Wednesday 9 April 2014

ሙክታር ከድርና የኦሮሞ አክራሪዎች – ናዮሚ በጋሻዉ !


እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ሆነው አገልግሏል። አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ትልቅ ክልል የምትባለው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳነት ሆኗል። ሙክታር ከድር ይባላል። የኢህአዴግ አንዱ የሆነው የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክርሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ነው።
ከአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ 150 ኪሎሜትር ርቃ በምትገኝ ሄቶሳ በምትባል የአሩሲ መንደር አንድ ትልቅ ግንባታ ለማስመረቅ በክብር እንግድነት ይገኛል። አንድ ወንዝ ተገድቦ፣ ወይንም የጤና ጣቢያ፣ ትምህርት ቤት ተሰርቶ ለመመረቅ አይደለም የመጡት። እልም ባለ ገጠር መሃከል፣ አካባቢዉ ሁሉ ሜዳና እርሻ በሆነበት ቦታ፣ አንድ ትልቅ በአይነቱም፣ በይዘቱም የተለየ፣ ፈረንጆች እንደሚሉት ‘ዊርድ’ የሆነ ሃዉልት ቆሟል። የአኖሌ ሃዉልት ይሉታል።
በቀድሞ ጊዜ በገዳ ስራአት ጀግና የነበሩ የኦሮሞ መኮንኖችን ገድል የሚዘክር፣ ወይም በቅርብ ታሪካችን እንደ አብዲሳ አጋ፣ ባልቻ አባ ነፍሶ የተሰኙ የኦሮሞ ጀግኖችን የሚያሳይ ሃዉልት ቢሆን ሸጋ ነበር። ነገር ግን ሃዉልቱ ጡት የያዘ አንድ እጅን ያሳያል። ከመቶ አመት በፊት የሚኒሊክ ወታደሮች የአርሲ ኦሮሞዎችን ጡት ቆርጠዋል የሚሉትን የሌለ የፈጠራ ታሪክ ለማስታወስ ነዉ ብለው ሀውልቱን ያቆሙት። ያዉ በሚሊዮኖች በሚቆጠር ከሕዝብ ካዝና በተወሰደ ብር የተሰራ ሃዉልት። “አማራዎች እንደዚህ ጡት ቆራጮች ናቸው!” የሚለው የጥላቻ መልእክት በኦሮሞ ወጣቶች ላይ ከልጅነታቸው ጀምሮ ለማስረጽ ሆን ተብሎ የቆመ ሃዉልት። ኦሮሞው አማራዉን እንዲጠላ፣ እንድ ፍልስጤምና እስራኤል በመሃከላቸው ግድግዳ ተፈጥሮ እንዳይተማመኑ እንዲተላለቁ ለማድረግ የቆመ ሃዉልት። የሰይጣን የዲያብሎስ ሃዉልት!!!
በአኖሌ በአጼ ሚኒሊክ ወታደሮች ተደረገ የተባለው ጡት ቆረጣ መደረጉን የሚያረጋግጥ ምንም አይነት የጽሁፍ መረጃ የለም። ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በፓልቶክ ሲጠየቁ “ምንም አይነት የጽሁፍ ማስረጃ የለም፤ ግን በአፈ ታሪክ ነው የተላለፈው” ነበር ያሉት። የአጼ ሚኒሊክ ወታደሮች አያታቸውን አስረዉ ወፍጮ እንዲፈጩ ማስገደዳቸዉን የተናገሩት ዶ/ር ነጋሶ ፣ በወለጋ የሚኒሊክ ወታደሮች ጡት ቆርጠው እንደሆነ ሲጠየቁ “ወለጋ እንደዝያ አልሆነም” ነበር መልሳቸው። አጼ ሚኒሊክ በጎጃም በሃርረ፣ በወላይታ በበርካታ ቦታዎች ወታደሮቻቸው ልከው አስገብረዋል። በአርሲ ተደረገ ከሚባለው ማረጋገጫ ካልቀረበበት አፈ ታሪክ ዉጭ በሌሎች ቦታዎች የጡት ቆረጣ ተደረገ የሚል በአፈ ታሪክም አልተሰማም።
እንግዲህ እንደዚህ ዉሸት የሆነን አፈታሪክ በማራገብ ፣ ት/ቤቶችና ክሊኒኮች በመሳሰሉ ቁም ነገሮች ላይ ገንዘብ ከማጥፋት ይልቅ፣ ዘረኛዉና ጠባቡ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ይህ አይነቱን፣ ሕዝብን ከሕዝብ የሚያቃቅር፣ ዜጎችን ወደ እልህና ወደ ጦርነት እንዲሄዱ የሚገፋፋ፣ ጥላቻን በሰዎች ልብ ዉስጥ የሚዘራ፣ አሳዛኝና አስቀያሚ ሃዉልት ማቆሙ፣ ምን ያህል ለአገር ጥቅም ሳይሆን ለአገር መጥፋት እየሰራ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።
እስቲ ወደ ሙክታር ከድር መልሼ ልዉሰዳችሁ። በቅርቡ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ በኦሮሚያ ዉስጥ የሚኖሩ ኦሮሞ ያልሆኑ ኢትዮጵያዉያንን በተመለከተ በኦህደድ ወንጀሎች ስለተሰሩ ግፎች ሲናገሩ፡
«I do know that there are Oromo individuals who do say “ non-Oromos or those who do not speak Afan Oromo, have no rights. They are second citizens.” I have expressed already that I am against such people. This brings me back to the OPDO “Gimgama” of 1989. OPDO was then confronted with serious problems of human rights violation, corruption and anti-democratic Oromo nationalism. We evaluated the leadership, the cadres and members of OPDO under the motto “Clean OPDO from OLF attitude (anti-democratic/narrow) and Naftagna (please note that Naftagna is not equal to Amhara) practices (violation of democratic and human rights including corruption). The result of the “Gimgama” was that thousands were found out to have anti-democratic attitudes and carried out Naftagna practices. 189 cadres were imprisoned so that they are brought to justice because of high corruption and serious human rights violationስ. Thousands were expelled because of their bad attitudes and bad practices. Only about 300 were kept after receiving warnings” በማለት ነበር በኦህድድ አክራሪዎች የተፈጸሙትን ወንጀሎች የዘረዘሩት።
ማስጠንቀቂያ ተሰጧቸው ከነበሩ አክራሪ ዘረኞች መካከል ማን የሚገኝ ይመስላቹሃል? የአኖሌ የጥላቻ ሃዉልት መራቂ የሆነው ኦሮሚያን ኦሮሞ ካልሆኑት የማጽዳት አላማ በዉስጡ ያለው፣ የኢትዮጵያዉ ጀነራል ምላዲቹ ፣ ሙክታር ከድር አንዱ ነበር።
የኢትዮጵያ ህዝብ ከኢህአዴግ ምን ይጠብቃል የጥላቻ ሀውልት እንጂ!
«Among these were Alemayehu Atomsa and Muktar Kadir. Anyway, what was going on then was really very sad. Non-Oromo Ethiopian investors and traders were not welcome. Documents for bids for land were leaked out to Oromos so that they could win against non Oromo (for example against the 7 rich Gurage in Jimma). Shops were closed down. Boards to guide people were written only [in] Qube (no Amharic and English translation). Appeal documents written in Amharic were rejected. Schools refused to give lessons in Amharic. (With silly arguments “we were formally forced to learn in Amharic, now it is their turn to be forced to learn in Afan Oromo.) We will not pay money for Amharic teachers and books”). Unfortunately, I hear that the attitude and practice still lingers.» ይላሉ ዶር ነጋሶ በጽሁፋቸው።
ታዲያ የሙከታር ከድር ዘረኛና የጥላቻ ታሪክ እየታወቀ፣ የኦሮሚያ ፕሬዘዳንት ማድረጉ፣ የአኖሌን የጥላቻ ሃዉልት ማቆሙ፣ ኦሮሞዉን ለመጥቀም ነው ወይንስ ኦሮሞውን ከሌላ ህዝብ ጋር ለማጋጨት? ኦሮሞው ከሌላው ሕዝብ ጋር የተዛመደ፣ የተዋለደ፣ የተሳሰረ አይደለምን? ለዲሞክራሲ ቆመናል የሚሉት፣ የኦሮሞ ድርጅት መሪዎችስ ይሄን የነሙክታር ከድር መርዝ ማዉገዝ የለባቸውምን? ለኦሮሞው ከአማራዉ፣ ከጉራጌዉ፣ ከጉሙዙ፣ ከቡርጂዉ፣ ከሲዳማው፣ ከጌዴዎው፣ ከሶማሌው ጋር አብሮ ተከባብሮ፣ ተስማማቶ መኖር አይሻለዉምን ? ለምንስ እነዚህ አካራሪ ኦሮሞዎች ጠብ ይፈልጋሉ? ለምን ተነጥለው ለመታየት ይሞክራሉ? የሚያስተሳሰር፣ የሚያቀራራብ፣ አንድ የሚያደርገን ማብዛትና ማስፋፋት እንጂ የሚያጣላና የሚያቃቅር ነገር ለምን እንጭራለን ?
አክራሪዎች በአኖሌ እንዳየነው አይነት ካከረሩ፣ ኦሮሞ ለኦሮሞዎች በሚል፣ ባለፈበትና በማይሰራ ባዶ ፉከራ ከተነሱ፣ በዚያኛዉ ወገን ያሉት ተመሳሳይ እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ ዘነጉትን? ወይስ “በዙሪያችን ካሉ ሌሎች ሕዝቦች እዚያ ማዶ ያለው የትግሬ ጦር ይጠብቀናል” የሚል ግምት አላቸው? እነዚህ አክራሪ ኦሮሞዎች ሰው ዝም ሲላቸው ትንሽ ልባቸው ያበጠ መሰለኝ። አላወቁትም እንጂ፣ እንዲሁ በባዶ ባበዱ ቁጥር እራሳቸዉን ነው የሚያስገምቱት። አለም በግሎባላይዜሽን በተሳሰረችበት ዘመን፣ ምን ያህል ኋላ ቀሮች መሆናቸዉን ነው የሚያሳዩት።
እንግዲህ ልብ ይገዙ ዘንድ እመክራቸዋለሁ። ጥላቻ ለማንም አይጠቅም። እልህ ለማንም አይጠቅምም። ዘረኝነት ለማንም አይጠቅምም።
ኢትዮሚድያ – Ethiomedia.com
April 8, 2014

No comments:

Post a Comment