Thursday 28 August 2014

መስዋትነት


መስዋትነት ከኤልሳቤጥ ግርማ (ኖርዌይ)



ዛሬ ወያኔ የሥልጣን ዘመኑ በጨመረ ቁጥር የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍትህ ነፃነትና የዲሞክራሲ መብቱን እያጣ እንዲሁም የሚደርሰበት መከራ እየጨመረ መምጣቱ የማን አለብኝነትና የመኖር ዕድሜውን እያራዘመ እንደሆነ ማሳየቱን ቀጥሎአል።
ይህ ተግባሮት በቅርቡ በአቶ አንድአርጋቸዉ ፅጌ በሃገራችን በኢትዮጵያ ዉስጥ ፍትህ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን እዉቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀና ዝግጅቱንም በዕዉን ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ላይ እየደረሰ ያለዉ ግፍ እንኳን ያልበቃቸዉ ዛሬም ድረስ የስለላቸዉን መረብ እየዘረጉ ከጋሻጃግሬዎቻቸዉ ጋር በማበር ኢትዮጵያውያንን ከየቦታው እያሳደዱ በማሰርና በማሰቃየት ላይ ይገኛሉ።
እነርሱም አሁንም ቂመኞች ናቸው፤ እነርሱ አሁንም ዘረኞች ናቸው፤ እነርሱ አሁንም የዘር ፖለቲካ እየረጩ ነው፤ እነርሱ አሁንም ለህዝቡ ለፍቅርና ለይቅርታ ምላሻቸዉ ትዕቢትና እቢሪት ጥላቻና እልህ፣ ቂምና ክፋት እየሆነ ነው። ይህም አልበቃ ብሎአቸዉ እንደፈረስ እየጋለቡ በወጣቱ ትውልድ ላይ ዘመቻቸውን እንደቀጠሉ ይገኛሉ።
ታድያ ይህ በህዝባችን ላይ እየተፈፀመ ያለው ኢሰባዊነት እጅግ አሳዛኝና ዘግናኝ በመሆኑ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያንን በተለያየ ቦታና ጊዜ እረፍት እየነሳዉ በቁጭት ላይ ይገኛል። በመሆኑም በሃገራችንና በወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለው በደል አብቅቶ ያንን የምንናፍቀው ነፃነትና ፍትህ እንድንቀንናጅ ትግላችንን ማጠናከሩ አሁን ላይ አማራጭ የሌለውና እጅ ለእጅ ተያየዘን፣ ተደጋግፈን የአምባገነኑን ወያኔ እድሜ ማሣጠር የምንችልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። ሁላችንም የየበኩላችንን አስተዋዕፆ የምናሳይበት ሰዓት አሁን ነው።
አርበኛችንና የቁርጥ ቀን የሆነው ልጃችን አንዳርጋቸው እንዲሁም መሠል ኢትዮጵያዊያንን ወገኖቻችን በጨቋኙ መሪ እጅ ስር መውደቃቸው አንገታችንን የሚያስደፋና ተስፋ የሚያስቆርጠን ሳይሆን እንደውም ከምንግዜውም በላይ የትግላችን ስልት ቀይሮና አጠናክሮት ይገኛል ።
በመሆኑም የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህን በሃገርና በህዝብ እየደረሰ ያለውን በደልና ግፍ ለመታገልና ጨርሶ ከስሩ ለመገርሰስ ለትግሉ የሚጠይቀዉን ሁሉ መስዋትነት እየከፈለ ይገኛል።
በዚህም መሰረት በዓለም አቀፍ ደረጃ በኦገስት 31,2014 ባዘጋጀው ወቅታዊ ስብሰባና የድጋፍ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ በመካፈል ለሀገራችን ለኢትዮጵያና ለህዝቧ ነፃነት ፍትህ ያስፈልጋታል የምንል ኢትዮጵያዊያን ሁሉ በተመሳሳይም በኦስሎ በሚዘጋጀው ዝግጅት ላይ ተገኝተን ሃገራዊ ጥሪ አጋርነታችንንና ግዴታችንን መወጣት አለብን።

ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኖራለች!!!

No comments:

Post a Comment