Saturday 14 September 2013

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አንዳርጋቸው ጽጌ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሕዝብ ጋር ሊወያዩ ነው



(ዘ-ሐበሻ) የግንቦት 7 ንቅናቄ አመራር የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እሁድ ሴፕቴምበር 22 ቀን 2013 በዋሽንግተን ዲሲ/ ቨርጂኒያ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለሕብረተሰቡ ገለጻ ለማድረግ ሕዝባዊ ስብሰባ መጥራታቸውን የመርሃ ግብሩ አዘጋጆች ለዘ-ሐበሻ በላኩት በራሪ ወረቀት አስታወቁ። “የወቅቱ የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታና ለነፃነትና ለዴሞክራሲ የሚደረገው ትግል ላት ገለጻ ይደረጋል” በሚል በአርሊንግተን ቨርጂኒያ ከቀኑ 2 ሰዓት ጀምሮ የተጠራው ይኸው ሕዝባዊ የውይይት መድረክ ሰፊ የጥያቄና መልስ ክፍል ስለሚኖረው ማንኛውም ኢትዮጵያዊና ኢትዮጵያን ወዳጅ በመገኘት እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ለዚህ ሕዝባዊ ውይይት መድረክ የመጥሪያ በራሪ ወረቀት የሚከተለው ነው::

No comments:

Post a Comment