪካዊ ክስተት ነበር:: በስምምነት ላይ የተመሰረተው ባህላዊ አፍሪካዊ የመንግሥት ስርዓት(Traditional African Government by Agreement) ስፍራውን ለአውሮፓ በቀሉ ፉክክር ተኮር የፖለቲካ ስርዓት (Government by Competition) ለመልቀቅ የተገደደበት ዘመን ነበር ሃያኛው ክፍለ ዘመን:: የዛፍ ስር ስብሰባ በፓርላማ አባ ገዳዎች አባ
ዱላዎችና የጎበዝ አለቆች በሚኒስትሮችና ኮማንደሮች የቃል ሕግ በጽሁፍ ሕግ(ሕገ መንግሥት)ወዘተ ተተኩ::
ለሀገራችን ኢትዮጵያ የዘመኑን አውሮፓዊ የፖለቲካ ፋሽን መከተል የውዴታ ግዴታ ነበር::  የኢትዮጵያ “የስልጣኔ” አባት ተብለው የሚጠሩት ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ ነበሩ በሕይወታቸው የመጨረሻ ዓመታት ባንዱ የመጀመሪያውን ካቢኔ በመመስረት ኢትዮጵያን ከአውሮፓዊው የፖሊቲካ ስርዓት ጋር ያስተዋወቋት:: የአፄ ምኒሊክን አልጋ ወራሽ በመፈንቅለ መንግሥት አስወግደው አልጋ ወራሽ የሆኑት ራስ ተፈሪ መኮንን በ1911 ጃን ሜዳ ላይ መሀል ሰፋሪ በተሰኘው የቤተ መንግሥት ጦር በመታገዝ አስራ ሁለት አጋንንት ሆነው ተገኙ ያሏቸውን በአፄ ምኒሊክ የተሾሙትን አስራ ሁለት ሚኒስትሮች በማስወገድ የመጀመሪያውን የዘውድ ምክር ቤት ራሳቸው በመረጧቸው መኳንንት አባላት አቋቋሙ:: ምርጫና መረጣ ምክር ቤት፤ መካሪና አማካሪ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሕይወት ዉስጥ በገሀድ ብቅ ማለት ጀመሩ::
ሐምሌ 9 ቀን 1923 የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ታወጀ:: በቀጣዩ ዓመትም የሕግ መወሰኛ ምክር ቤትና የሕግ መምሪያ ምክር ቤት ተብለው የተሰየሙ ሁለት ምክር ቤቶች ያሉት ፓርላማ (bicameral parliament)ተመሰረተ:: ‹‹ሕዝቡ ራሱ መምረጥ እስከሚችል ድረስ የምክር ቤቶቹ አባላት በንጉሡና በመኳንንቱ ይመረጣሉ›› በሚለው ሕገ መንግሥታዊ አንቀጽ መሰረትም የሁለቱም ምክር ቤቶች አባላት የተመረጡት በንጉሠ ነገሥቱ ነበር::
በፋሽስት ኢጣሊያ ወራራ ሳቢያ የመበተን እጣ የገጠመው የመጀመሪያው ፓርላማ ለዳግም ትንሳዔ የበቃው በ1935 ነበር:: ሁለተኛው ፓርላማ እንደፊትኛው ሁሉ ባለ ሁለትዮሽ ምክር ቤት ነበር:: የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላትም በንጉሠ ነገሥቱ ይሁንታ የተመረጡ ነበሩ:: በሁለቱ ፓርላማዎች መካከል የነበረው መለስተኛ ልዩነት ከቀድሞው በተለየ መልኩ የሕግ መምሪያ ምክር ቤት አባላት በንጉሠ ነገሥቱ ሳሆን በሀገር ሽማግሌዎች የተመረጡ ባላባቶች መሆናቸው ነበር:: የሁለቱ ምክር ቤት አባላትም ለአስራ አምስት ተከታታይ ዓመታት በአባልነት ቆይተዋል::
በሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ተጽዕኖ ሳቢያ ንጉሠ ነገሥቱ ነባሩን ሕገ መንግሥት ለማሻሻል ተገደዱ:: በ1948 ተሻሽሎ በወጣው ሕገ መንግሥት መሰረትም ሕዝቡ በየአራት ዓመቱ እንደራሴዎቹን ራሱ የመምረጥ መብት እንዳለው ተደነገገ:: ያን ድንጋጌ ተከትሎም ከ1948 እስክ የካቲት 1966 ሕዝባዊ አብዮት ድረስ ባሉት ዓመታት አምስት የፓርላማ ምርጫዎች ተካሂደዋል::
መስከረም 2 ቀን 1967 ንጉሠ ነገሥቱን ከዙፋን አውርዶ ስልጣን ላይ የወጣው ወታደራዊ ጁንታ ፓርላማውን በትኖ በምትኩ ከተለያዩ የሠራዊቱ ክፍሎችና መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ 60 ግለሰቦችን ያቀፈ ከአንድ ዓመት በላይ በሕይወት ያልቆየ አንድ የመማክርት ጉባዔ መሰረተ:: ከመማክርት ጉባዔው ፍጻሜ በኋላ ለአስራ አንድ ዓመታት ያለ አንዳች ምክር ቤትና ሕገ መንግሥት ሀገሪቱን የመሩት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም የስልጣን እድሜ ፀሐያቸው እያሽቆለቆለች ባለችበት ወቅት ሕገ መንግሥት ቢጤና በኢሰፓዎች ጠቋሚነትና አስመራጭነት የተመረጡ 835 አባላት ያሉት አንድ ግብዳ ብሔራዊ ሸንጎ የተሰኘ ምክር ቤት እንካችሁ ማለታቸው ይታወሳል::
ግብዳው ብሔራዊ ሸንጎ “የሕዝብ” ብሶት በወለዳቸው ከሲታ ብሶታዊያን ከተበተነ ሁለት አሰርት አለፈው:: ከደርግ ውድቀት ወዲህ አራት አወዛጋቢና አስተዛዛቢ ብሔራዊና የአካባቢ ምርጫዎች ተከናውነዋል:: እነሆ አሁን ደግሞ አምስተኛውን የአካባቢና የአዲስ አበባ መስተዳድር ምርጫ ለማካሄድ በዋዜማ ላይ እንደሚገኙ ከወደ ገዥዎቻችን መንደር ሰማን::
የአካባቢ ምርጫ እንደ ዋነኛው ብሔራዊ ምርጫ በቀጥታ ለመንግሥት ስልጣን ባያበቃም ቅሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሕዝብን የልብ ትርታ የሚያዳምጡበትና ወደ ቤተ መንግሥት ለሚያደርጉት ጉዞ ስንቅ የሚሸምቱበት የፖለቲካ ገበያ ነው:: ይሁን እንጅ ባለፉት አራት የአካባቢ ምርጫዎች እንዳደረጉት ሁሉ ዋነኛ ተቃዋሚዎች አሁንም ራሳቸውን ከምርጫው ማግለላቸውን ይፋ አድርገዋል:: ምክኒያቱም ግልጽና ግልጽ ነው:: የሀገርና ሕዝብ ኃብት በተለይም የመገናኛ ብዙኃን ከዓመት እስከ ዓመት የገዥው ፓርቲ ፕሮፓጋንዳ ማሰራጫና የምርጫ ማስፈጸሚያ በሆኑባት፣ገልተኛ የምርጫ ቦርድ በሌለባት፣ ሀሳብን በነጻነት መግለጽ ወንጀል በሆነባት፣ መራጮች በገዥው ኃይል ካድሬዎች በሚዋከቡባት፣ የምግብ ለስራ ፕሮግራም ወደ ምግብ ለምርጫ ፕሮጀክትነት በተቀየረባት ባጭሩ የፖለቲካ ምህዳሩ በጠበበባትና የምርጫ ውድድር ሜዳው ወጣ ገባ በሆነባት ሀገር ዉስጥ ነጻ ፍትሃዊና እንከን አልባ ምርጫ ማድረግ ስለማይታለም ነው::
ከላይ ባጭሩ ለማሳየት እንደተሞከረው ባለፉት 81 ዓመታት ሀገራችን በርካታ ምርጫዎችን አስተናግዳለች:: እንዳለመታደል ሆኖ አንዳቸውም ነጻ ፍትሃዊና እንከን አልባ አልነበሩም:: ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ያስቆጠረው የሕዝባችን የነጻ ፍትሃዊና እንከን አልባ ምርጫ ጥያቄ እስከ አሁን ምላሽ አላገኘም:: ሕዝባችን ነጻ ፍትሃዊና እንከን አልባ ምርጫ ይሻል:: በነጻ ፍትሃዊና እንከን አልባ ምርጫ ብቻና ብቻ ነው ለውጥ ሊመጣ የሚችለው:: ነገር ግን እንዴት ነው ለውጥ በሌለበት ነጻ ፍትሃዊና እንከን አልባ ምርጫ የምናየው? እንዴትስ ነው ነጻ ፍትሃዊና እንከን አልባ ምርጫ በሌለበት ለውጥ የምናየው? ማየት የምንፈልገውን ዓይነት ምርጫ ለማካሄድ ለውጥ ያስፈልገናል:: ነገር ግን አሁን በሀገራችን ዉስጥ ባለው ነባራዊ ሁኔታ ለውጥን ማየት የማይታሰብ ነው:: አሁን በሀገራችን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ሳይለወጥም ምንም ዓይነት ነጻ ፍትሃዊና እንከን አልባ ምርጫ ማድረግ አይታለምም:: ያለ ነጻ ፍትሃዊና እንከን አልባ ምርጫም ሰላማዊ ለውጥ አይታሰብም:: በመሆኑም ስልጣን ለባለቤቱ ማለትም ለሕዝቡ እስኪመለስ ድረስ መታገል የግድ ነው:: ከሰላምዊ የትግል ስልቶች አንዱም በእሁዱ ምርጫ መሰል ልግጫ በመራጭነትም ሆነ በተመራጭነት ከመካፈል ራስን ማግለል ነው::
በሰለሞን ሞገስ ዉብ ስንኞች የጀመርኳትን ጦማሬን ከወራት በፊት ይህን ምርጫ አስመልክተው የደሴ ሙስሊሞች የገጣጠሟት ነች ተብላ በፌስ ቡክ በተሰራጨች አጠር ያለች ግጥም ልቋጭ:-
እኛ የለንበትም…
አንመዘገብም
አንወጣም አንመርጥም
ኢሕአዴግና ደርግ
ደርግና ኢሕአዴግ
አህያና ፈረስ፤ፈረስና በቅሎ
ቀልቀሎ ስልቻ፤ ስልቻ ቀልቀሎ
ሁሉም የጋማ ከብት ማን ከማን ተሽሎ
መምረጥስ ማየትን “ማየት”ዝም ብሎ!
ማን ነበር “ዝምታ ከጩኸት በላይ ይሰማል”ያለው?
መዓ ሰላማህ

Monday, 8 April 2013

ድሀ ከሆኑ አይቀርስ – ልክ እንደ አቶ መለስ


ድሀ ከሆኑ አይቀርስ – ልክ እንደ አቶ መለስ

(ኤፍሬም እሸቴ – http://www.adebabay.com)፦ ሰሞኑን በተካሔደው የኢሕአዴግ ጉባዔ ላይ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር የአቶ መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ያደረጉትናAzeb Mesfin is an Ethiopian, member of parliament  በኢቲቪ የዜና ዕወጃ ላይ የቀረበው ንግግራቸው የማኅበራዊ ድረ ገጾች የመወያያም የመሳሳቂያም የመሳለቂያም ርዕሰ ጉዳይ ሆኖ ነበር። “#SomeoneTellAzebMesfin” በሚል “ሐሽ ታግ/ #Hashtag” (ቅምር-ቃል ልበለው?) በትዊተር ላይ ኢትዮጵያውያን የግል ሐሳባቸውን ሲሰጡበት የቆዩት የወይዘሮዋ ንግግር ያተኮረው በአቶ መለስ ደሞዝና ድህነት ላይ ነበር።
ያልሰማ ካለ ንግግራቸውን ቀልበጭ አድርጎ ለማቅረብ፦ “ለቤተሰቤ፣ ለግሌ ሳይል የሞተ፣ አራት ሺህ ይሁን ስድስት ሺህ ብር የወር ደሞዝ በፔይሮል የሚከፈል ብቸኛ የአገር መሪ መለስ ብቻ ነበር። የኢሕአዴግ መዋጮ ተቆርጦ በሚተርፈው ገንዘብ እንተዳደርበታለን” ወይም ተዳድረናል የሚል ነው። ወይዘሮዋ ስለ ድህነታቸው ሲናገሩ ይህ የመጀመሪያ ጊዜያቸው አይደለም። ከዚህ ቀድሞም ተመሳሳይ ሐሳብ ሲናገሩ የሚያሳይ ቪዲዮ በየኢንተርኔቱ ላይ ተለጥፎ ተመልክቻለኹ። ለኢትዮጵያውያን ሐሳብ መነሻ የሆነው እንግዲህ በእኔ አባባል “እኛ ድሆች ነን” የሚለው አነጋገራቸው ነው።
አቶ መለስ ራሳቸው ከሁለት ዓመት በፊት አዲስ አበባ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ደሞዛቸው 6400 ብር (360 ዶላር አካባቢ) እንደሆነ ተናግረው ነበር። በርግጥ አቶ መለስ ድሃ ነበሩ ወይስ አልነበሩም ብሎ መከራከር ጉንጭ ማልፋት ካልሆነ በስተቀር ድሃ እንዳልነበሩ አገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው እውነታ ነው። ምናልባት ድሃ መሆን ማለት የተለየ ትርጉም ካልተሰጠው በስተቀር።
እንዲያውም አንድ የትዊተር ፀሐፊ የወ/ሮ አዜብን አባባል ከ18ኛው መቶ ክ/ዘመን የፈረንሳይ ልዕልት ቀበጥ አባባል ጋር አመሳስሎባቸዋል። ሜሬ አንቶውኔት (Marie Antoinette) የተሰኘችው ይህች ልዕልት በድህነት ይማቅቅ የነበረው የፈረንሳይ ሕዝብ “የሚበላው ዳቦ አጣ” ስትባል “ለምን ኬክ አይበላም” እንዳለች ይነገራል። የድህነት መመዘኛዋ የሚበላ በማጣትና ባለማጣት ላይ ሳይሆን በምርጫ እና በማማረጥ ላይ ነው። የወ/ሮ አዜብም ንግግር ይህንን ስላቅ እንድናስታውስ ግድ ብሎናል።
እውነቱን ለመናገር ድህነት እንዲህ ከሆነ፣ ድሃ መሆን እንደ አቶ መለስ ነበር። በቤተ መንግሥት እየኖሩ፣ አገር ምድሩን እያዘዙ እየናዘዙ፣ በስንትና ስንት ብረት አንጋች እየታጀቡ፣ መሬት እንዳይነካቸው በቀይ ምንጣፍ እየሄዱ፣ ጠዋት የበሉትን ማታ ሳይደግሙ፣ ልጆቻቸውን በእንግሊዝ ት/ቤት ብሎም በውጪ አገር እያስተማሩ፣ ምድራችን ያፈራችውን ምርጥ ልብስ እየለበሱ፣ ጠዋት ማት በቴሌቪዥን እየታዩ … ድህነት እንዲህ ነው።
ወይዘሮ አዜብም ድሆች ሆንን፣ ማቀቅን፣ በ6ሺህ ብር ደሞዝ ኖርን ሲሉ የሌላውም ሕዝብ ድህነት ልክ እንደርሳቸው የሆነ ከመሰላቸው ነው ችግር የሚገጥመን። ሌላው ሕዝብ በርግጥም በኑሮ ውድነትና በድህነት እየማቀቀ ነው። ነገር ግን ድህነቱ እርሳቸው ካለባቸው ድህነት ይለያል።
ሌላው ሕዝብ ከወር ወር በልቶ የሚደርስበትን ቀለብ መግዣ እያጣ፣ ለልጆቹ ልብስ፣ ለራሱ ነጠላ መግዣ እየተቸገረ፣ ከሰውነት ጎዳና ወጥቶ፣ በቀን ሦስት ጊዜ መብላት ስለማይችል በቀን አንድ ጊዜ (አንዳንዱም በፈረቃ) እየቀመሰ ነው የሚኖረው። በርግጥ ባለቤታቸው አቶ መለስ ስልጣን ላይ እንደወጡ ሕልማቸው (ራዕያቸው) ምን እንደሆነ ሲጠየቁ “የኢትዮጵያ ሕዝብ በቀን ሦስት ጊዜ ሲበላ ማየት ነው” እንዳሉት አልሆነም። ይባስ ብሎ ድሮ የነበረችውንም አጥቷል።
ያለፈ ሥርዓት ናፋቂ እንዳይሉኝ እንጂ ባለፉት ጊዜያት “ጤፍ ተወደደ” ሲባል የሚገባን “ጤፍ የማይበሉ ሕዝቦች ጤፍ መብላት በመጀመራቸው” ሳይሆን በርግጥም የእህል ችግር ስለነበር ነው። ጤፍ ባይበላ ስንዴውና ገብሱ፣ ሲቸግርም የፉርኖ ዱቄት እንጀራ አይጠፋም። ጎመንንና ቆሎን የመሳሰሉም ቢሆኑ ያጣ የነጣውም ቢሆን የማያጣቸው ነገሮች ነበሩ። የአሁኑ ድህነት ግን ቤት ዘግቶ የሚያስለቅስ፣ ወደ አደባባይ ወጥቶ ለመለመን የሚያስቸግር የእግር ውስጥ እሳት ነው።
በፌስቡክ አጫጭር ጽሑፎቿ የማውቃት ሕይወት እምሻው የተባለች አንዲት ፌስቡከኛ/ጦማሪት ከሰሞኑ ታክሲ ላይ የገጠማትን አንድ ገጠመኝ አንጀት በሚበላ አካኋን አስፍራው አንብቤያለኹ። ገጠመኟ ከዚህ ርዕሰ ጉዳይ ጋር ስለሚሔድ ልጥቀሰው። ነገሩ ሥራ ስለረፈደባት አንዲት የመንግሥት ሠራተኛ የሚያትት ነው። ልጅቱ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀች፣ በኤክስፐርትነት ተቀጥራ የምትሠራ፣ ደሞዟ ከምንም ከምንም ተቆራርጦ 865 ብር እጇ ላይ እንደሚገባ ትጠቅሳለች። እንደርሷ ዓይነት ብዙ ሰዎችን እንደምታውቅ ትነግረናለች – ሕይወት። አንጀት የሚበላው ነገር ደግሞ እንዲህ ይላል፦
“እጄ ላይ የሚገባው ደሞዝ 865 ብር ነው፡፡ ፡፡ የቤት ኪራዬ 300፡፡ ለዛውም ከከተማ የትናየት፡፡ አስፋልት ለመድረስ 30 ደቂቃ በእግሬ ኳትኜ፡፡ ክፍለ ሃገር ላሉት እናትና አባቴ ካለዚያ መኖር ስለማይችሉ በወር 150 ብር እልካለሁ፡፡ የሚተርፈኝ 400 ምናምን ብር፡፡ መብላት አለብኝ፡፡ መልበስ አለብኝ፡፡ ትራንስፖርቱ እንደምታይው ነው፡፡ በታክሲ መሄድ ከተውኩማ ቆይቼ ነበር …። ሰሞኑን ግን ብዙ ግዜ ስላረፈድኩ አውቶብስ ለመጠበቅ ፈራሁ፡፡ ከሁለት ዓመት ወዲህ ምግብ እንኳን በሥርዓቱ መብላት አልችልም፡፡ አይገርምሽም…? ምግብ መብላት አልችልም! ከዩኒቨርስቲ በዲግሪ ተመርቄ ሌላው ቢቀር መራብ አለብኝ?!” ድህነት እንዲህ ነው – ወ/ሮ አዜብ።
ድሮ የምናውቀው ድህነት ሥራ የሌለውን፣ ምንም ገቢ የማያገኘውን፣ ጉልበትና ዕውቀት ያጣውን የሚያጠቃ የአገር በሽታ ነበር። የዘመናችን ድህነት ግን ሰው ሥራ ኖረው አልኖረው፣ ዕውቀት ኖረው አልኖረው፣ ዲግሪ ተሸከመ አልተሸከም፣ ኮሌጅ በጠሰ አልበጠሰ የማይለቅ ነው። ኮሌጅ መግባትና መማር፣ ሥራ መያዝ በድሮው ጊዜ ራስን ለቻለ ኑሮ አስተማማኝ ነበር። ዛሬ ጊዜ ግን ከቤተሰብ አንድ ሰው ብቻ ሠርቶ ሳይሆን ባልም ሚስትም ደህና ገንዘብ እያገኙ የኑሮን ቀንበር ለመሸከም የሚንገታገቱበት ዘመን ላይ ነን። ድህነት ማለት ይኼ ነው ወ/ሮ አዜብ።
ምናልባት ይህንን ጽሑፍ የሚያነብ አንዳንድ ቅንጡ በቃ ይኼ ሁሉ ስለ ወ/ሮ አዜብ መናገር ምን ያስፈልጋል፣ እርሳቸው የተናገሩት ሦስት ደቂቃ፣ እናንተ የምታላዝኑት 30 ሰዓት ሊል ይችላል። እኔ ግን በርሳቸው አባባል ውስጥ የፓርቲያቸውን አካሔድ፣ አቋም፣ መሪ ተብለው ሥልጣኑን የተቆናጠጡት ሰዎች ከሕዝቡ የቀን ተቀን ኑሮ ምን ያህል የራቁ ሰዎች እንደሆኑ የምረዳበት ስለሆነ ብዙ ብዙ ሊባልበት እንደሚገባ ነው የሚሰማኝ። አገራችን “ለምን ኬክ አይበሉም” የሚሉ የቅርብ ጊዜ ቀዳማይት እመቤት ነው ያሏት ማለት ነው።
ምናልባትም ወ/ሮ አዜብን በተመለከተ ውይይቱ መቀጠል ያለበት የአዲስ አበባ ቀጣይ ከንቲባ ሊሆኑ እንደሚችሉ ከግምት በላይ እርግጠኝነት በመስፈኑም ነው። እንደ ፓርቲው አሠራር የፈለገውን ሐሳብ በሕዝብ አስተያት ምክንያት የሚለውጥ እንዳለመሆኑ አዜብም ከንቲባነታቸው ሳይታለም የተፈታ ይመስላል። ድህነትን በዚህ ደረጃ የሚመለከት ሰው እንዴት የድሀው ሕዝብ ከንቲባ ሊሆን ይችላል? ከንቲባዎች የግድ ድሆች መሆን የለባቸውም። ነገር ግን ድህነትን እና ሀብታምነትን የሚለዩ መሆን ግን ይጠበቅባቸዋል። ሕዝባቸውን ካላወቁት ምኑን ሊያስተዳድሩት ይችላሉ?
ወደ ሕዝብ ባለመቅረብና በቤተ መንግሥት ቤተ መንግሥታዊ ኑሮን በመኖር መለስን የሚስተካከላቸው አልነበረም። በሞታቸው ጊዜ ከየቪዲዮ ካዝናው እየወጣ ለማስተባበል እንደተሞከረው አልነበረም። የቦሌ መንገዶች ይመሰክራሉ። አካላቸው ከሕዝቡ እንደመራቁ ስለ ሕዝቡ እና ስለ ድህነቱ ያላቸው አስተያየት እንደሚስታቸው እንዳልነበረ ግን ቢያንስ ከንግግራቸው እንረዳለን።
ከኢሕአዲጎቹ ወደ ሕዝቡ በመቅረብ አቶ አርከብ የተሻሉ እንደነበሩ ብዙዎች ይናገራሉ። ወደ ሕዝቡ የዕለት ተዕለት ኑሮ ለመዝለቅ የደፈሩ ነበሩ። ሕዝቡም ለዚህ ቀረቤታ የአክብሮት ምላሹን ሰጥቷቸዋል። ፓርቲው ወደ ሕዝቡ መቅረብ ከፈለገ እንዲህ ዓይነት ሰዎችን ወይም እንዲህ ዓይነት አስተሳሰብ ያላቸውን መጠቀሙ ይበጀው ነበር። ከንቲባነትን ከአርከበ ወደ አዜብ ማውረድ ግን በሕዝብ ዕንባ መቀለድ ነው። ምናልባትም ለዚህ ዓይነቱ መራራ ቀልድ ፓርቲውም ዋጋ የሚከፍልበት ይመስለኛል።
ድሆች ባትሆኑም ድህነታችንን ብትረዱልን እንዴት ግሩም ነበር።
ይቆየን – ያቆየን
(ይህ ጽሑፍ አዲስ አበባ በሚታተመው አዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው።)

ለ3ኛ ጊዜ ህትመቱ የተቋረጠበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ” ከእንግዲህ ከጫካ መለስ ባሉ መታገያ መንገዶች በመጠቀም መብታችን እናስከብራለን” አለ


ለ3ኛ ጊዜ ህትመቱ የተቋረጠበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ” ከእንግዲህ ከጫካ መለስ ባሉ መታገያ መንገዶች በመጠቀም መብታችን እናስከብራለን” አለ

መጋቢት ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-እውቁ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይህን የተናገረው ልእልና ጋዜጣ በመንግስት ጫና እንዳድታተም ከታገደች በሁዋላ ነው። ጋዜጠኛ ተመስገን ” የንግድ ሚኒስቴር በልእልና ጋዜጣ የቀድሞ ባለቤትና በአዲሱ ባለቤት መካከል ህገወጥ የሆነ የስም ዝውውር ተደርጓል በማለት የንግድ ፈቃዱ  ” እንዲሰረዝ መደረጉን ተነግሯል።
ፍትህ ጋዜጣ በህገወጥ መንገድ እንዳይታተም ከተደረገ በሁዋላ፣ ጋዜጠኛው አዲስ ታይምስ መጽሄትን ከሌላ አሳታሚ ላይ በመግዛት ለተወሰኑ ሳምንታት ሲያሳትም ቆይቷል። መጽሄቷ በተመሳሳይ መንገድ እንድትዘጋ ከተደረገ በሁዋላ፣ ጋዜጠኛ ተመስገን እንደገና ልእልና ጋዜጣን ከሌላ አሳታሚ ላይ በመግዛት ስራውን ለመስራት ሞክሮ ነበር። ይሁን እንጅ ከ100 ሺ ብር በላይ በሆነ ወጪ የገዛው ጋዜጣ  ከመንግስት በተላለፈው ጫና እንዳይታተም በድጋሜ ታግዶበታል
ተመስገን በራሱ ስም ፈቃድ አውጥቶ መስራት ከተከለከለ፣ ከእንግዲህ ወዲያ ስለሚኖረው አማራጭ ሲጠየቅ፣ “ያለኝ አማራጭ ከሲቪክ ተቋማት ጋር በመተባበር ፣ ከጫካ ትግል በመለስ ያሉትን የሰላማዋ ትግል አማራጮች በመጠቀም ፣ አስገዳጅ ሁኔታ በመፍጠር መብታችንን እናስከብራለን” ብሎአል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ሰሞኑን በገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ከፍተኛ ወከባ ሲደርስበት እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል።  ተመስገን፣ ከ106 ያላነሱ ክሶችም እንዳሉበት ይታወቃል።