Thursday 4 September 2014

በተማሪዎች ላይ የኃይል እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ተገለጸ

UNiversity students
በትምህርት በኢህአዴግ ጽ/ቤትና በትምህርት ሚኒስትር ትብብር ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሚሰጠው ስልጠና በተማሪዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ተገልጾአል፡፡ በስልጠናው ሰነድ ላይም ተካትቷል፡፡ ‹‹የትምህርት ተቋማትን ወደ ትክክለኛው የትግል ስልት የመመለስ አስፈላነት›› በሚል አብይ ጉዳይ ላይ በተሳሳተ ስልት ይንቀሳቀሱ እንደነበር በመጥቀስ ‹‹ተማሪው ጥያቄውን የሚያቀርበው ትምህርቱን እየተማረ፣ የትምህርት ቤቱን ህግና ደንቦች እያከበረ ሊሆን ይገባል፡፡…..ህገ ወጥ ሆኖ ህጋዊ ምላሽ ማግኘት አይቻልም፡፡›› በሚል ‹‹ህገ ወጥ ከሆኑ›› ህገ ወጥ ምልሽ እንደሚጠብቃቸው ያስጠነቅቃል፡፡

ሰንዱ አክሎም ‹‹በተማሪው ማህበረሰብ ውስጥ አፍራሽ አዝማሚያ ያላቸው ተማሪዎች ነውጥን ለማስፋፋት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በጥብቅ በመታልና የንብረት ውድመት እንዳይደርስ በጥብቅ መታል ይገባል፡፡ በቅድሚያ ራስን መነጠል እና ቀጥሎም የነውጥ ኃይል አራማጅና ደጋፊ የሆኑትን ማጋለጥና ትግል ማድረግ ይገባል›› በሚል በተማሪዎቹ ላይ ሊወሰድ የሚችለውን እርምጃ ይዘረዝራል፡፡
ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/34261

No comments:

Post a Comment