Friday 8 March 2013

ኢህአዴግ እንደ ድርጅት አንድ ሆኖ መውጣት ተስኖታል ተባለ


የካቲት ፳፯ (ሃያ ሰባትቀን ፳፻፭ / 

ኢሳት ዜና:-በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች የውስጥ ሽኩቻ መበራከት የተነሳ ኢህአዴግ እንደ ድርጅት አንድ ሆኖ መውጣትእንደተሳነው የሚያመለክቱ መረጃዎች እየወጡ ነው።

በህወሀት ውስጥ ሁለት ቡድኖች ድርጅቱን ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ መጀመራቸው ከተዘገባ ከወራት በሁዋላ ችግሩከመቃለል ይልቅ እየጨመረ መምጣቱን አንድ የቀድሞ የህወሀት ነባር ታጋይ ለኢሳት ዘጋቢ ገልጸዋል።

ነባር ታጋዩ፤ በአቶ ስብሀት ነጋ በኩል ባሉ ሰዎች ወደ ድርጅቱ እንዲመለሱ ጥሪ ቀርቦላቸው እንደነበር ጠቅሰው፤  እርሳቸውግን አሻፈረኝ ማለታቸውን ገልጸዋል።

በድርጅቱ ውስጥ የሚታየው ክፍተት ለአደባባይ ባይበቃም፣ ህዝቡ የሚያየውና  እየተነጋገረበት ያለ ጉዳይ መሆኑን ነባርታጋዩ ገልጸዋል። በኦህዴድ በኩል ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በሁዋላ የታየው ክፍተትም እየሰፋ እንጅ እየጠበበ ሲሄድአለመታየቱ ነው የተገለጸው።

ከአንድ ወር በፊት የጨፌ ኦሮሚያ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት በድርጅቱ ውስጥ የሚታየው ሙስና እና ጎሳዊነትእንደጨመረና ድርጅቱንም አደጋ ላይ እንደጣለ አንዳንድ የምክር ቤቱ ተወካዮች ቢናገሩም፣ ምክር ቤቱ በስፋትእንዳይወያይበት መደረጉን በወቅቱ መዘገባችን ይታወሳል።

በተለይም በከፍተኛ ህመም የሚሰቃዩትን ፕሬዚዳንቱን አቶ አለማየሁ አቶምሳን ለመተካት ቢፈለግም፣ በእርሳቸውና በአፈጉባኤ አባዱላ ገመዳ ደጋፊዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ሌላ ፕሬዚዳንት ለመሾም ሳይቻል በመቅረቱ አቶአለማየሁ  በስልጣን  ላይ እንዲቆዩ ተደርጓል።

በኦህአዴድ ስራ አስፈጻሚዎች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ተባብሶ በዞን ደረጃ ያሉ ስራ አስፈጻሚዎች ሳይቀሩእንደተከፋፈሉና አጠቃላይ ድርጅቱ ወደ ሞት እያመራ እንደሆነ መዘገባችን አይዘነጋም።

ሪፖርተር  ዛሬ ባወጣው ዘገባ ደግሞ ኦህዴድ የካቲት 20 ቀን 2005 .ጠቅላላ ጉባዔውን ለማድረግ የተሰበሰበቢሆንም ፤ያልተጠበቁ አጀንዳዎች በመቅረባቸው  ለኢሕአዴግ በሚቀርበው የሁለት ዓመታት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትላይ ብቻ በመወያየት ጉባዔውን ለሚቀጥለው ሳምንት አስተላልፎአል።

የኦህዴድ አባላት፤ ድርጅታቸው የተለያዩ ችግሮች ስላሉበት ጉዳዩ  በአጀንዳ ተይዞ ውይይት እንዲደረግበት ጥያቄማቅረባቸውን ተከትሎ፣ የሥራ አስፈጻሚው ኮሚቴ ሰብሳቢዎች በድጋሚ ሌላ ስብሰባ እንደሚደረግና በዚያ ስብሰባ ላይአሉ” የተባሉ ችግሮችን በማንሳት መወያየትና መፍታት እንደሚቻል ቢናገሩም፣ ስምምነት ላይ አልተደረሰም ብሎአል-ጋዜጣው።

አባለቱ፤ ችግሩ የሕልውና ጉዳይ መሆኑን ደጋግመው በመግለጽ ራሱን የቻለ አጀንዳ ተይዞለት ውይይት እንዲደረግበትቢጠይቁም፣ እንዲሁም የተወሰኑ አባላት ድርጅቱ በሁለት ዓመታት ውስጥ ባከናወናቸው ሪፖርት ውስጥ የተነሳው ጥያቄተካቶ አንድ ላይ እንዲታይ ሐሳብ ቢያቀርቡም ፤ስምምነት ላይ ስላልተደረሰ ነው ጉባዔው እንዲተላለፍ የተደረገው።

ሥራ አስፈጻሚው፤ ለኢሕአዴግ በሚያቀርበው የሁለት ዓመታት ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ሲወያይ በዋናነት ያነሳቸውችግሮች፣ በድርጅቱ ውስጥ የአመራር ችግር መኖሩን፣ እንደ ድርጅቱ ሳይሆን በግል የመጠቃቀም ሁኔታ መባባሱን፣ለሥልጣን መሯሯጥ መስተዋሉን፣ ድርጅት ሳይመክርበት የፍርድ ቤት ሹማምንት ከኃላፊነት እንደሚነሱ መደረጋቸውን እናየግለሰቦች አምባገነንነት መንገሱን  የሚመለከቱ ናቸው።

አባላቱ በችግሮቹ ዙሪያ ከተወያዩ በኋላ፣  የተፈፀሙት ድርጊቶች ተገቢ እንዳልሆኑ መተማመናቸውን ጋዜጣው አክሎዘግቧል።

ከዚህም ባሻገር የኦህዴድ ስራ አስፈጻሚ አባል የነበሩት አቶ ጁነዲን ሳዶ ከድርጅት ተባረው አገር ጥለው መጥፋታቸውእንዲሁም በድርጅቱ ውስጥ በርካታ የእስልምና እምነት ተከታዮች መንግስት የሚከተለውን ፖሊሲ መቃወምመጀመራቸው በኦህዴድ ብቻ ሳይሆን በኢህአዴግም ውስጥ ትልቅ ራስ ምታት ፈጥሯል ተብሏል።

ለኢሳት ቅርበት ያላቸው የኢህአዴግ  ሰዎች እንደገለጡት፣ በርካታ የኢህአዴግ በተለይም የኦህዴድ አባላት ሙስሊምኢትዮጵያውያን የጀመሩትን እንቅስቃሴ ከመደገፍ አልፈው በተለያዩ መንገዶች አስተዋጽኦ እያደረጉ ነው።

በኢህአዴግ ውስጥ የሚታየው ልዩነት ያሳሰበው ሪፖርተር  ጋዜጣ ዛሬ በርእሰ አንቀጹ ድርጅቱ በመጪው ጉባኤ አንድ ሆኖበመውጣት ለአገሪቱ የተጠናከረ አመራር እንዲሰጥ ተማጽኗል።  

ጋዜጣው ” ሁኔታዎች እየከበዱና እየተካበዱ ናቸው፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃም በአገር ደረጃም የኢኮኖሚው ሁኔታ አሳሳቢእየሆነ ነው፡፡ ምንም እንኳ አሁንም በኢትዮጵያ ከፍተኛ ዕድገት ለማስመዝገብ የሚያስችል አመቺ ሁኔታ ቢኖርም፤የውጭምንዛሪ እጥረትን፣ ግሽበትንና የኑሮ ውድነት ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም፤ ለተጀመሩና ለታቀዱ ዓበይት ፕሮጀክቶችማስፈጸሚያ በቂ ገንዘብ አግኝቶ መተግበር ትልቅ ፈተና ነው” ብሏል።

የመልካም አስተዳደር መጥፋት፣ የአቤቱታ ብዛትና የሰሚ እጦት እጅግ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱንም አልሸሸገም።
ጋዜጣው አያይዞም፦ ” መጪው የኢህአዴግ ጉባኤ ጠንካራ ኢሕአዴግና ጠንካራ መንግሥት ፈጥሮ፤ ጠንካራ መፍትሔበመስጠት እንደ አንድ ኩሩ ሕዝብ እጅ ለእጅ ተያይዘን እንድንቀጥል ማድረግ  ይጠበቅበታል ፣ህዝብም ጠንካራ ኢሕአዴግከጉባዔው እውን እንዲሆን ይጠብቃል” ብሎአል።

በሌላ በኩል ደግሞ በአገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች የኢህአዴግን መዳከም በመጠቀም ወደ አንድነት ጎዳና በማምራትለለውጥ መስራት እንዳለባቸው ከተለያዩ ወገኖች ጥሪ እየቀረበ ነው።

በቅርቡ በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች በተካሄደ የኢሳት ገቢ ማሰባሰብ ዝግጅት ላይ የተገኙ ኢትዮጵያውያን፤ ኢሳት ሁሉንምተቃዋሚዎች በአንድ ጉባኤ በመጥራት አብረው እንዲሰሩ ግፊት እንዲያደርግ ተማጽነዋል። 

No comments:

Post a Comment